Get Mystery Box with random crypto!

"ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒

የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodoxtewahdoc — "ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒
የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodoxtewahdoc — "ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒
የሰርጥ አድራሻ: @orthodoxtewahdoc
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 22.88K
የሰርጥ መግለጫ

🌹«ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን
/አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ።♥ https://t.me/Orthodoxtewahdoc

ሐምሌ 3 በ2014 ዓ°ም ተከፈተ።
📌እግዚአብሔር ቢፈቅድ የቅዱሳኑን ታሪክ እንመማርበታለን ብለን ከፈትነው ቅዱስ እግዚአብሔር ይፍቀድልን አሜን‼
❤የእመ ብርሃን ልጅ🤗

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2023-06-12 19:13:47 ☞ወር በገባ በ6 የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ወርሐዊ መታሰቢያው ነው፡፡እኛ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አማኞች፡ኢየሱስ ስንል አምላከ አማልእክት፡ የአማልክት አምላክ ኢየሱስ ስንል እግዚእ ወአጋእዝት፡ - የጌቶች ጌታ

☞ኢየሱስ ስንል ንጉሠ ነገሥት፡ - የነገሥታት ንጉሥ
☞ኢየሱስ ስንል አልፋ ወ ኦሜጋ፡ - መጀመሪያው እና መጨረሻው፣ ፊተኛው
ኋለኛው
☞ኢየሱስ ስንል ንጉሠ ሰማይ ወምድር፡ - የሰማይና የምድር ንጉሥ
☞ኢየሱስ ስንል ኤልሻዳይ፡- ኹሉን ቻይ
ኢየሱስ ስንል አዶናይ፡ - መድኃኔዓለም
☞ኢየሱስ ስንል ወልደ አብ ወልደ ማርያም፡ - የአብ ልጅ የማርያም ልጅ
በተዋሕዶ
ልደት የከበረ
☞ኢየሱስ ስንል ፈጣሬ ኩሉ፡ - ኹሉን የፈጠረ
☞ኢየሱስ ስንል እግዚአብሔር ማለታችን ነው፡፡
ስሙን ስንጠራ ይኽ ሁሉ በልባችን ሰሌዳ ታስቦ ነው፡፡
☞ጌታዬ ኢየሱስ ሆይ አበቃቀሉ ለሚያምር ክቡር ለሆነው የራስ ፀጉር ሰላምታ
ይገባል፡፡
☞ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ከፀሐይ ብርሃን ይልቅ እጅግ ለሚያበራው ፊትህ
ሰላምታ ይገባል፡፡
☞ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ የፍጥረትን ጥሪ ከመስማት ቸል ለማይሉ
ጆሮችህ ሰላምታ ይገባል፡፡
☞ጌታዬ ኢየሱስ ሆይ እጅግ ያማረ የከርቤ መፍሰሻ ለሆኑ ከንፈሮችህ ሰላምታ
ይገባል፡፡
☞ጌታዬ ኢየሱስ ሆይ በታቦር ተራራ ምሥጢረ መለኮትህን ለመግለጽ
ተለንቀሳቀሰው አንደበትህ ሰላምታ ይገባል፡፡
☞ጌታዬ ኢየሱስ ሆይ ቸር ማኅያዊ ለሚሆን ቃልህ ሰላምታ ይገባል፡፡
☞ጌታዬ ኢየሱስ ሆይ ለሰው ፍቅር ሲል ለተጠማ ጉሮሮህ ሰላምታ ይገባል፡፡
☞ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ኅብረታቸው ነጭ ለሆነ የእጅ ጥፍሮችህ ሰላምታ
ይገባል፡፡
☞ጌታዬ ኢየሱስ ሆይ ምጥቀቱ ለማይ መረመር ዕርገትህ ሰላምታ ይገባል፡፡
☞(መልክአ ኢየሱስ)
☞ሲራክ ተክለጻዲቅ የተዋህዶ ልጅ
☞ https://t.me/Orthodoxtewahdoc
898 views "ወለተ ሥላሴ" "አነ ዘክርስቶስ" , 16:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 19:13:26 26//ከእንጨት ለቃሚዋ ቤት የገባህ ኤልያስ ሆይ ለአንተ ጭኖች ሰላም እላለሁ።በሚሰማ የበረከት ቃል ገንዘቧን በባረክህ ግዜ ጎዶሎ የነበረው የማሰሮ ዘይት ሞላ ተጨመረም እፍኝ ሙሉው ዱቄትም እጥፍ ድርብ ሆነ ።

