Get Mystery Box with random crypto!

"ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒

የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodoxtewahdoc — "ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒
የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodoxtewahdoc — "ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒
የሰርጥ አድራሻ: @orthodoxtewahdoc
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 22.88K
የሰርጥ መግለጫ

🌹«ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን
/አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ።♥ https://t.me/Orthodoxtewahdoc

ሐምሌ 3 በ2014 ዓ°ም ተከፈተ።
📌እግዚአብሔር ቢፈቅድ የቅዱሳኑን ታሪክ እንመማርበታለን ብለን ከፈትነው ቅዱስ እግዚአብሔር ይፍቀድልን አሜን‼
❤የእመ ብርሃን ልጅ🤗

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2023-05-10 14:32:04 #ተአምረ አባ ሊባኖስ

☞•••ወር በገባ በ3 ታስበው የሚውሉት አባታችን አባ ሊባኖስ ያደረገው ተአምር፡፡☞ጸሎቱና በረከቱ ከሁላችን ከሕዝበ ክርስቲያን ጋር ይኑር ለዘአለዓለሙ አሜን፡፡☞ከንጉስ ጭፍራዎች የታመመ ትከሻውም ከጉልበቱ ጋር እስከሚገናኝ የጎበጠ አንድ ወታደር ነበር፡፡

☞ወደ አባታችን ወደ አባ ሊባኖስም ቦታ በፈረስ ጭነው አምጥተው አባታችን
አባ ሊባኖስ በመስቀል ባርኮ ባፈለቀው በሕይወት ውሃ አጠመቁትና በክብር
አባታችን በአባ ሊባኖስ መቃብር ውስጥ አስቀመጡት፡፡
☞ከዕለታት በአንድ ቀን ካህናቱ በማህሌት እያመሰገኑ ሳለ የዚያ በሽተኛ
አጥንቶቹ ሲንቋቁ ከቤተክርስቲያን እንጨት የተሰበረ መስሏቸው ወደ
ቤተክርሲቲያኑ ጠፈር ይመለክቱ ጀመር፡፡
☞ዳግመኛም ወደዚያ በሽተኛ ሮጠው ቢሄዱ ሁለተናዉ ተቃንቶ ድኖ አገኙት፡፡
ከተኛበትም አነሱትና እግሩና ወገቡ ፀንቶለት ተቃንቶ በእግሩ ሄደ፡፡
☞አንድ ካህንም ወንድሜ ሆይ እንደምን ሆነህ ዳንክ ብሎ ጠየቀው እሱም ተኝቼ
ሳለ አንድ ሰው በመነኩሴ ተመስሎ ወደ እኔ መጣና በመስቀል ምልክት በላዬ
ላይአማተበ አጥንቼ ሁሉ እየተንቋቁ ጮኹ ይኸው ዛሬ እንደምታየኝ ተቃንቼ ድኜ
አለሁ አለ፡፡
☞ያየና የሰማ ሁሉ እግዚአብሔር አመሰገኑ፡፡ለቅዱስ ለአባ ሊባኖስ ፈጽሞ
ተገዙለት፡፡
☞ያም በሽተኛ አባታችን አባ ሊባኖስ በፀሉቱ ከአፈለቀው ከፀበሉ ይዞ ወደ ንጉሱ
ወደ ሰይፈ አርዕድ ሄደ፡፡
☞በዚህ ምክንያት ንጉሱ ሰይፈ አርዕድ ወደደው ያን በሽተኛ ያየውም ሰው ሁሉ
አደነቀ፡፡
☞ያም በሽተኛ ብዙ ገንዘብ ሁሉ ለአባ ሊባኖስ ቤተክርስቲያን አወረሰ፡፡ስሙም
መጣዕ መሐሮ ተባለ፡፡
☞የአባታችን የአባ ሊባኖስ ጸሎት በረከታቸው ከሁላችን ከተዋህዶ ልጆች ጋር
ይሁን፡፡
☞ገድለ አቡነ ሊባኖስ
☞ሲራክ ተክለጻዲቅ የተዋህዶ ልጅ
☞2-7-2014
1.3K views "ወለተ ሥላሴ" "አነ ዘክርስቶስ" , 11:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-10 14:31:24 እንኳን አደረሳችሁ
✞✞✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ
አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞

❖ ግንቦት 3 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

+"+ ቅዱስ ያሶን ሐዋርያ +"+

+ባለንበት ዘመን አሳዛኝ ከሆኑ ነገሮች አንዱ የቅዱሳኑ
ስማቸው ከነሥራቸው መዘንጋቱ ነው:: ለቅድስት ቤተ
ክርስቲያን
ደማቸው እንዳልፈሰሰ: አጥንታቸውም እንዳልተከሰከሰ
ይሔው አስታዋሽ አጥተው ስማቸውም ተዘንግቶ ይኖራል::

+አንዳንድ ንፉቃን ደግሞ ከዚሁ ብሶ ጭራሹኑ ኦርቶዶክስ
ተዋሕዶ ስለ ክርስቶስ ትታ ስለ ቅዱሳኑ ብቻ ትሰብካለች
ይሉናል::

+በእጅጉ ከሚያሳዝኑኝ ነገሮች አንዱ የቅዱሳን ሐዋርያት
(የ120ው ቤተሰብ) መዘንጋት ነው:: ከ120ው ቤተሰብ
የአብዛኞቹ
ስም በመዘንጋቱ: ሊቃውንቱም ዝምታን በመምረጣቸው
"ያሶን: አርስጦስ: አፍሮዲጡ: ቆሮስ . . . እያልን የ72ቱን
አርድእት ስም ስንጠራ ግር የሚለው ዓይነት ትውልድ
ተፈጥሯል::

+እስኪ እንዲያው ቢያንስ ሐዋርያትንና ዐበይት ቅዱሳንን
እናስባቸው:: አስበናቸው የሚጨመረልን እንጂ
የሚጨመርላቸው የለምና::

+ዛሬ የምናስበው ቅዱስ ያሶን ሐዋርያ ከ72ቱ አርድእት
አንዱ ነው:: ጌታችንን ከጥምቀቱ በኋላ ተከትሎ ለ3
ዓመታት
ከእግሩ ሥር ቁጭ ብሎ ተምሯል:: ከጌታችን ዕርገት በኋላ
መንፈስ ቅዱስን ተቀብሎ ለስብከተ ወንጌል ወጥቷል::

+ለብዙ ጊዜ ከቅዱስ ዻውሎስ ጋር ተመላልሶ ሰብኳል::
በመከራውም ተካፍሎታል:: ታላላቆቹ ሐዋርያት
ሰማዕትነትን ከተቀበሉ
በኋላ ለመጣው አዲስ ክርስቲያን ትውልድ ከጌታችን
ኢየሱስ ክርስቶስ ቃል በቃል የሰማውን አስተላልፏል::

+ወንጌልን ስለ ሰበከላቸው አሕዛብ ብዙ ጊዜ አስረው
ይደበድቡት: ያንገላቱት ነበር:: አንዳንድ ጊዜም እሳት
እያነደዱ
ያቃጥሉት ነበር:: ፈጣሪው ግን በተአምራት እያዳነው
ከርሱ ጋር አልተለየም::

+ከከተማ ወጥቶ በዱርና በእስር ቤቶች ብዙ ነፍሳትን:
ሽፍቶችንም ሳይቀር ወደ ክርስትና ማርኳል:: ቅዱስ ያሶን
ለረዥም
ዓመታት ሰብኮ በመልካም ሽምግልና አርፏል::

❖ ንግሥት ወለተ ማርያም ❖

+ዳግመኛ በዚህ ቀን ኢትዮዽያዊቷ እናታችን ቡርክት
ወለተ ማርያም ትታሰባለች::

+ወለተ ማርያም ማለት የደጉ አፄ ናኦድ ሚስት: የአፄ
ልብነ ድንግልና የቅድስት ሮማነ ወርቅ እናት ናት::
በንግስትነት
በቆየችባቸው ዘመናት (ከ1487-1500 ዓ/ም) የረሃብ
ጊዜ በመሆኑ ብዙ ሕዝብ አልቆ ነበር::

+ቡርክት ወለተ ማርያም ከጾምና ከጸሎት ባሻገር
የተራቡትን በማብላት ብዙዎችን ታድጋለች:: የንጉሡን
ቤተሰብ ወደ መልካም
ክርስትና በመምራትም የተመሰገነች ነበረች:: በዚህ ቀንም አርፋ ተቀብራለች::

❖አምላካችን ከቅዱሳኑ በረከት አይለየን::

