2023-05-10 14:37:02
#በዓታ ለማርያም ማለት
✞ #እመቤታችን የብጸሐት ልጅ ናት ( የስለት ልጅ) 3 ዓመት ሲሆናት አፍዋ እህል ሳይለምድ ሆድዋ ስው ሳይውድ ብለው እናት አባትዋ ውስደው ለቤተ እግዚአብሔር ስጡዋት ሊቀ ካህናቱ ዘካርያስ ይባላል ✞ የእመቤታችን መልኳ እንደ ፅሀይ ሲያበራ አይቶ ይእችን የመስለች ውብ ብላቴና ተረክቤ እንደምን አድርጌ አኖራታለው ብሉ ደውል አስምቶ ካህናትን ስብስቦ የምግቧን ነግር ሲማከሩ መልአኩ ቅዱስ ፋኖኤል ዕብስት ስማያዊ ጸዋ ስማያዊ ይዞ ከላይ እርቦ ታየ
ሊቀ ካህናቱ ዛሬ ሀብቴን ክብሬን በስው መካከል
ሊገልጥልኝ መስለኝ ብሎ ሊቀበል ቀርበ መልአኩ ወደ ላይ ስቀቀበት
+ ካህናቱም ሊቀበሉ ቀርቡ መልአኩ ወደ ላይ ስቀቀባቸው
+ እህሩገ እስራኤልም ቀርቡ መልአኩ ወደ ላይ ስቀቀባቸው
+ ሐና እያቄምም ሊቀበሉ ቀርቡመልአኩ ወደ ላይ ስቀቀባቸው
ሐና ምን አልባት ለዚህች ብላቴና የውርደ መንፈስ ቅዱስ ሳይሆን አይቀርምና እስኪ ትተሻት ጥቂት እልፍ በይ አሏት ትታት ትንሽ እልፍ ብትል መልአኩ ውርዶ ግራክንፉን አንጥፋ ቀኝ ክንፈን አጉናጸፏ በቆመ ብዕሲ አድርጉ መግቧት አርጓል
"ምግቧ ሰማያዊ ነው ሲል ነው "
የምግቧ ነግር ከተያዘልን ይህችን ውብ ብላቴ ከስው ጋራ ምን ያጋፈታል ኖሮዋ ከቤተ መቅደስ ይሁን ብለው ከቤተመቅደስ አግብተው አኖርዋት ሄደዋል
እመቤታችንም መላእክት ሊቃነ መላዕክት አያጫውትዋት እያርጋጓት 12ዓመት በቤተ መቅደስ ተቀምጠች ከእናት አባትዋቤት 3ዓመት በአጠቃላይ 15ዓመት ሲሆናት
አይሁዶች መቼም ለምቀኝነት አያርፉምና ይእች ብላቴና ለአቅመ ሔዋን ደርሳለች እሷን ያለ ጉልማሳ በቤተ መቅደሳችን አስገብተን ቤተ መቅደስሳችንን ታርክስብናለች እንዲያውም ጠረጠረናት ትውጣልን የጠየቀችሁን አድርግላት አሉት
ሊቀ ካህናቱም ዘካርያስ ከእመቤታችን ሄዶ ልጄ እንደምን ብለሽ መኖር ትውጃለሽ አላት
እመቤታችንም ፍፃምተ ፈቃድ ፤ ትሁት ናትና እንግዲህ ከእግዚአብሔር በታች ያለከኝ አባት አንተ ነህ ውደ እግዚአብሔር አመልክትልኝ አለችሁ
ወደ እግዚአብሔር ቢያመለክት ጌታ ስራውን ያለ ምክንያት አይስራውምና ከነገደ ይሁዳ ሚስቱ የሞተችበትን በትር ስብስበ በቀዳማይ ሰዓታት ሌሊት ይዘህ ገብተ ስትፀልይበት እደር ከዚያ ምልክት አሳይካለው ለዕዚያ ስው ስጣት አለው
ሊቀ ካህናቱም በትር ቢስበስብ 9መቶ 1985 በትር ሆነ ያንን በቀዳማይ ስዓት ሌሊት ይዙ ገብቶ ሲጸልይበት ቢያድር