*ሰላም ለአብራኪከ*

27፣ ዝናብን ለመስጠት ፀሎት በጀመርህ ጊዜ የራስህ መደገፊያ ለሆኑት ጉልበቶችህ ሰላምታ ይገባል ።

የባረካ ልጅ የሄኖክ ጓደኛ የቀርሜሎስ ሰው ኤልያስ ሆይ ለነፍሴ ንስሓ ፋሲካን አድርግበት ዘንድ አባቴ የማማለድ አዳራሽህ ያለው የት ነው።

*ሰላም ለአእጋሪከ*

28፣ በይሁዳ ምድር እስከ ምትገኝዋ እስከ ምድረ ኮሬብ ድረስ ለአርባ ቀን ያክል ያለማቋረጥ ለተጓዙ እግሮችህ ሰላምታ ይገባል ።ኤልያስ ሆይ የዘመኔን ጉድለት ንገረኝ። በፀሎትህም ነጭ የሆነ የበረዱን ዘመን ጠብቅ ለትውልድ ሁሉ ተስፋቸው የሀገሩ ፍሬ ነውና።

*ሰላም ለሰኮናከ*

29 ፣ በሰረገላ ከተጫነው ከንጉሱ ከአካዓብ ይልቅ አሯሯጡ ፈጣን ለሆነ ለተረከዝህ ሰላምታ ይገባል።

ኤልያስ ሆይ የሞት ሰረገላ ፈጥኖ በከበበኝ ግዜ እኔ ወደ ንስሀ ቤት በመግባት እቀድመው ዘንድ አዳኝ የሆነ የእውቀት ሀይልን አስታጥቀኝ።

*ሰላም ለመከየድከ*

30 .ወዲያና ወዲህ ሆኖ በተከፈለ ጊዜ ዮርዳኖስን ለረገጠው ጫማህ ሰላምታ ይገባል። አዲስ የሆነ የወልድ ማረግ መንገድን የረገጥህ ኤልያስ ሆይ በሌለበት ቦታ የሚነድድ እሳት ፈረስን አገኘህ፣ለዕርገትህ ጊዜም ነፋስን ጠቀስኸው።

*ሰላም ለአፃብኢከ*

31 ዐሥር ለሆኑ ደናግል ጣቶችህ ሰላምታ ይገባል፣ዳግመኛም ለመብራት ጥፍሮቻቸው ሰላምታ ይገባል ። የመርዓዊ የክርስቶስ ወዳጅ ኤልያስ ሆይ ዐሥሩን ቃላት መፈጸም የተሳነኝ እኔን እንደ ወዳጁ ዮሐንስ በፍቅርህ ግምጃ ካጌጡት ጋር ጨምረኝ

*ሰላም ለቆምከ ወለመልክእከ*

32 ለቁመትህ፣የተሰወረውን ለሚመለከት ለድንግሉ ለእስክንድር ዓይን ግልጽ ለሆነው ለመልክህም ሰላምታ ይገባል። የሰማዕታት መጨረሻ ጴጥሮስ ኤልያስ ሆይ በእውነት ተቆጣኝ፣ከዳግመኛም ሞት ታድነኝ ዘንድም በይቅርታ ዝለፈኝ።

*፫አመት ወ፮ አውራሃ* *ሰልስተ አመተ ወ ስድስቱ አውርሃ*

33 ሦስት አመት ከስድስት ወር ወደ በረሃ ሸሸህ በውስጧ ኖርህ።ኤልያስ ሆይ ለጌታህ መሸሽ መሪ የሆንኸውም አንተ ነህ ኢሳያስ በብሩህ ደመና ተጭኖ ወደ ምድረ ግብፅ ይወርዳል እያለ ተናግሯልና።