❖ግንቦት 3 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ ያሶን ሐዋርያ (ከ72ቱ አርድእት አንዱ)
2.አባ ብሶይ ሰማዕት
3.ቅዱስ አውሳብዮስ ቀሲስ
4.ቡርክት ወለተ ማርያም ንግሥት (የዐፄ ልብነ ድንግል እናት)

❖ወርኃዊ በዓላት
1፡ በዓታ ለእግዝእትነ ማርያም
2፡ ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና
3፡ ካህናት ዘካርያስ ወስምዖን
4፡ አባ ሊባኖስ ዘመጣዕ
5፡ አባ ዜና ማርቆስ
6፡ አቡነ መድኃኒነ እግዚእ
7፡ ቅዱስ ቄርሎስ ዓምደ ሃይማኖት
8፡ ቅዱስ ስምዖን ዘዓምድ

++"+ ሰብዓውም በደስታ ተመልሰው ጌታ ሆይ! አጋንንት
ስንኳ በስምህ ተገዝተውልናል አሉት:: እንዲህም አላቸው
. . .
እነሆ እባቡንና ጊንጡን ትረግጡ ዘንድ በጠላትም ኃይል
ሁሉ ላይ ሥልጣን ሰጥቻችሁአለሁ:: የሚጐዳችሁም
ምንም የለም::
ነገር ግን መናፍስት ስለ ተገዙላችሁ በዚህ ደስ
አይበላችሁ:: ስማችሁ ግን በሰማያት ስለ ተጻፈ ደስ
ይበላችሁ:: +"+ (ሉቃ.10:17)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>

https://t.me/zikirekdusn
"መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ::" /ማቴ ፫:፫/
ዝክረ ቅዱሳንን ተማሩ ብለን እንለምናችኋለን!!

ዝክረቅዱሳን (ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት)

" ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::
አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/
https://t.me/zikirekdusn
1.1K views "ወለተ ሥላሴ" "አነ ዘክርስቶስ" , 11:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-10 14:31:22
1.0K views "ወለተ ሥላሴ" "አነ ዘክርስቶስ" , 11:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-09 23:54:30 ✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
"የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል" ምሳ 1፥33
        
✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
ስንክሳር ዘወርኃ ግንቦት/፪/2

https://t.me/Orthodoxtewahdoc
የያዕቆብ ሌሊት ይሁንልን
2.0K views "ወለተ ሥላሴ" "አነ ዘክርስቶስ" , edited  20:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-09 23:53:32
2.0K views "ወለተ ሥላሴ" "አነ ዘክርስቶስ" , 20:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-03 16:28:37 #ኢትዮጵያዊው ፃድቅ አቡነ ሀብተ ማርያም

•••ወር በገባ በ26 የምናስባቸው አምስቱን መቅሰፍቶች የማስወገድ ስልጣን የተሰጠቸው ፃዲቁ አባታችን አቡነ ሀብተማርያም የነበሩበት ዘመን 1486 ዓ.ም ንጉስ እስክንድር በነገሰበት ጊዜ ነው። አባቱ ፍሬ ቡሩክ እናቱ ዮስቴና ይባላሉ። ፍሬ ቡሩክና ዮስቴና በህገ እግዚአብሔር በሃይማኖት በትሩፋት በምግባር ፀንተው የሚኖሩ ደጋግ ክርስቲያኖች ነበሩ፡፡ አቡነ ሀብተማርያም ከተሰጣቸው ቃል ኪዳኖች ውስጥ አምስት መቅሰፍቶች የማስወገድ ስልጣን ተሰጧቸዋል፡፡ እነሱም፡-

1/ መብረቅ፣
2/ ቸነፈር፣
3/ ረሃብ፣
4/ ወረርሽኝ፣
5/ የእሳት ቃጠሎ ናቸው፡፡
ከብዙ ተጋድሎ በኃላ ፃዲቁ አቡነ ሀብተማርያም በፀሎት ላይ ሳለ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ትዕዛዝ የቆምክባትን ቦታ ምስራቁን፣ ምዕራቡን፣ ሰሜኑን፣ ደቡቡን ባርክ አለው፡፡ ሲባርክም ሶስት አጋንንት በፀሎቱ ስልጣን ታስረው በፊቱ ታዩት።