+ በዮሴፍ በትር ላይ የሎሚ ቅጠል አብባ አፍርታ ታየች
+ እርግብም በዮሴፍ እራስ ላይ አርፈለች
+ እጣም ቢጥሉ ለዮሴፍ ደርስው በሦስት ምስክር ለዮሴፍ ደርስች
ሱባዬ ገብተን የስጠንክን ሱባዬ ገብተን እስክንቀበልክ ድርስ ጠብቃት ተንከባከባት አሉት የዮሴፍም ይዟት ውደ ቤቱ ሄደ።
ከቤቱ አኑሯት ዘመኑ የንግድ ውቅት ነበርና ወደ ንግድ ለመሄድ ዕለቱን ተሸኝቶ አድሯል ዮሴፍ ከ3ወር በሀላ ተመለስ ዮሐንስ የሚባል ፍላስፍ ወዳጅ ነበርው ሊጠይቀው መጣ ጥቂት ተጨዋወተው ሊሄድ ተነሳ ሊሽኘው ውጣ
ዮሴፍ ይህች ብላቴና ፀንሳለች ከአንተ ነው ወይስ ከሌላ አለው በምን አውቀው ቢሉ በፈልስፈና የጌታስ ፀንስ በፈልስፈና አይታውቅም ብሎ
ሴቶች ሲፀንሱ ከቀደመው ይልቅ መልካቸው ያምራል ጡታቸው ይጦቅራል ከንፈራቸው ይደርቃል በዚያ አውቆ።
ዮሴፍም አር እኔ እንኳን ግቢር ቀርቶ ሐልኦም አልውቅባትም አለው እንግዲያውስ ስስነች ተብላ እንዳትውገርብህ ገብተህ ጠይቀ ተረዳ አለው።
ዮሴፍም ውደ ቤት ተመልሶ ድንግል ማርያምን
የፀነሽው ከማን ነው ብሎ ጠየቃት
ድንግልም ከመንፈስ ቅዱስ ነው አለችሁ ከዚህ በፈት እንዲህ ተደርጉ አያውቅም እና ነገሩ እርቀቀበት ቢርቀው ከደጅ ወድቆ ይኖር የነበር ደርቅ ግንድ አለ ይሀንን አለምልማ አብባ አፈርታ አሳይታዋለች
በዚያውስ ላይ ዐፁቅ በባህሪያቸው እንዲያብቡ ንቦችን እንዲራቡ የሚያደርግ ጌታ እኔንስ በእቱም ድንግልና ፀንሼ በህቱም ድንግልና እንድውልድ ቢያደርገኝ ይሳነዋል ትላለክ???
ብላ ነገሩን እንደዚህ አስርድታዋለች
ይህም አልቀርም ውድያው ለባህል የሚውጡበት ጊዜ ደርስ የሴፍም ትቺያት ብሄድ ያደርገውን አውቆ ትቷት መጣ ይሎኛል
ይዥትም ብሄድ ሴስነች ብለው በድንጋይ ወግርወ በእሳት አቃጥለው ይገድሉብኛል ምን ይሻለኛል እያለ ይህን ሲያውጣ ሲያውርድ መላከ እግዚአብሔር በህልም ታየው ተነጋገርው
ዮሴፍ ከእርሷ የሚወለደው የአብ አካለዊ ቃል በግብር መንፈስ ቅዱስ ነውና አይዞህ አትፈሪ ይዘሀት ውጣ አለው ይዝዋት ውጥቷል ነገሩም አልቀርም
" ማየ ዘለፈአጠጧት " ይህ በኦሪቱ ልማድ ነው ባልየው መንፍሳዊ ቅናት ተነሳስቶ ከሌላ ውንድ ደርሳለች ብሎ ሚስቱን የጠርጠራት እንደሆነ
" አሪፀ ስግምን ውሃ በገንቦ አሲዞ እራሷን አከናንቦ ወደ ቤተ መቅደስ ይዟት ይሄዳል ሊቀ ካህናቱ ከምህዋሩ ለይ ሆኖ ክንብንብሽን ግለጭው ይላታ እንዲህ ይግለጥብኝ በይ ሲያስኛት ነው
ከኦሪቱ የሚደገም የሚነበብ የሚጸለይ አንዳንድ አለ