ስልሳውን የሰበታት ሱባዔ መፈጸምን ከፈፀምህ ብኃላ የክርስቶስን መምጣት ለሚቀድመው አመጣጥህ ሰላምታ ይገባል።
ኤልያስ ሆይ የበድንህ ማረፊያ እነሆ ጌታህ በተሰቀለበት ፣ደሙን፣ባፈሰሰበት፣ዮሴፍም በድኑን በሳማበት በፍጥሞ ነው።

*ሰላም ለምፅአትከ*

35. ራሱን አዳኝ ክርስቶስ ነኝ ለሚለው አውሬ ሰውነትህን ለመስጠትህ ሰላምታ ይገባል።የበጎች መዳኛ ኤልያስ ሆይ የርሃብ ተኩላዎችና ጽኑዕ ደዌ በግህ እኔን ከጉልምስና መንጋዬ እንዳይነጥቁኝ ጠባቂ ሁነኝ።

*ሰላም ለመጥዎትከ*

36. እንደ ደቀ መዝሙሩ እንደ ዮሀንስ ቃል በአራት ቀን እኩሌታ በሁለት ቀን ለሚሆን ትንሳዔህ ሰላምታ ይገባል።
መጥምቁ ዮሐንስ ስለጌታችን ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ከእኔ. በፊት የነበረው ከእኔ ብኃላ ይመጣል ብሏልና።ቅን የሆንህ ኤልያስ ሆይ በእውነትም ይገባኃል።

*ካህን ወነብይ ወሰማዕት*

37. ካሕንና፣ነብይ በሁለተኛው ጥሪት ሰማእት የምትሆን በታቦሩም ጉባኤም ከሐዋርያት ጋር ሐዋርያ የሆንህ፣የመነኮሳትንም ሕግ መስራች(ሠሪ)የሆንህ ኤልያስ ሆይ በአምስተኛው ሱባኤ በሰላም ምስጋናህን ፈጽሜያለሁና እንደ አስነሳህው እንደ ዮናስ ወዳጅ አድርገኝ

*ስብሐት ለአብ*

38 ,ለሄኖክ ስራውን ገናናነቱን ሁሉ ላሳየው ለአብ ምስጋና ይገባል ከሀዋርያት ጋር በአንድነት ክብሩን ያይ ዘንድ ኤልያስን ለመረጠው ለወልድ ምስጋና ይገባል ለእዝራ የእሳት ጽዋን ላጠጣው ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይገባል የኤልያስ መልክአ በዚህ ተፈጸመ :: ዳግመኛም ለአገልጋይህ ለእኔ የንስሀ ዘመንን ትሰጠኝ ዘንድ በመልክህ ሰላምታ እማጸንሀለሁ አሜን ::

*ኤልያስ እም ኤልሳዕ*

39, ከኤልሳዕ ይልቅ ሌላውን የማታስቀድም ኤልያስ ሆይ ካረግህ በኃላም ባህርን ስትከፍል ተመለከተህ እደዚሁም ሁሉ አንደበቴ ስምህን መጥራት እዳያቆርጥ ዳግመኛም ልቦናዬ አንተን ማስታወስን እዳይረሳ ዘወትር ከእኔ ጋር ሁን አሜን ::

አቡነ ዘበሰማያት____ የተለያዮ ትምህርቶች በዝህ ያግኙ https://t.me/+hHIKQgF1DygyOThk
643 views "ወለተ ሥላሴ" "አነ ዘክርስቶስ" , 16:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 19:13:26 ወር በገባ በ1እና በ6 ቅዱስ ኤልያስ ነው
መልከአ ቅዱስ ኤልያስ እነሆኝ #ኦ ኤልያስ

1.ተአምራትን ላደረገ ለደቀ መዝሙርህ ለኤልሳዕ ከመጠምጠሚያ ጋር መንፈስን በእጥፍ የሰጠኸው ኤልያስ ሆይ የመልክህን ሰላም እናገር ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እንደወለዳቸው በየሀገሩ ቋንቋም እንደተናገሩ እንደ ሀዋርያት በተቀደሰች ረድኤትህ ከጌታህ ጸጋን ስጠኝ።