እነዚህም አጋንንት ከኖህ ጀምሮ ሰውን በማሳት ከኖርን በኋላ ከአንተ ጋር ምን ፀብ አለን አሉ አባታችንም አቡነ ሀብተማርያም በትዕምርተ መስቀል ሲያማትብ ሁለቱን አጋንንት ምድር ተከፍታ ዋጠቻቸው አንዱ ጊዜዬ ስላልደረሰ አታጥፋኝ አለው፡፡ ያን ጊዜ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አቡነ ሀብተማርያምን ይህንን ተወው ጊዜው አልደረሰም አለው።

የጌታ ቃል እንዲህ ብሎ በተናገረ ጊዜ ሰይጣን ከአባታችን ተለይቶ ጠፋ፡፡ ማር 9፡23 ከዚህም በኋላ ዕለተ ሞቱ በደረሰ ጊዜ ለሞቱ ምክንያት የሚሆን ቸነፈር ያዘው፡፡ ጌታችንም በምስጋና ወደ እርሱ መጥቶ ወዳጄ ሀብተማርያም ሆይ ዛሬ ወደአንተ የመጣሁት ከድካም ወደ እረፍት እወስድህ ዘንድ ነው ሰባት የጽድቅ አክሊሎችን አዘጋጅልሃለሁ አለው።

1/ ስለ ንፁህ ድንግልናህ፣
2/ አለምንና በውስጡ ያለውን ንቀህ በመኖርህ፣
3/ ስለ ፍፁም ምንኩስናህ፣
4/ ዘወትር አራቱን ወንጌላትን በማንበብህና በመፀለይህ፣
5/ ስለ እኔ ብለህ ስለተራብከው፣
6/ በጾም ስለተጋደልክ፣
7/ ቂምና ጥላቻን፣ ትዕቢትን፣ ትምክህትን፣ በልብህ ውስጥ ባለማስቀመጥህ ስለ ንፁህ ተልዕኮ ክህነትህ፣ ስለ ንፁህ መስዋዕትህ ነው ብሎ ቃል ኪዳን ሰጠው፡፡

በተጨማሪም እኔ የሰጠሁህን ቃል ኪዳን ተስፋ አድርጎ መጽሐፈ ገድልህን ለሚጽፈው ስሙን በመንግስተ ሰማያት በእውነት መጽሐፍ እጽፈዋለሁ፣ ለቤተክርስቲያንህ ዘይትን፣ ወይንን፣ ዕጣንን፣ ህብስትን እስከ ቀዝቃዛ ውሃ ድረስ በአንተ ስም መብዓ የሰጠውን የወደደውን ሁሉ አደርግለታለሁ፡፡ በመንግስተ ሰማያትም ከወዳጆቼ ከቅዱሳን ጋር በደስታ አኖረዋለሁ፡፡

የአቡነ ሀብተማርያም ፈጣሪ ኃጢአቴን ይቅር በለኝ ብሎ ያንተን ስም ጠርቶ ቢለምነኝ ኃጢአቱን አስተሰርይለታለሁ ብሎ ቃልኪዳን ገባለት ይህንንም ካለው በኋላ ጌታችን ሶስት ጊዜ ሳመው፡፡ ያን ጊዜም ከመድኃኒዓለም ጣዕም ፍቅር የተነሳ ነፍሱ ከስጋው ተለየች። #መዝ [115*6] በሰማያዊ መልአክት በምድራውያን ስውራን ቅዱሳን ዘንድ ታላቅ ደስታ ሆነ #ህዳር 26 ቀን አረፈ፡፡ ካህናት በመልካም ልብስ ገንዘው በዝማሬ በማህሌት ከቅዱስ አባታችን ከአቡነ ተክለሃይማኖት አጽም ጋር በፃዲቁ መቃብር ቀበሩት፡፡

