Get Mystery Box with random crypto!

"ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒

የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodoxtewahdoc — "ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒
የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodoxtewahdoc — "ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒
የሰርጥ አድራሻ: @orthodoxtewahdoc
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 22.88K
የሰርጥ መግለጫ

🌹«ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን
/አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ።♥ https://t.me/Orthodoxtewahdoc

ሐምሌ 3 በ2014 ዓ°ም ተከፈተ።
📌እግዚአብሔር ቢፈቅድ የቅዱሳኑን ታሪክ እንመማርበታለን ብለን ከፈትነው ቅዱስ እግዚአብሔር ይፍቀድልን አሜን‼
❤የእመ ብርሃን ልጅ🤗

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 76

2023-03-07 21:50:19 ሊያድነን ወደደ፥ ሰው ሆነልን፥ አዳነን!
*[የሰኞ ውዳሴ ማርያም - ስለመዳናችን የሚነግረን]
ጌታ 5500 ዘመን በዲያብሎስ ባርነት የነበረ አዳምን ነጻ ያወጣው ዘንድ "ፈቀደ - ወደደ"። እግዚአብሔር ሰውን ለማዳን ሲነሳ የመጀመሪያው ነገር "ሊያድነን መውደዱ፥ ሊታረቀን መፍቀዱ" ። ወደ ቀደመ ክብራችን ልጅነት፥ ወደ ቀደመች ርስታችን ገነት ሊመልሰን መፍቀዱ የመጀመሪያው የፍቅሩ መገለጫ ነበር። እግዚአብሔርን የመሰለ ጌታ፥ ገነትን የመሰለች ቦታ፥ ልጅነትን የመሰለ ከፍታ በማጣቱ ልቡ ያዘነና የተከዘ አዳምን ነጻ ሊያወጣው ወድዶ ብቻ አልቀረም።

ሊቁ "ሠረቀ በሥጋ እም ድንግል ዘእንበለ ዘርዐ ብእሲ ወአድኅነነ።" እንዳለ ከድንግል ያለ ወንድ ዘር በሥጋ ተወልዶ አዳነን። "ሊያድነን ቢወድ፥ ሊታረቀን ቢፈቅድ" እንኳን የአዳምን ካሳ ከፍሎ ፍትሕንና ይቅርታን ሊያስማማ የሚችል፥ ዓለምን ማዳን የሚችል ፍጡር ባለመኖሩ እርሱ ራሱ ሰው ሆነልንና አዳነን። ይህ ሰው የሆነና እኛን ይቅር ይለን ዘንድ የወደደ በእኛም ያደረ ቃል ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ቅዱስ ዮሐንስ "ከአባቱ ዘንድ እንዳለው ክብር የሆነው ክብሩን አየን።" ብሎ እንደተናገረ እኛም "ወርኢነ ስብሐቲሁ - ክብሩን/ምስጋናውን አየን" ብለን ተናገርን(ዮሐ 1:14)።

"እንዲሁ" ዓለምን የወደደ እግዚአብሔር፥ በመልክ የሚመስለው በባሕርይ የሚተካከለው አንድያ ልጁን "የሚያምንበት ሁሉ እስከ ዘለዓለም ፈጽሞ ይድን ዘንድ" አሳልፎ ሰጥቷልና፥ "ውረድ፥ ተወለድ፥ ሙት፥ ተሰቀል፥ አድን" ብሎ ለድኅነተ ዓለም ልኮታልና ሰው ሆይ ፈጽሞ ደስ ይበልህ። ልዑል እግዚአብሔር ክንዱን ሰድዶልናልና።

ይህ ክርስቶስ ሰው በመሆኑ የነቢያት ሀገራቸው ቤተልሔም ደስ ይላታል። የቀድሞውን አዳም ነጻ የሚያደርገው ወደ ክብሩም የሚመልሰው ሁለተኛው አዳም በእርሷ ተወልዷልና። የሰው ሁሉ ሰውነትም ክርስቶስ ሰው በመሆኑ ፈጽሞ ደስስ ይለዋል። የቀድሞውን እርግማን አጥፍቷልና፥ ሕዳሴንም አድሎናሎና። ቅዱስ ጳውሎስ "እንግዲህ በክርስቶስ ኢየሱስ ላሉት አሁን ኵነኔ የለባቸውም።" ብሎ እንደተናገረ(ሮሜ 8:1)።

