Get Mystery Box with random crypto!

"ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒

የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodoxtewahdoc — "ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒
የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodoxtewahdoc — "ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒
የሰርጥ አድራሻ: @orthodoxtewahdoc
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 22.88K
የሰርጥ መግለጫ

🌹«ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን
/አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ።♥ https://t.me/Orthodoxtewahdoc

ሐምሌ 3 በ2014 ዓ°ም ተከፈተ።
📌እግዚአብሔር ቢፈቅድ የቅዱሳኑን ታሪክ እንመማርበታለን ብለን ከፈትነው ቅዱስ እግዚአብሔር ይፍቀድልን አሜን‼
❤የእመ ብርሃን ልጅ🤗

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2023-05-12 15:59:45 #አቡነ_አሮን_ማለት_ማን_ናቸው

☞•• ወር በገባ በ5 ጣራ ክፍት ሆኖ ዝናብ የማያስገባው  የአባታችን የአቡነ አሮን (ዘመቄት) ወርሐዊ መታሰቢያቸው ነው፡፡የመቄቱ አቡነ አሮን ወላጅ አባታቸው የላስታው ጻድቁ ንጉሥ ዐፄ ገብረ መስቀል ነው፡፡

☞የላስታ ነገሥታት የዘር ሐረጋቸው ከንጉሥ ሰለሞን ዘር ሲያያዝ የመጣ ነው፡፡
☞ከ 10ኛው እሰከ 13ኛው መቶ ክፍለ ዘመን (920-1253) ዓ/ም ገደማ
በላስታ ቡግና ምድር የነገሡ የላስታ ቡግና ተወላጅ የሆኑ የኢትያጵያ ቅዱሳን
ነገሥታት የንግሥናቸው መጠሪ የዛጉዌ ሥርወ መን በመባል ይታወቃል፡፡
☞የንጉሥ ሰለሞን ዘር የሆነው መራ ክርስቶስ 3 ልጆችን ወለደ፡፡ እነሱም
ጠንጠወድም፤ ግርማ ስዩምና ዣን ስዩም ናቸው፡፡
]☞ጠንደውድም ገብረ መስቀልን ወለደ፤ ገቡረ መስቀልም አቡነ አሮን ወለደ፤
ግርማ ስዩም ይምርሐነ ክርስቶስን ወለደ፤ ዣን ስዩም ደግሞ ገብረ ማርያምንና
ላሊበላን ወለደ፡፡ ገብረ ማርያም ነዓኩቶ ለአብን ወለደ፡፡ አነዚህ ቅዱሳን
ነገሥታት እንደ መልከጸዴቅ ክህነትነን ከንግሥና ቅድስናን ከንጽሕና ጋር አንድ
አድርገው በመያዝ እግዚአብሔርንም ሕዝብንም በቅድስናና በንጽሕና
አገልግለው አልፈዋል፡፡
☞ወደ ቀደመ ነገራችን እንመለስ አቡነ አሮን በ5 ዓመታቸው ሙት
አስነስተዋል፡፡
☞በ16 ዓመታቸው መንነው ዋልድባ ገዳም ገብተዋል፡፡
☞በሀገራችን እየተዘዋወሩ ወንጌልን ሲሰብኩ የሸዋው ንጉሥ አንኮበር ድረስ
ጠርተዋቸው ሄደው ሲመለሱ አዋሽ ወንዝ ሞልቶባቸው አገኙት፡፡ ሲሻገሩ
ዳዊታቸውን ወሰደባቸው፡፡ አሁንም በድጋሚ ሌላ ጊዜ በሸዋው ንጉሥ አንኮበር
ድረስ ተጠርተው ከ7 ዓመት በኃላ ተመልሰው በአዋሽ ወንዝ ሲሄዱ መልአክ
መጣና"መቋሚያህን ወደ ወንዙ ላክ አላቸው፡፡ መቋሚያቸውንም ቢልኩ
ዳዊታቸውን ይዘው አወጡ፡፡
☞ዳዊቱም በውኃው አልራሰም ነበር፡፡ ይልቁንም አቧራውን አራግፈው
ፈጣሪያቸውን አመሥግነው ዳዊታቸውን ይዘው ሄደዋል፡፡ ያ ዳዊታቸው ዛሬም
ድረስ በጋይንት አብርጎት ቅዱስ ሚካኤል ይገኛል፡
☞ሰሜን ወሎ መቄት ወረዳ የሚገኘው እጅግ አስደናቂ ገዳማቸው ፍልፍል ዋሻ