አሜን የአባታችን የአቡነ ሀብተ ማርያም በረከተ ረድኤት ምልጃቸው ከሁላችን ጋር ይሁን።

☞ወር በገባ በ26 የጻድቁ አባታችን የአቡነ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን ወርሐዊ
መታሰቢያቸው ነው፡፡
☞በ245 አመተ ምህረት በቅድስት ሀገር እየሩሳሌም ኅዳር 26 ቀን ተወለዱ፡፡
☞ሲወለዱም ታላቅ ብርሀን ከሰማይ ወርዶ ለ7ቀናት አብርቷል፡፡
☞በተወለድም ጊዜ አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወለድ ቅዱስ አሀዱ ውእቱ
መንፈስ ቅዱስ ብለው ፈጣሪያቸውን በአንድነት በሦሰትነት አመስግነዋል፡፡
☞አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሀን በሌላኛው ሰማቸው ፍሬምናጦስ እየተባሉ
ይጠራሉ፡:
☞በ257 አመተ ምህረት ከእየሩሳሊም ወደ ኢትዮጵያ መጡ፡፡
☞አባታችን በአክሱም በታላቅ ተጋድሎና በትጋት ኖሩ፡፡
☞ቅዳሜ እና እሁድ የዛፍ ቅጠሎችን ከመመገብ በቀር ሌላ ምግብ
አይቀምሱም ነበር፡፡
☞በየቀኑም አምስት ሺህ ስግደትን ይሰግዱ ነበር፡፡
☞ፍሬምናጦስ ወደ እስክንድሪያ ለመሄድ አስበው ሳለ እንደተኙ ድንግል
ማርያም ተገልጣላቸው (ድቅናና ቅስናን መቀበል ይገባሀል ለጵጵስና ተዘጋጅ
እግዚአብሄር ይችን ከፍ ያለች ማዕረግ ሰቶሃል የልጄ ወዳጅ ሆይ በጸሎትና
በልመናህ በስብከትህም የኢትዮጵያ ሰዎች ሁለ ይድናሉ፡፡በእጄህ ስጋዎ ደሙን
ይቀበላሉ አለቻቸው፡፡)
☞አባታችን በእመቤታች በአለ ረፍት ቀን ጥር 21 ቀን በአክሱም ፅዮን በውስጧ
ለመጀመሪያ ጊዜ ሲቀድሱ ቅዱስ ሚካኤል እና ቅዱስ ገብርኤል በግራ እና በቀኝ
እየራዷቸው እሳቸው ከምድር ሦስት ክንድ ከፍ ብለው ሥርአተ ቅዳሴውን
ፈጽመው ለነገስታቱም ለሕዝብም አቁርበዋል፡፡
☞አባታችንም በድፍን ኢትዮጵያ በአራቱም አቅጣጫ እየዞሩ፤ እያጠመቁ አብያተ
ክርስቲያናትን እያሰሩና አገልጋይ የሚሆን ቀሳውስት እየሾሙ በሀገራችን ላይ
ብርሃንን የፈነጠቁ ለኢትያጵያ መግለጽ ከሚቻለው በላይ እጅግ ታላቅ
ባለውለታዋ ናቸው፡፡
☞ከአባ ሰላማ በፊት አኛ ኢትዮጵያውያን ክርስቶስን ከማመን በቀር ጥምቀትና
ሥጋ ወደሙ የመቀበል ልማድ አልነበረንም፡፡ በድንኳን ካለችው ታቦተ ጽዮን
በቀርም ታቦታትና አብያተ ክርስቲያናት አልነበሩም፡፡
☞አባታችን አብነ ሰላማ ከመጡ በኃላ ነው አብያተ ክርስቲያናት የታነጽት
ገዳማት የተገደሙት፡፡
☞አባታችን በተንቤ ምድር በምነና በጽሙና ሲቀመጡ ቆጥኝ ፈልፍለው በሠሩት
ቤተክርስቲያን ላይ የብርሃን መሰላል ተተክሎላቸው በእርሱም ወደ ሰማይ
ወጥተው ከሃያ አራቱ ካህናት ሰማይ ጋር የሥላሴን መንበር አጥነዋል፡፡
☞የተንቢን ምድር ቡሩካን በሆኑ እጃቸው አንስተው አስባርከዋል፡፡
☞መድሀኒአለም እንዲህ አላቸው (በክብር የሚመስልህ የለም እኔ ፈጣሪህ
የእሳት ፈረሶች የሚሆኑ መላዕክት በኪሩቤል ላይ እንደምቀመጥ አንተም ከእነርሱ
በላይ ትሆናለህ፡፡
☞ሰለ ትምህርት ሰለ ስብከትህ ኢቴዮጵያን በሃይማኖት ስለ አበራሀቴ ከፍ ያለ
ክብራትና ማዕረጋትን ፈጽሜ ሰጠሀሁ አንተም ከበቅዱሳን በላይ ብርሀን
አደረግሁ፡፡ከእናቴ ከድንግል ማርያም በታች ትቀመጣለህ አላቸው፡፡
☞አባታችን አባ ሰላማ ሐምሌ 26 ቀን ሲያርፍ ነፍሳቸውን መላዕክት አይደሉም
ራሱ መድሀኒአለም በክብር ተቀብሎ ከእርሱ ጋር አሳስጓታል፡፡
☞ቅዱሳን ነገስታት አብርሀ ወ አጽበሀም ጻድቁ ከዐረፍ በኃላ ወደ ደብረ
መድሀኒት መጥተው ለመካነ መቃብራቸው ሲሰግዱ አባ ሰላማ
ተገልጠውላቸው ከእነሰራዊታቸው ባርከዋቸዋል፡፡
☞የጻድቁ አባታችን በረከት ረዲኤታቸው እንዲሁም አማላጅነታቸው አይለያችሁ፡፡
☞የጽሁፍ ምንጭ መዝገበ ቅዱሳን
የአባቶቻችን በረከት አይለየን አሜን
417 views "ወለተ ሥላሴ" "አነ ዘክርስቶስ" , 13:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-03 16:28:24 #አቡነ ኢየሱስ ሞዓ