በዚህች ዕለት የሚነበበው ውዳሴ ማርያም እንደሚነግረን ሰውን ለማዳን የወደደ፥ ከመውደዱም የተነሳ ሰው ሆኖ የተዛመደ ክርስቶስ አዳምን ወደ ቀደመ ክብሩ ልጅነት፥ ወደ ቀደመ ቦታው ገነት መልሶታል። "መሬት ነህና ወደ መሬት ትመለሳለህ" ብሎ የፈረደበትን ፍርድ አጥፍቶ ተስፋ መንግሥተ ሰማያትን ሰጥቶታል፥ ከስህተትም አድኖታል። ሔዋንንም ከዕርግማን፥ ከሞት ጻዕረኝነትም ነጻ አድርጓታል። የቀደመ  እርግማናቸውን አጥፍቶ የጠላት ምክሩን አፍርሶባቸዋል።

ክብር ምስጋና ለእርሱ ይሁን። የእመቤታችንን የውዳሴዋን ፍቅር ያሳድርብን።

ዲ.ን አምደመስቀል ሙሉጌታ

አቤቱ በመንግስትህ በመጣህ ጊዜ አስበን
1.3K views "ወለተ ሥላሴ" "አነ ዘክርስቶስ" , 18:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-07 20:13:12 በጾም ሰዓታችሁ ጊዜ ይሁንም አይሁንም ሦስት ነገሮችን በሕሊናችሁ ትይዙ ዘንድ እመክራችኋለሁ፡፡
እነርሱም፡-
☞ ክፉ ከመናገር መከልከልን፣
☞ ማንንም ሰው እንደ ጠላት ከማየት መቆጠብንና
☞ እንደ ልምድ አድርጋችሁ ከያዛችሁት መሐላ ትርቁ ዘንድ እመክራቸኋለሁ፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
430 views "ወለተ ሥላሴ" "አነ ዘክርስቶስ" , 17:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-07 19:45:51
"…ፓስተር ቢንያምም ከሰበር ሰሚ ችሎት በፊት አሁን ከመሸ ከወኅኒ ቤት ተፈቷል። ወንድማችን እንኳን ደስ አለህ…!ምንጭ ዘመዴ

"…እግዚአብሔር ይመስገን

ቴሌግራም ይቀላቀሉ

https://t.me/ZemedkunBekeleZ
580 views "ወለተ ሥላሴ" "አነ ዘክርስቶስ" , 16:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-07 17:43:06 #ቅዱስ ባለ ወልድ