ሲሆን ጣራው ክፍት ነው፡፡ ክፍት በሆነው ጣራ በኩል ፀሐይ ሲገባ ሰለሚያቃጥል
ጥላ ይይዛሉ ነገር ግን የጻድቁ ግዝት ስላለበት ዝናብ ወደ መቅደሱ ፈጽሞ
አይገባም፡፡
☞አቡነ አሮን በአንቺም ሜዳ በሚባል ቦታ ፀሐይንም ገዝተው አቁመዋታል፡፡
☞ከታች ጋይንት ተነሥተው መንገድ ሲሄዱ በሰንበት ቀን በሬ ጠምዶ ሲያርስ
የነበረን ገበሬ ለምን በሰንበት ታርሳለህ ቢሉት ምቀኛ መነኩሴ ብሎ በጅራፉ
ቢገርፋቸው በሬዎቹ ግን ፈጽሞ አልንቀሳቀስ ብለው ቆመዋል፡፡
☞በዚህ የተናደደው ገበሬም አቡነ አሮንን መሬት ላይ ጥሎ ገረፋቸው፡፡ እሳቸው
ተነሥተው ሲሄዱ ዛፎች ተነቅለው እየተከተሏቸው ቃል አውጥተው በሰው
አንደበት አመስግነዋቸዋል፡፡
☞የህንጻው አይነት☞ ስቁረት ሁለት አምዶች አስራ አራት መስኮት ሰባት
አንደኛው ስቁርት ዝናብ የማይገባበት ፀሐይና ጨረቃ እንዲሁም ከዋክብት
ብርሃናቸውን የሚሰጡበት ለማየት የሚያስደንቁ ሁለተኛው ብርሃናትም
ዝናባትንም ይፈራራቁበታል፡፡ የወረደው ወይም ዝናብም ወዴት እንደሚሄድ ወይም
የት እንደሚጠራቀም አይታወቅም፡፡ ይህንን እነደዚህ አድርገው አንፀው ወደ
ፈጣሪያቸው አመለከቱ፡፡
☞ክብር ምስጋና ይግባውና ጌታችን መላእክት አስከትሎ ወርዶ ቤተ መቅደሱን
ባርኮ ቃል ኪዳኑን አፅንቶ አስከ ምፃት ድረስ እንዲሁ እያበራች ትኑር ብሎ
አርጓል፡፡
☞አባ አሮን መንክራዊም ቃል ኪዳናቸውን ተቀብለው ትንሽ ጊዜ ከቆዩ በኃላ ወደ
በኬ ምድር ለቡራኬ ወጡ መላአክ ጊዜ እረፍታቸው እንደቀረቀበ ነገራቸው ያን
ጊዜ ደስ ብሏቸው ወደ ገዳማቸው ሲመለሱ የመጀመሪያይቱ የእሳት ጥላሻት
ተሰማያቸው ጎዳና በር እናላቲ የሚባሉ አቀበትና ቁልቁለት አሉ በነዚህ መንገዶች
ለመጓዝ በጣም ደከሙና አየተደገፋ ዘለቁ፡፡
☞ከበሩ ሲደርሱ አሳረፏቸው ከዚያ በኃላ አንደበታቸው በረታ ልሳናቸው ፈታ
ማኅበረ መነኮሳቱን አዕናኑ ቃል ኪዳናቸው አበረከቱ፡፡
☞በገዳሙ ውስጥ የምንኩስና ክብር የተቀበለ ከቤተክርስቲያኑ ስጋ ወደሙ
የተቀበለ እጣን ጧፍ ማንኛውም በጎ አድራጎት ለቤተ መቅደሱ የተራዳ
በተለይም ይህችን ቦታ የረገጠ ገድልህን የሰማ ያሰማ የጻፈ ያፃፈ እሰከ አስራ
አምስት ተውልድ እምርልሃለሁ ብሎ የሰጣቸውን ተስፋ ተናግረው ወደ ገዳሙ
ሴት እንዳያልፍ በለው ካሰናበቱ በኃላ ጌታችን መላእክት አስከትሎ የብፁአ
አባታችን ነፍስ ለማሳረግ ሲወርድ ታላቅ ግርማ ሆነ፡፡
☞ከበሩ አንዲት ወይራ ነበረች ወይራይቱም ለፈጣሪዋ ሰገደች፡፡ እሰከአሁን
ደርቃ ተጋድማ የወንድና የሴት መለያ ሁና ትታያለች በዚያ ግርማ መላእክት
በማህሌት መስከረም 5ቀን ነፍሳቸውን ከስጋቸው ለይተው አሳረጓት ፡፡
☞ስለዚህ መስከረም አምስት የእረፍታቸው ቀናቸው ነው በረከታቸው ከሁላችን
ጋር ይሁን፡፡
☞የጻድቁ ታላላቅ ገድላት
☞እንደነ ሙሴና አሮን በአምደ ደመና ከመሬት መሰወር፡፡
☞እንደ ዳንኤል አናብስት ማሰገድ
☞እንደ ሙሴ ከድንጋይ ላይ ውሃ ማፍለቅ
☞እንደ ኤልሳ ባህርን ሁለት ጊዜ መሻገር፡፡
☞እንደ እያሱ ፀሐይ ማቆም
☞እንደ ሐዋርያት ድውይ መፈወስ፡፡ ከቡዙ በጥቂቱ ነው፡፡
☞ባህሩን የከፈሉበት ውሃ ያፈለቁበት ፀሐይ ያቆሙበት ዳዊታቸውን ያወጡበት
በትረ መስቀላቸው ልዩና በቁመቱ በአራት ማዕዘን የተቀረፀ ሲሆን እስካሁን
በገዳሙ ያለና ብዙ በሽተኞችን በመፈወስ ላይ ይገኛል፡፡
☞ህንፃውን ያነፁበትና ጉድብ የተባለው መጥረቢያ ቅዱስ ኡራኤል የሰጣቸው
ሶስት መልክ ያለው ይህም እየታጠበ ብዙ ድውያንን በመፈወስ ላይ ይገኛል፡፡
☞የጻድቁ አባታችን የአቡነ አሮን ምልጃቸው ከሁላችን ጋር ይሁን፡፡
☞(መዝገበ ቅዱሳንእና ገድለ አቡነ አሮን)
☞ሲራክ ተክላጻዲቅ የተዋህዶ ልጅ