#ወር በገባ በ26 ለጸሎት ወደ ሐይቁ ሲገቡ ብርሃን ከሰማይ ይወርድላቸው የነበሩት ለ52 ዓመትም በሐይቁ ውስጥ ቆመው ሲጸልዩ የኖሩትና ከየገዳማቱ ቅዱሳን መጻሕፍትን በማሰባሰብና በመጻፍ የመጀመርያውን ዘመናዊ የቤተ ክርስቲያን ቤተ መጻሕፍትና ት/ቤት በሐይቅ እስጢፋኖስ ገዳም በማቋቋም 800 የበቁ ቅዱሳን ሊቃውንት መነኮሳትን አሠልጥነው በመሾም በመላ ሀገራችን ያሠማሩ የነበሩት ‹‹ወላዴ አእላፍ ቅዱሳን›› አቡነ ኢየሱስ ሞዐ በወርሐዊ በዓላቸው ታስበው ይውላሉ ነው፡፡
አቡነ ኢየሱስ ሞዐ፡- ሀገራቸው ጎንደር ክፍለ ሀገር ስማዳ ወረዳ ሲና ዳኅና በሚባል ቦታ ነሐሴ 26 ቀን ተፀንሰው ግንቦት 26 ቀን 1210 ዓ.ም ከአባታቸው ዘክርስቶስና ከእናታቸው እግዚእ ክብራ ተወለዱ፡፡ የተወለዱትም በቅዱስ ነአኲቶ ለአብ ዘመነ መንግስት ነው፡፡ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ የአቡነ ተክለ ሃይማኖት የቆብ አባት ሲሆኑ ታላቁን ሐይቅ ቅዱስ እስጢፋኖስን ገዳም የቆረቆሩ ደገኛ አባት ናቸው፡፡ ዕድሜያቸው 30 ዓመት እስከሚደርስ ድረስ ከቤተሰቦቻቸው ትምህርተ ሃይማኖትንና ግብረ ገብን ሲማሩ ከቆዩ በኋላ በ1240 ዓ.ም ይህንን ዓለም በመተው ወደ ደብረ ዳሞ ገዳም ገቡ፡፡ በደብረ ዳሞ ገዳም መነኰሳቱን እየረዱ፣
የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት እያጠኑ፣ ቅዱሳት መጻሕፍትን እየገለበጡ ለሰባት ዓመታት ከቆዩ በኋላ የደብረ ዳሞ 3ኛ አበ ምኔት ከሆኑት ከአባ ዮሐኒ እጅ ምንኩስናን በ1247 ዓ.ም ተቀበሉ፡፡አንድ ቀን ሌሊት መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ወደርሳቸው መጥቶ ‹‹የስምህ መክበርያ ወደሆነው ሐይቅ ወደ ተባለው ሥፍራ ሂድ›› አላቸው፡፡ አባታችንም‹‹ቦታውን እንዴት ዐውቀዋለሁ?›› በማለት መልአኩን ቢጠይቁት ‹‹ተነሥ! ጉዞህን ጀምር ቦታውን እኔ አሳይሃለሁ›› አላቸው፡፡ አባ ኢየሱስ ሞዓ በመልአኩ እንደታዘዙት ከበዓታቸው ተነሥተው ተከተሉት፡፡ የብዙ ወራት መንገድ የሆነውን
ጐዳናም በስድስት ሰዓት አደረሳቸው፡፡ በዚያን ወቅት ከሐይቅ ገዳም በስተ ሰሜን ወደነበረው ጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤተ ክርስቲያን ደረሱ፡፡ ወደ ሐይቅ እስጢፋኖስ ከመግባታቸው በፊት ለ6 ወራት ያህል በጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤተ ክርስቲያን አገልግለዋል፡፡ ያገለግሉበት በነበረው ቤተ ክርስቲያን ቀን ቀን ሕዝቡን ሲያስተምሩ በመዋል ሲመሽ ወደ ሐይቁ በመግባት ሲጸልዩ ያድሩ ነበር፡፡በሐይቅ እስጢፋኖስና በዙርያው ለነበሩ አበውም ማታ ማታ አንድ ብርሃን ወደ ሐይቁ ሲገባ ጠዋት ጠዋትም ሲወጣ ይታያቸው ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ አባታችን በገዳሙ አባቶች ልመናና በልዑል እግዚአብሔር ትዕዛዝ ወደ ሐይቅ ገዳም ገብተው አበምኔት ሆኑ፡፡ሐይቅ እስጢፋኖስ ገዳም ከደሴ 30 ኪሎ ሜትር ርቆ የሚገኝ ሲሆን የመሠረቱት ካልዕ ሰላማ የተባሉ ግብፃዊ ጻድቅ ናቸው፡፡ ሐይቅን አባ ሰላማ ካልዕና ዐጼ ድል ነአድ በ862 ዓ.ም ነው የቆረቆሩት። ገዳሙን ካቀኑት በኋላ ‹‹የማንን ታቦት እናስገባ?›› ብለው ሲያስቡ ቶራ የምትባል እንስሳ ጭነት ተጭና ከመካከላቸው ተገኘች፤ ጭነቱን አውርደው ቢያዩት በሐር ጨርቅ የተጠቀለለ የቅዱስ
እስጢፋኖስንና የቅዱስ ጊዮርጊስን ሁለት ታቦት አገኙ፡፡ በላዩም ላይ ‹‹ይህንን ታቦት በኢየሩሳሌም የሚኖሩ የተሰወሩ ቅዱሳን ከእግዚአብሔር ታዘው የላኩት ነው›› የሚል ጽሑፍ አገኙ፡፡ይህ ከሆነ ከ400 ዘመን በኋላ ነው አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ወደዚህ ቦታ የመጡት፡፡አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ለ52 ዓመት ቀን ቀን መንፈሳዊ ሥራቸውን እየሠሩ ሌሊት ሌሊት ሐይቁ ውስጥ ቆመው ሲጸልዩ ያድራሉ፡፡ አባ ኢየሱስ ሞዐ በሐይቅ እስጢፋኖስ በአበ ምኔትነት በቆዩባቸው 45 ዓመታት ከየገዳማቱ ቅዱሳን መጻሕፍትን በመገልበጥና በማሰባሰብ የመጀመርያው ዘመናዊ የቤተ ክርስቲያን ቤተ መጻሕፍት በሐይቅ እስጢፋኖስ ገዳም እንዲቋቋም አድርገዋል፡፡ በዚሁ
ገዳም ውስጥ የመጀመርያውን የቤተ ክርስቲያን ቋሚ ትምህርት ቤት በማቋቋም 800 መነኮሳትን በትምህርተ ሃይማኖት አሠልጥነው በንቡረ ዕድነት ማዕረግ ሾመው በመላ ሀገራችን እንዲሠማሩ አድርገዋቸዋል፡፡ ከእነዚህም
ተማሪዎቻቸው መካከል አቡነ ተክለ ሃይማኖት (ደብረ ሊባኖስ)፣ አቡነ ኂሩተ አምላክ (ጣና ሐይቅ ዳጋ እስጢፋኖስ) ፣አቡነ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ (ቦረና)፣ አባ በጸሎተ ሚካኤል (ቦረና)፣ አቡነ ገብረ እንድርያስ (ቦረና)፣ አቡነ ሕዝቅያስ
(ቦረና)፣ አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ (ዳውንት)፣ አቡነ አሮን (መቄት- ጣራው ክፍት የሆነው)፣ አቡነ ተክለ ኢየሱስ ሞዐ (ሐይቅ)፣ አቡነ አላኒቆስ (ትግራይ)፣አቡነ በግዑ (ሐይቅ)፣ አቡነ ሠረቀ ብርሃን (ሐይቅ)፣ አቡነ ብስጣውሮስ (ሐይቅ)፣ አቡነ ዮሴፍ (ላስታ) ዋና ዋናዎቹና በጣም ጥቂቶቹ ናቸው፡፡ ጻደቁን ንጉሥ ዐፄ ይኩኖ አምላክንም በትምህርተ ሃይማኖት አንጸውና ኮትኩተው ያሳደጉት ጻድቁ አባታችን ናቸው፡፡ እነዚህም ልጆቻቸው እያንዳንዳቸው እጅግ አስገራሚ ገድል ያላቸው የከበሩ ቅዱሳን ናቸው፡፡