•••የባለወልድ{ በዓለ ወልድ }ትርጉም ወር በገባ በ29 ቀን የሚከበር ጌታችን በድንግል ማርያም ማሕፀን ተፀንሶ መወለዱንና ሙቶ መነሳቱን የሚያሳስብ በዓል ነው።ቀደም ሲል የነበሩ አበው ነቢያት ሲጸልዮ{ እግዚእነ አምላክነ ንጉስነ } እያሉ ይጸልዮ ነበር፡፡ ይህም ከግብረ ዲያብሎስ ለዲያብሎስ ከመገዛት እንዳልዳኑ ለማጠየቅ ነው፡፡እኛን ግን ከግብርናተ ዲያብሎስ ነጻ አውጥቻችኋለሁ ሲል አባታችን ሆይ ብላችሁ ጸልዮ ብሎ አስተማረን፡፡ልጆች እንደመሆናችሁ መጠን እግዚአብሔር አባ አባቴ ብላችሁ የምትጠሩትን የልጁን መንፈስ በልባችሁ አሳደረ።{ ገላ 4፥6 }፣{ሮሜ 8፥15 }አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር አባትነቱን በሁለት ነገር ከምድራዊ አባት ለይቶታል ፡፡በመውለድና በመግቦት ከምድራዊ አባት ይለያል፡፡ምድራዊ አባት በዘር በሩካቤ ይወልዳል፡፡በማር፣በወተት፣በፍትፍት ያሳድጋል፤ኃላም በሞት ሲያልፍ የምታልፍ ርስትን ያወርሳል፡፡ እርሱ አምላካችን ግን ሲወልደን በርቀት ሲያሳድገንም በሥጋውና በaደሙ ነው፡፡ከስጋ የተወለደ ስጋ ነው ከመንፈስ የተወለደ መንፈስ ነው።{ ዮሐ 3፥6 }ኃላም የማታልፍ ርስት መንግስተ ሰማያትን በክርስቶስ ደግሞ ርስትን ተቀበልን
{ ኤፌ 1፥11 }፣{ 1ኛጴጥ 3፥5 }።
ቅዱስ ባለወልድ የአምላኮች አምላክ የጌቶች ጌታ የንጉሦች ንጉሥ አንተ ነህ የቅዱሳን አምላክ የድንግል ማርያም ልጅ በመንገዳችሁ ሁሉ ይቅደም በያላችሁበት ሰላማቹን ያብዛው የእለት እንጀራችንን ይስጠን።ቅዱስ ባለወልድ ከክፉ ነገር ሁሉ ይጠብቀን ቸርነቱ ምሕረቱ ረድኤት በረከቱ አይለየን ቤተክርስቲያንና ሃገራችን ኢትዮጵያን ከፈተና ይጠብቅልን ብርታቱንም በመላው ሕዝበ ክርስቲያን አድሮ ይኑር አሜን።
☞በአበው ነቢያት ሐዋርያትን በሐዋርያትም እኛን አቅርቦ አባታችን ሆይ ብለን እንድናመሰግነው ለፈቀደልን ለልዑል እግዚአብሔር ክብር ኃይልና ምስጋና ይድረሰው ለዘለዓለሙ አሜን።
የቅዱስ ባዓለ ወልድ ይቅርታው ቸርነቱ ረድኤት በረከቱ አይለን።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለ ወላድቱ ድንግል ማርያም
ወለ መስቀሉ ክቡር
አሜን ።አሜን ። አሜን።
ይቆየን

https://t.me/Orthodoxtewahdoc
625 views "ወለተ ሥላሴ" "አነ ዘክርስቶስ" , 14:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-07 17:42:55 #ቅዱስ አባታችን አባ አፍፄ ማለት

☞ወር በገባ በ 29 የአባ አፍጼ ወርሐዊ መቲሰቢያው ነው፡✞ አባ አፍጼ ከተሰዐቱ ቅደሳን አንዱ ናቸው፡፡
☞አባቱ አቡድራስ እናቱ አቅሌስያ ይባላሉ፡፡ በሕፃንነቱ ትምህርተ ቤተ ክርስቲያንን ተምሮ በ15 ዓመቱ ዲቁና ከተቀበለ በኃላ ወደ ግብጽ በመኼዶ ገዳመ አስቄጠስ ገብቶ ሥርዐተ ምንኩስናን ተቀብሏል፡፡