በዚህ ጆይን እያላችሁ አንብቡ እናንብብ ከቅዱሳን በረከት ይክፈለንhttps://t.me/Orthodoxtewahdoc
728 views "ወለተ ሥላሴ" "አነ ዘክርስቶስ" , 12:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-12 15:59:07 እንኳን አደረሳችሁ
††† እንኳን ለነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ኤርምያስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †††

††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††

††† ቅዱስ ኤርምያስ †††

††† ታላቁ ነቢይ ቅዱስ ኤርምያስ ከዐበይት ነቢያት አንዱ ሲሆን ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በስድስት መቶ አካባቢ የነበረ ነቢይ ነው:: አባቱ ኬልቅዩ ይባላል:: ከካህናተ እስራኤል አንዱ ነበር::

እግዚአብሔር ኤርምያስን የጠራው ገና በሕፃንነቱ ነበር:: "ከእናትህ ማኅጸን ሳትወጣ መርጬሃለሁ: ቀድሼሃለሁ" ሲልም በገሃድ መስክሮለታል:: (ኤር. 1:5)

ከቅዱሳን ነቢያት እንደ ኤርምያስ የተሰቃየና ያለቀሰ የለም:: ከሰባ ዘመናት በላይ ስለ ወገኖቹ አልቅሷልና ሊቃውንት "ነቢየ ብካይ" (ባለ እንባው ነቢይ) ይሉታል::

ዘመኑ ዘመነ-ኃጢአት (ዘመነ ዐጸባ) ነበር:: እሥራኤላውያን ከመሪዎቻቸው ከነ ሴዴቅያስ ጋር በክፋት ተባብረውም ነበርና ኤርምያስን አልሰሙትም:: ይልቁኑ ክፉ ቦታ ውስጥ አስረው አሰቃዩት:: እግዚአብሔር ግን በኢትዮጵያዊው አቤሜሌክ አማካኝነት ከመከራው አዳነው::