ሊቀ ካህናቱ ያንን ደግሞ ህራር እጣኑን አመደ ምስዋቶን በጥብጦ ባልሽ የጠርጠርሽን አድርገሽ ስውርሽ እንደሆነ
ስውነትሽ ይበጥ ፣ ጉንሽ ይላጥ ፣ አጥንትሽ ይርገፍ
አላደርግሽው እንደሆነ
በውንድ ልጅ ይታርቅሽ ብሎ ይስጣታል
እርሷም አሜን ውአሜን ብላ ተቀብላ ትጠጣዋለች ።
እርግማኑ ይደርግብኝ ምርቃኑ ይደርግልኝ ስትል ነው ባልዋ የጠርጠራትን አድርጋ ስውራ እንደሆነ ውድያው ስውነቷ ያብጣል ፣ጉንዋ ይላጣል ፣አጥንቷም ይርግፈል
ያላደርገችው እንደሆነ በውንድ ልጅ ይታርቃታል
በዚያ ልማድ ነው
ለእመቤታችንም ቢያጠጥዋት ፈትዋ ከፀሐይ ስባት እጅ አብርቶ ተገኘ ታየ ከዚያ የተስበስ ህዝቡ ይህችን ብላቴ ባላደርገችው ነገር በከንቱ አምተናታል ብለው
የተናገሩት ለእርሷ ስጥቶ ውይትፀርይ ብሉ ተናገር።
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በቤተ መቅደስ ሳለች እንዲህ ብላ ተናገርች መላኩ ቅዱስ ገብርኤል ከነገርኝ ነገር ቃል በቀር ሌላ እንደማላውቅ እግዚአብሔር ያውቃል ብላ ተናገርች ።
✞ ንፅህት ድንግል ማርያም አምላክን ለመውለድ የታመነች ናት
✞ አምላክን ለመውለድ የታመነች ድንግል ማርያም ብቻ ናት
✞ የስውን ልጅ ለማማለድ ድንግል ማርያም የታመነች ናት
ድንግል ሆይ !!! የማይውስነውን ውስንሽ
የማይቻለውንን ቻልሽ ምንም ምንም ሊችለው የሌለውን ቻልሽ
ምልዕተ ፀጋ ምልዕተ ክብር እመቤታችን የአብ አካላዊ ቃል ማደሪያው ድንግል እመቤታችን
የማህፀኗ ፈሬ ኢየሱስ ክርስቶስ ዓለሙን ሁሉ አዳነ
ከእኛ መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስን አጠፈ
እመቤቴ ማርያም ሆይ
ዘር ያልወደቀባት ገበሬ ያልጣረባት የቅዱስ ቁርባንን አዝመራ ያፈራሽ ገራህት ሆይ፤ ከትጉሃን መላእክት ጋር ወደኔ ፈጥነሽ ነይ፡፡
ድንግል እመቤቴ ሆይ
ብልህ አዋቂ የሆነ ከልጅነቱ ጀምሮ አንቺን ያፈቅራል፤ ሰነፍ ልበ ቢስ ግን በከንቱ ይጠላሻል፤ ዳሩ ግን በመከረው የተንኮል ምክር ወጥመድ እሱ ራሱ ይጠመድ፡፡
እመቤታችን ድንግል ማርያም በበረከት እና በረድኤት ትጎብኘን ፤ ከልጅዋ ከወዳጅዋ ከመድኃኔዓለም ዘንድ ታማልደን ፤ አሜን!!!
ድንግል ሆይ ከልጅሽ ከውዳጅሽ ከኢየሱስ ከክርስቶስ ለምኝልን ከሀጥያታችንን ያስተስርይልን ዘንድ አሜን!!!
ወስብሓት ለእግዚአብሔርው
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክብር አሜን
1.9K views "ወለተ ሥላሴ" "አነ ዘክርስቶስ" , 11:37