አቡነ ተክለ ሃይማኖት ወደ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ መጥተው በሐይቁ ዳር ቆመው ሳለ ቅዱስ ሚካኤል መጥቶ በእግሩ በውኃው ላይ እየሄደ እያሳያቸው ተከትለውት እንዲሄዱ ነገራቸው። አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖትም ሐይቁን
በእግራቸው ተራምደው ተሻግረው አቡነ ኢየሱስ ሞዐን አገኟቸው፡፡ እርሳቸውም አቡነ ተክለ ሃይማኖት ወደ እርሳቸው እየመጡ እንደሆነ በመንፈስ ዐውቀው ነበርና ሲያገኟቸው በጣም ተደስተው ከተቀበሏቸው በኋላ አመነኩሰዋቸዋል፡፡
አቡነ ኢየሱስ ሞዐ እጅግ በጣም ብዙ መነኮሳትን አፍርተዋል ፡፡የመጀመሪያው መነኩሴ አባ እንጦንስ ነው፡፡ እንጦንስ መቃርስን፣ መቃርስ ጳጉሚስን፣ ጳጉሚስ ቴዎድሮስን፣ አቡነ አረጋዊንና 8ቱን ቅዱሳን አመነኮሱ፡፡ አቡነ አረጋዊም ወደ
ኢትዮጵያ በ460 ዓ.ም መጥተው ክርስቶስ ቤዛን፣ አባ ክርስቶስ ቤዛም መስቀለ ሞዐን፣ መስቀለ ሞዐም አባ ዮሐኒን፣ አባ ዮሐኒም አባ ኢየሱስ ሞዐን፣ አባ ኢየሱም ሞዐም አቡነ ተክለ ሃይማኖትን አመነኮሱ፡፡ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ምን
ያህል ቀደምትና ባለ ታሪክ አባት እንደሆኑ ከዚህ መረዳት ይቻላል፡፡በዮዲት ጉዲት እጅጉን ተጐድታ የነበረችው ሀገራችን ዳግም የወንጌሉ ብርሃን እንዲበራባት ሊቃውንት፣ እንዳይታጡባት፣ ቅዱሳት መጻሕፍት እንዳይቆነጻጸሉ፣ መነኮሳት አባቶች ወደ ደቡብ ኢትዮጵያ ወርደው ገዳማትን እንዲያስፋፉ ያደረጉት አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ለቤተ ክርስቲያናችንና ለሀገራችን ትልቅ ባለውለታ ናቸው፡፡በተለይም በሐይቅ እስጢፋኖስ ያፈሯቸውን 800 ሊቃውንት በመላዋ ኢትዮጵያ በመሰማራታቸው ዛሬ የምናያቸውን አብዛኛዎቹን ገዳማትና ቅዱሳት መጻሕፍት አቆይተውልናል፡፡ አባታችን ለ45 ዓመታት ሐይቅ እስጢፋኖስ ገዳምን በአበ
ምኔትነት እያስተዳደሩ ከቆዩ በኋላ ኅዳር 26 ቀን 1292 ዓ.ም በዕለተ እሑድ ዐርፈዋል፡፡ ባረፉበት ዕለትም በወቅቱ በቦታው የታየው ብርሃን ሀገሪቱን መልቶ ታይቷል፡፡
ረድኤት በረከታቸው ይደረርብን በጸሎታቸው ይማረን!
ምንጭ ከገድላት አንደበት
275 views "ወለተ ሥላሴ" "አነ ዘክርስቶስ" , 13:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