የተሰበከላቸውን የንስሐ ጥሪ አልሰሙምና ስልምናሦር የሚባል የአሕዛብ ንጉሥ መጥቶ አሥሩን ነገድ ማርኮ በ722 አሦር (ነነዌ) አወረዳቸው:: በኋላ ደግሞ በኃይለኝነቱ የታወቀው የባቢሎን ንጉሥ ይማርካቸው ዘንድ ወደ ሁለቱ ነገድ ኢየሩሳሌም ደረሰ:: ኤርምያስ ወደ ከተማዋ ዳር ወጥቶ ስለ ኢየሩሳሌምና ስለ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ አለቀሰ::

ከቤተ መቅደስ ንዋያት እኩሉን ለምድር አደራ ሰጣትና ሸሸገችው:: ነቢዩ የተናገረው አይቀርምና ንጉሡ ናቡከደነጾር እኩሉን ገድሎ: እኩሉንም ማርኮ: ኢየሩሳሌምን አቃጥሎ: የአሕዛብ መዘባበቻ አድርጐ በ586 ባቢሎን አወረዳቸው::

ቅዱስ ኤርምያስን ግን ትሩፋን (ከመከራው የተረፉት) ይዘውት ወደ ግብጽ ወረዱ እንጂ አልተማረከም::
በዚያም ተአምራትን አድርጐ አራዊትን አጥፍቷቸዋል:: ትንሽ ቆይቶ ግን እውነተኛ አባት : ነቢይ : መምሕርም ነውና ወደ ሕዝቡ (ወደ ባቢሎን) ወረደ:: በዚያም ትንቢትን እየተናገረ : ሕዝቡን ከሰባ ዓመታት በኋላ ወደ ሐገራቸው እንደሚመለሱ እያስተማራቸው በባቢሎን ቆይቷል:: ያለ በደሉም በመከራቸው ተካፋይ ሆኗል::

ሰባው ዘመን ሲፈጸም እግዚአብሔር እንደ ቃል ኪዳኑ በኤርምያስ መሪነት እሥራኤል ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ:: አሁንም ግን ክፋታቸውን ይተው ዘንድ ፈቃደኞች አልነበሩምና ኤርምያስ ገሠጻቸው::

በዚህ ተበሳጭተው ሊወግሩት ሲሉ ጸጋ በዝቶለት : ምሥጢርም ሰፍቶለት ስለ ነገረ ሥጋዌ (ስለ ክርስቶስ የማዳን ሥራ) አምልቶና አጉልቶ ትንቢት ተናገረ:: አንዴ ልቡናቸው ታውሮ ኤርምያስ ነው ብለው ድንጋዩን በድንጋይ ሲወግሩት ውለዋል:: ዘግይቶ ግን ኤርምያስ ራሱን ገለጠላቸው:: ስለ እነርሱ ሲል ሰባ ዘመን ያለቀሰውንና ምትክ የሌለውን አባታቸውን ወግረው ገደሉት::

ታላቁ ነቢይ ቅዱስ ኤርምያስ ሃምሳ ሁለት ምዕራፎች ያሉት ሐረገ ትንቢት ተናግሯል / ጽፏል:: ዜና ሕይወቱ ከራሱ የትንቢት መጽሐፍ በተጨማሪ በተረፈ ኤርምያስ : በመጽሐፈ ባሮክ : በገድለ ኤርምያስ : በዜና ብጹዐን : በመጽሐፈ ስንክሳርም ተጽፏል::

††† ቸር እግዚአብሔር በኤርምያስ ምልጃ ሃገራችንን ከጥፋት: ሕዝቦቿን ከስደትና ከመቅሰፍት ይሰውርልን::

††† ግንቦት 5 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ኤርምያስ ነቢይ (ከታላላቆቹ ነቢያት አንዱ)

††† ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ ጴጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት
2.ቅዱስ ጳውሎስ ሐዋርያ
3.አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ
4.ቅዱስ ዮሐኒ ኢትዮጵያዊ
5.ቅዱስ አሞኒ ዘናሒሶ