*ሰላም ለትርጓሜ ስምከ*

2. ዘይት ለተባለ ለስምህ ትርጓሜ ሰላምታ ይገባል።መቆረጥን ላልተቆረጠ ጸጉርህም ሰላምታ ይገባል ።ስምህን በመጥራት ኤልሳዕ የዮርዳኖስ ውሃ ከፈለ ፤ክፋትን ሳልሰራ ክፉ ስምን አትስጠኝ።

*ሰላም ለርዕስከ ወለ ገጽከ*

3,ለራስህ መልኩ እንደ ጽጌረዳ ለሚያበራው ወደ ብሔረ ሕያዋን በገባ ጊዜ እስክንድር ለተመለከተው ፊትህም ሰላምታ ይገባል።ኤልያስ ሆይ የኩነኔ እና የጭቀትን ወንዝ እሻገርበትም ዘንድ የአንተን መጠምጠሚያህን ስጠኝ።

*ሰላም ለቀራንብትከ ወለአይንትከ*

4 //ለቅንድቦችህ በታቦር ደም ግባቱ ያማረ የክርስቶስን ምስጋና ለተመለከቱ አይኖችህ ሰላምታ ይገባል።

ከታላቅነቱ የተነሳ የሙሴ ጓደኛ የሐዋርያት አለቃቸው ኤልያስ ሆይ ይቅርታን እንዳደረገው እንደ አብድዪ ይቅርታህን አሳየኝ። እንደ ኢዩብም የኃይል መንፈስን አሳድርብኝ።

*ሰላም ለአእዛኒከ*

5. መጀመሪያ በኮሬብ ብኃላም በታቦር ከእግዚአብሔር ዘንድ ነገርን ለሰሙ ጆሮችህ ሰላምታ ይገባል።ኤልያስ ሆይ ምቾትን ሁሉ ትፈጽምልኝ ዘንድ ከድንግል ማርያም ጋር በአንድነት ና።

*ሰላም ለመላትሒከ*

6.ቀጭን እንደሆነ የፉጨት ድምፅ ያለ የአብን ቃል በሰማ ግዜ በመጠምጠሚያው ለተሸፈነው ፊትህ ሠላምታ ይገባል።ይዘኑትን ፊት ብሩህ የምታደርግ ኤልያስ ሆይ በጸሎትህ የመካኗ ደመና ማሕፀን በተፈታ ጊዜ በዚያን ወቅት ኀዘኑ ተረሳ።

*ሰላም ለአዕናፍከ*

7.የጻድቃን ነፍሶች በየጊዜው የሚያሸቱት ሽታው የአሞራ አበባ ለሆነው ለአፍንጫህ ሰላምታ ይገባል።
ከኄኖክና እርሱን ከመሰሉት ጋር በአንድነት የምትኖር ኤልያስ ሆይ ለተወደደው የይቅርታ ደመና አበባው እንዳያልፈኝ አባቴ ለአፍንጫዬ የመዓዛህን በር ክፈት።

8. *ሰላም ለልሳንከ ወለአፍከ*

ለከንፈሮችህ በጽሕም ለተከበበ ከዕርሱም የእሳትና የፍም ነጸብራቅ ለሚወጣበት ለአፍህ ሰላምታ ይገባል።የሁዋላና የፊት ነብይ ኤልያስ ሆይ በሄድሁበት መንገድ ዝናም እንዳይመጣብኝ የቀደመው ተአምርህን ፅንዓት ዛሬ አሳየኝ።

*ሰላም ለስህን ህብስተ*

9 .በመጀመሪያ በሁለተኛ ጊዜም በተቀደሰው መልአክ እጅ የህይወትን ሕብስት ላላመጠው ለጥርስህ ሰላምታ ይገባል። በየለቱ የማትለወጥ ጉዋደኛ ኤልያስ ሆይ በአንድነታቸው ክርክር እንዳይመጣ የዘወትር ፍቅርን ስጣቸው ።