☞ከሌሎች 8 ቅዱሳን ጎደኞቹ በመኾን ወደ ኢትዮጵያ መጥቷል፡፡
☞በአክሱም ተቀምጦ በቤተ ቀጢን የሀገሪቱን ባሕል እና ቋንቋ አጥንቷል፡፡
☞ገዳማዊ ኑሮን ለመመሥረት በእየራሳቸው ሲበታተኑ ከአክሱም 8 ኪሎ ሜትር
ራቅ ብሎ ወደ ሚገኝ የሐ ወደ፡ተባለው ጥንታዊ ከተማ በመኺድ ጣዖት
አምላኪውን ሕዝብ አስተምሮ ወደ ክርስትና መልሷል፡፡
☞ቀጥሎም ሳባውያን ከደቡብ ዐረብ በመፍለስ ቀይ ባሕር ተሻግረው የሐ
ውስጥ እንደ ሰፈሩ የሠሩትን የጣዖት ማምለኬያ መቅደስ ባርኮ ወደ ቤተ
ክርስቲያን በመለወጥ ለክርስቲያኖች መገልገያ አድርጎታል፡፡
☞ንዑድ ክቡር የዓለም ብርሃን የፀሐይ ጮራ የሆነ ተአምራትና ድንቆችን
የሚያደርግ የማር አቡነ አፍጼ ተአምር ይህ ነው ጸሎቱ በረከቱ ከህዝበ
ክርስቲያኑ ጋር ይሁን፡፡
☞ልጅ የሌለው ልጅ በማጣቱም ምክንያት ሲያዝን የሚኖር አንድ ሰው ከሩቅ
ሀገር ንዑድ ክቡር የዓለም ብርሃን ወደ ሆነ ተአምራትና ድንቆችን ወደ ሚያደርግ
ማር አቡነ አፍጼ ቤተ ክርስቲያን መጣ በአቡነ አፍጼም በዓል ቀን አባቴ ሆይ
በእግዚአብሔር ዘንድ በከበረች በምትስማም ጸሎትህ የተሰገነ እግዚአብሔር
ደስ የሚያሠኝ ፈጽሞ የተባረከ ትእዛዙ መንፈሳዊት የሰውንም ፍጠረት ሁሉ
የሚያረጋጋ ፈቃድን የሚፈጽም ልጅ ትሰጠኝ እማፀናለሁ ብሎ ለመነ፡፡
☞በበዓሉ ቀን ማምሻ ንዑድ ክብር የዓለም ብርሃን የፀሐይ ጮራ የሆነ
ተአምራትና ድንቆችን የሚያደረግ የማር አቡነ አፍጼ በግልጥ ታየው ሰውየውንም
ወዳጄ ሆይ ልጅ በማጣት ምክንያት አትዘን እንሆ ሚስትህ እግዚአብሔር ደስ
የሚያሠኝ ትእዛዙንም አብዝቶ የሚፈጽም በጎና የተባረከ ልጅ ትወልዳለች አለው፤
ይህንንም ብሎ ንዑድ ክቡር የዓለም ብርሃን የፀሐይ ጮራ የሆነ ተአምራትን
ድንቆችን የሚያደርግ ማር አቡነ አፍጼ ከእሱ ተሠወረ፡፡
☞ሰውየውም ይህንን ነገር ሰምቶ ፈጽሞ ደስ አለው፤ንዑድ ክቡር የዓለም ብርሃን
ከሆነ ከማር አቡነ አፍጼ ግርማ ሞገስና ከጸዳሉ የተነሣ ይህን ሁሉ ቸርነት
ያደረገለትን ፈጽሞ እግዚአብሔር አመሰገነ፡፡
☞ከዚያ በኃላ ወደ ሀገሩ ተመለሰ ወደቤቱም ገብቶ ይህን ሁሉ ነገር
ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻው ድረስ ንዑድ ክቡር የዓለም ብርሃን የፀሐይ
ጮራ የሆነ ማር አቡነ አፍጼ እንደተገለጠለትም ለሚስቱ ነገራት፡፡የአቡነ አፍጼ
የገድሉና መጽሐፍ የተነበበትን የአባታችንን ጠበል ረጫት አጠጣትም፡፡
☞ከዚያ በኃላ ሚስቱን በግብር ዐወቃት ያንጊዜም ፀነሰች፡፡ የፅንሱ ጊዜ
ሲፈጸምም መልከ መልካም ልጅ ወለደችለት፡፡ አሦስት ዓመት ፍጻሜ በኃላ ይህ
ሰው ለዓለም ብርሃን አቡነ አፍጼ ቤተ ክርስቲያን እጅ መንሻ ይሰጥ ዘንድ ቡዙ
ገንዘብ ይዞ ሄደ፡፡
☞ያንም ገንዘብ ለካህናት ሰጣቸው በረከትም ተቀበለ፡፡
☞የንዑድ ክቡር የዓለም ብርሃን የፀሐይ ጮራ ተአምራትንና ድንቆችን
የሚያደርግ የማር አቡነ አፍጼን ደግነቱን ትሩፋቱን ተአምሮቹንና ድንቆችን
እየመሰከረ ወደ ሀገሩ ተመለሰ፡፡
☞ጸሎቱና በረከቱ የክርስቲያን ወገኖች ከምንሆን ከእኛ ከሁላችን ከሀገራችን
ከኢትዮጵያ ጋር ትሁን ለዘለዓለሙ ይሁን፡፡
☞(ገድለ አፍጼ)
☞አባታችነ አቡነ አፍጼ የእኛንም ጎዶሏችንም ይሙሉልን፡፡
☞ሲራክ ተክለጻዲቅ የተዋህዶ ልጅ
☞28-5-2014
425 views "ወለተ ሥላሴ" "አነ ዘክርስቶስ" , 14:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