††† "ኢየሩሳሌም ሆይ ነቢያትን የምትገድል : ወደ እርሷ የተላኩትንም የምትወግር : ዶሮ ጫጩቶቿን ከክንፎቿ በታች እንደምትሰበስብ ልጆችሽን እሰበስብ ዘንድ ስንት ጊዜ ወደድሁ! አልወደዳችሁምም:: እነሆ ቤታችሁ የተፈታ ሆኖ ይቀርላቹሃል:: እላችሁአለሁና : በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው እስክትሉ ድረስ እንግዲህ ወዲህ አታዩኝም::"
(ማቴ. ፳፫፥፴፯-፴፱)

††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††

https://t.me/zikirekdusn
"መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ::" /ማቴ ፫:፫/
ዝክረ ቅዱሳንን ተማሩ ብለን እንለምናችኋለን!!

ዝክረቅዱሳን (ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት)

" ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::
አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/
https://t.me/zikirekdusn
815 views "ወለተ ሥላሴ" "አነ ዘክርስቶስ" , 12:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-12 14:53:52 ስማኝ ልጄ

1.ጠንካራ ሰው ሁን ማለት አትውደቅ ማለት አይደለም ወድቀህ መነሳትንም ልመድ ማለት እንጂ!!!!
2. ዝም በል ማለት አትናገር ማለት አይደለም ሌሎችን ለመስማት ጆሮ ስጥ ማለት እንጂ!!!!

3. ሆዳም አትሁን ማለት አትብላ ማለት አይደለም በሰው ሀቅ አትለፍ ማለት እንጂ!!!!

4. አትቆጣ ማለት ስሜት አይኑርህ ማለት አይደለም ከቁጣ ቶሎ ተመለስ ማለት እንጂ!!!!

5. ይቅርታ አድርግ ማለት አልተጎዳህም ማለት አይደለም በሆድህ ቂም መያዝ ሌላ ጉዳት ስለሆነ እንጂ!!!!

6. ጠላትህን ውደድ ማለት ጠላት ጥሩ ነው ማለት አይደለም ከጥላቻ ይልቅ ፍቅር ስለሚያሸንፍ!!!

7. ደስተኛ ሁን ማለት ሁሉ ይኑርህ ማለት አይደለም ባለህ ነገር ደስ ይበልህ ማለት እንጂ!!!!

8. ስራህን ውደድ ማለት የምትሰራው ስራ ጥሩ ነው ማለት አይደለም ነገ ጥሩ ስራ እንዲኖርህ ዛሬ የምትሰራውን ስራ ውደድ ማለት እንጂ!!!!

9. ወረኛ አትሁን ማለት አታውራ ማለት አይደለም ምንም ስለማታውቀው ነገር አታውራ ማለት እንጂ!!!!

10. ትሞታለህ ማለት አትስራ ማለት አይደለም ምንም ቁም ነገር ስትሰራ አትሙት ማለት እንጂ!!!!

11. ብቸኛ አትሁን ማለት ሮጠህ ትዳር ያዝ ማለት አይደለም ልብህን ግዜህን ያለህን ሁሉ አሳልፈ ለመስጠት ዝግጁ ሁን ማለት እንጂ!!!!

12. እውነተኛ ሁን ማለት ሰዎች ባሉበት ብቻ እውነትተናገር ማለት አይደለም ለራስህም የእውነት ኑሮ ኑር ማለት ማለት እንጂ!!!!

13. አትጣላ ማለት ከሰው ጋር አትኑር ማለት አይደለም ቂም ይዘህ አትቆይ ማለት እንጂ!!!!

14. ኩራተኛ አትሁን ማለት አትዘንጥ ማለት አይደለም ሌሎችን አትናቅ ማለት እንጂ!!!

15. ቆንጆ ነህ ማለት ከሌሎች የተሻልክህ ነህ ማለት አይደለም አምሮብሃል ማለት እንጂ!!!!

16. አዋቂ ሁን ማለት እንደገና ት/ቤት ሂድ ማለት አይደለም ብልህ ሁን ማለት እንጂ!!!!

ማስተዋሉንያድለን አሜን።
1.3K views "ወለተ ሥላሴ" "አነ ዘክርስቶስ" , 11:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-12 12:51:49 በዚህ ቀን እደሰታለሁ ብለህ ፕሮግራም አታዉጣ እያንዳንዷ ቀን ስጦታህ ናት ተደሰትባት በጤና መኖርህ በራሱ ትልቅ ደስታ ነዉ !!
1.4K views "ወለተ ሥላሴ" "አነ ዘክርስቶስ" , 09:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-12 01:10:38 ☞አርብ የፍቅር ቀን

☞በዕለተ ዐርብ የሚፀለይ ጸሎት

☞ንስሓ የገባ ኃጢአተኛ ሰው እንኳን ቢሆን ይህችን የአቡነ እስትንፋ ክርስቶስ
ጸሎት በጸለየ ጊዜ ሺህ ነፍሳትን ከሲኦል እንደሚያወጣ ጌታችን በማይታበል ቃሉ
ለአባታችን ነግራቸዋል፡፡ ይቺ ፀሎት በአምላክ ልቡና ያለች ጸሎት ነፍሳትን
ከሲኦል አታወጣም ብሎ የሚጠራጠር ቢኖር መንግሰተ ሰማያት አያያትም
የተባለላት የተመረጠች ጸሎት እንሆ በዐለተ ዐርብ ፀልየን በረከት እንጋኝ፡፡
☞ጸሎትና ልመና ወደ እግዚአብሔር ምልጃ ለነፍስና ለሥጋ የሚጠቅም ነው፡፡
በሕይወተ ሥጋ ያሉ ሰዎች ይህንን ጸሎት በሚጸልዩበት ጊዜ አባቶቻቸውን
እናቶቻቸው ዘመዶቻቸውንና ወዳጆቻቸውን በአንዲት ጊዜ ከሲኦል ያወጡበታል፡፡
የሾህ አክሊል ጎንጉነው ያቀዳጁሽ የጌታችን የመድሀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ
ራስ ሆይ ለአንቺ ሠላምታ ይገባሻል፡፡ሥጋችን ለማንጻትና ነፍሳችንን ለመቀደስ
አስከመመታት ደረሰሽ ንጽህ ደምን አፈሰሰሽ፡፡እገሌና ኤገሌን ማርልኝ እያለ ስም
ይጥራ(አባታችን ሆይ በል)
☞ሰይጣን የተፋውን የኃጢአት ምራቅ ከእኛ ለማስወገደ ስለ እኛ አይሁድ ርኩስ
ምራቃቸውን የተፋብሽ የዓለም ቤዛ የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የከበርሽ
ፊት ሆይ ሠላምታ ላንቺ ይገባሻል፡፡ ዛሬ የእኔን ኃጢአት አሰወግጅ፡፡(አባታችን ሆይ
በል)
☞አላዋቂ በሆኑ በሰቃልያን አይሁዱ እጅ በጥፊ የተመታችሁ የዓለም ቤዛ
የመድኃኒታችን የኢየሱስ ጉንጮች ሆይ ለእናተ ሰላምታ ይገባችኀል በእናተ
ምክንያት የተዘጋ ገነት ተከፈተ እንዲሁ የልቦና በር ፈጽሞ ይከፈትልኝ፡፡(አባታችን
ሆይ በል)
☞የነፍሳችን የሥጋችን መድኃኒት ትሰጭን ዘንድ የመረረ ሐሞትና ከርቤን
ትጠጪ ዘንድ የወደድሽ የዓለም ቤዛ የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የከበርሽ
አፍ ሆይ ለአንቺ ሰላምታ ይገባሻል፡፡ እንደዚሁ ለእኔ የሕይወት መጠጥ አጠጪኝ
፡፡ (አባታችን ሆይ በል)
☞ሰለ እኛ በአደባባይ የሞት መስቀል የተሸከምሽ የዓለም ቤዛ የመድኃኒታችን
የኢየሱስ ክርስቶስ የከበርሽ ከፍ ከፍ ያልሽ ክንድ ሆይ ለአንቺ ሰላምታ ይገባሻል
ሁላችን የእጅ ፍጥረቶች ነንና የኃጢአታችንን ሸክም ተሸክሚል የበደላችንን ሸክም
አቅይልን፡፡(አባታችን ሆይ በል)
☞ሰለ እኛ ሰለፍጥረቶችሽ የመስቀል ግንድ የተላካብሽ የዓለም ቤዛ
የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልዮ የሆንሽ ጀረባ ሆይ ለአንቺ ሰላምታ
ይገባሻል ዛሬም የኃጢአታችንን ግንድ ላኪልን፡፡ (አባታችን ሆይ በል)
☞የተረገሙ አይሁድ በችንካር ይቸነክሩሽ ዘንድ የወደድሽ የመድሀኃኒታችን
የኢየሱስ ክረርስቶሰ ቀኝ እጅ ሆይ ለአንቺ ሰላምታ ይገባሻል፡፡እንደዚሁ
በስንፍናችን የሠራነው በደላችንን አጥፊልን፡፡ (አባታችን ሆይ ይበል)
☞አስቀድመሽ ሰለበደላችን ከሐዲያን አይሁድ ይቸነክሩሽ ዘንድ የወደድሽ
ያለመለወጥ ፍፁም እግዚአብሔር ፍፁም ሰው የሚሆን የመድኃኒታችን
የፈጣሪያችን የኢየሱስ ክርስቶስ የከበርሽ ግራ እጅ ሆይ ለአንቺ ሠላምታ
ይገባሻል፡፡ እንደዚሁ የእኛን በደል ችንክሪ የሞት ችንካር ከሚሆን ከዲያብሎስ
አድኝን፡፡(አባታችን ሆይ በል)
☞ሰለ ኃጢአታችን ክፋዎች አይሁድ ይቸነክሩሽ ዘንድ ፈጽመው ያስሩሽ
የፈጣሪያችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የከበርሽ ቀኝ እግር ሆይ ለአንቺ
ሰላምታ ይገባሻል እንደዚሁ ኃጢአታችንን አስተሰርይልን፡፡(አባታችን ሆይ በል)
☞በእውነት የታመነ እውነተኛ ቅን ንጉሥ የሚሆን የዓለም ቤዛ የመድኃኒታችን
የኢየሱስ ክርስቶስ የከበርሽ ግራ እግር ሆይ ለአንቺ ሰላምታ ይገባሻል ያለ በደል
በቅዱስ መስቀል ላይ የተቸነከርሽ እንደዚሁ ኃጢአታችንን ቸንክሪልን፡፡
የበደላችንን መጽሐፍ ደምስሽልን፡፡(አባታችን ሆይ በል)
☞ኃጢአታችንን የምንታጠብበትና የምናስተሠርይበት ውኃ ደምን(ከጎንሽ
እሰከምታፈሽ ድረስ)በመስቀል ላይ ሳለሽ ጎንሽ የተወጋሽ የጌታችን የአምላካችን
የኢየሱስ ክርስቶስ ልዩ እና የከበርሽ ጎን ሆይ ለአንቺ ሰላምታ ይገባሻል ተዘግቶ
የነበረው የሰማይ ምሥጢር በአንቺ ምክንያት ተገለጠ ተከፈተ እንደዚሁም ሁሉ
የልባችንን በር ይከፈትልን፡፡(አባታችን ሆይ ይበል)
☞በመስቀል ላይ መከራን ለተቀበሉ ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ
ክርስቶስ አካላት ሁሉ ሰላምታ ይገባቸዋል የጌቶች ጌታ የንጉሦች ንጉስ ጌታዬ
ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ለአንተ ክብር ምስጋና ይገባሃል በታላላቅ ችንንከሩህ ዘንድ
ለእኛ ስትል የወደድክ ዛሬም በፍቅር ትቸነክረን ዘንድ እለምንሃለን ከእኛ ጋር
መከራን ሰለተቀበልክ እኛም ከአንተ ጋር መከራን እንቀበላለን በመስቀል ላይ
የተቀበልከውን የመከራህ ተሣታፊዎች አድርገኸናልና በመከራ ሰለመስልንስ
እንዲዚሁ በጌትነትህ በምትመጣበት ጊዜ በዕለተ ምጽዐአት ከአገልጋዮችህ
ከቅዱሳን ጋር ክብርን አድለን፡፡[(አባታችን ሆይ በል
☞ታዖስ ወዖ አልፋ ቤጣ የምትባል ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ የባሕርይ
አባትህ አብ መጠጊያ ኃይል ይሁነን እግዚአብሔር ዕድል ፈንታቸው ጽዋ ተርታችን
ነው እንደ ቸርነትህ ጎዳናችንን አሰተካክልን አንተ ለወደድከው መራራውን ከማር
ይልቅ ጣፋጭ ይሆናል፡፡ እኛም ይህንን እንወዳለን እግዚአብሔረ ሆይ አንተ
መውደድን ሰጠን ፈጣሪያችን አሰመልክተን አሰተዋይ ልቡና ሰጠን ፈጣሪያችን
ጥበበኛ አድርገን፤ ፈጣሪያችን አድነን፤ በውስጥና በውጭ ያለውን የሚታየውንና
የማይታየውን አበሳ የምታውቅ አቤቱ እግዚአብሔር ሆይ አውግዮን፤አውሎግሶን
ልቦናችንን አና ሰማያዊውን ቤት ክፈትልን ዓይነ ልቡናችንንምአብራልን
ኃጢአታችንንም ይቅር በለን፡፡(አባታችን ሆይ በል)
☞መሐሪ የሆንክ አምላክ ሆይ ይቅር ባይ አምላክ ሆይ ቸር አምላክ ሆይ የእኛን
የበደለኞቹን ኃጢአት ይቅር በል፡፡ (አባታችን ሆይ በል)
☞ዓለም ሳይፈጠር አሰቀድመህ የነበርክ ዛሬም ያለህ ዓለምን አሳልፈህ
የምትኖር የወልድ የመንፈስ ቅዱስ ልባቸው አብ ሆይ ለአንተ ሰላምታ ይገባሐል
ዓለም ሳይፈጠር አስቀድመህ የነበርክ ዛሬም ያለህ ዓለምን አሳልፈህ የምትኖር
የአብ የመንፈስ ቅዱስ ቃላቸው ወልድ ሆይ ለአንተ ሰላምታ ይገባሃል፡፡(ሦስት
ጊዜበል) አቤቱ ፈጣሪያችን ሥጋችንንና ነፍሣችንን ባርክ አቤቱ ፈጣሪያችን
ሕይወታችንና ሞታችንን ባርክ አቤቱ ፈጣሪያችን ጸሎት ልመናችንን ባርክ፡፡
( አባታችን ሆይ በል፡፡
☞ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ የሚያስጨንቅ ለአንተ ቀላል ነው የራቀ ለአንተ
ቅርብ ነው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ይቅርታህ ከእኛ አታዘግይብን
(አታርቅብን የሚያደንቁህ ከፍ አድርጋቸው ለአንተ ቀላል ነውና ኃጢአታችንን
አስተስርይልን አንተ መከራ በደላችንን ይቅር በለን፡፡(አባታችን ሆይ በል)
☞እግዚአብሔር ፈጣሪያችን ሆይ በሦስትነትህ ተማፀነህ በትክክል ሥልጣን
ተማፀንህ በአንድነትህ ተማፀነህ በመለኮትህ ተማፀነህ አንተን በወለችህ
በድንግል ማርያም እናትህ ተማፀነህ በቅዱስ መስቀልህ ተማወነህ
በምትወደው በወዳጅህ በቅዱስ ዮሐንስ ተማፀነህ አንተን ባጠመቀህ በቅዱስ
ዮሐንስ መጥምቅ ተማፀንህ መልአከ ምክርህ በሆነ በቅዱስ ሚካኤል ተማፀነህ
የአንተን መወለድ ለድንግል ማርያም የደስታ ብሥራትን በነገራት በቅዱስ
ገብርኤል ተማፀነህ እኛም ኃጠአተኛ ባሮችሁ በወዳጅህ በእስትንፋሰ ክርስቶስ
ተማፀነህ የእኛንም የሕዝብ ኃጢአት ይቅር በል አሜን፡፡(አባታችን ሆይ በል)
☞ይቺ በአምላክ ልቡና ያለች ግሩም ጸሎት ነፍሳትን ከሲኦል አታወጣም ብሎ
የሚጠራጠር ቢኖር መንግስተ ሰማያትን አያያትም፡፡ብሎ ጌታችን ለአባታችን
ለአብነ እስትንፋሰ ክርስቶስ ቃል ኪዳን ገብቶላቸዋል፡፡
☞(ገድለ አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ)
☞ሲራክ ተክላጻዲቅ የተዋህዶ ልጅ
☞19-12-2014
1.7K views "ወለተ ሥላሴ" "አነ ዘክርስቶስ" , 22:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