*ሰላም ለልሳንከ*

10. በዕልፍ ሳይሆን በመቶ ወንዶች ዘንድ እንደሚነድድ እሳት ሰይፍ ለሆነው ለአንደበትህ ሰላምታ ይገባል። እስከዘላለሙ የማትተኛ ወፍ ኤልያስ ሆይ በፀሎትህ ዘወትር የሚያሰቃዬኝ የደዌ መንፈስ ከእኔ አስወግድ የአንደበቴ ዛፍ ለስምህ መጠለያ ነውና።

*ሰላም ለቃልከ*

11.በሽንገናላና በበደል ነገር ናቡቴን በገደለው ግዜ አክዓብን ላስደነገጠው ለቃልህ ሰላምታ ይገባል። ኤልያስ ሆይ በአምስቱ ሰነፎች ላይ በሩ በሚዘጋበት ግዜ ከሰማያዊ ሙሽራ ቤት ከብልሆቹ ጋር እገባ ዘንድ በደስታ ወደ አንተ አቅርበኝ።

*ሰላም ለእስትንፋስከ*

*12,,* የሞተ የመበለቷን ልጅ ላስነሣ ለትንፋሽህ የውኃው ምንጭ በጠፋ ጊዜም ለተጠማው ለጉረሮህ ሰላምታ ይገባል ።

ለአርባ ቀን ያህል የጾምህ ኤልያስ ሆይ ዛሬ ግን ረኅብና ጽምን አታሳየኝ ።አሞራ ሆነህ መግበኝ እንጂ።

*ሰላም ለክሳድከ*

*13,,* የቅድስና አስኬማን ለለበሰ ለአንገትህ ሰላምታ ይገባል። ልብሷ የፍየል ሌጦ ለሆነው ለትከሻህ ሰላምታ ይገባል። በምሳሌና በዜና ከታላላቆች ይልቅ ታላቅ የሆንህ ኤልያስ ሆይ ሕይወትህ የመላእክት ነው ። የሀገርህ ጠልም መና ነው አስኬማህም ነውር የለባትም ።

*ሰላም ለዘባንከ*

*14,,* ለጀርባህ የጉልማሳነትህ ጽሕም ንጉስ ለተጠጋበት በፊትህ ለሚገኘው ለደረትህም ሰላምታ ይገባል ። ሕማም በሌለበት ሀገር የምትኖር ኤልያስ ሆይ ነፋስ በነፈሰ ዝናብም በዘነመ ጊዜ በእቅፍህ አድርገህ ከበጋና ከክረምት መብረቅ ሰውረኝ ።

*ሰላም ለአዕዳዊከ*

*15,,* በመስቀል ላይ በቀራኒዮ እንደ ተሰቀለ እንደ ኢየሱስ ክርስቶስ ለጸሎት ለተዘረጉ እጆችህ ሰላምታ ይገባል ። ኤልያስ ሆይ ለለመነህ ምግቡን ስጠው። በፊትህ ቢበድልም በደሉን ይቅር በለው። ለሚቀና መገዛቱ ይቀርለት ዘንድ ተወስኗልና።

*ሰላም ለመዝራዕትከ*

16, በወይን ግድ እዳለ ቅርንጫፍ የአንጓዎችህ ቦታ ለሆኑ ክንዶችህ ሰላምታ ይገባል። በአለም ፍጻሜ ግዜ የትንሳኤን ተስፋ የምትናገር ኤልያስ ሆይ መጠኑ የአምላክ ትንሳኤ የሆነለት ትንሳኤህን በምናምን በእኛ ላይ በረከትህን ላክ።

*ሰላም ለእመትከ*

17,ለክድህ የሚሰጥ ስጋን ለመቀበል ከቁራ አፍ ይልቅ ለሚሰፋው ለመሃል እጅህ ሰላምታ ይገባል። ኤልያስ ሆይ የሳራ ሁለተኛ ከሆነች ከጥበበኛዋ እናትህ ሁለንተናህ በሳት ተከብቦ የተወለድኸው የእዮብ መታሰቢያ በሆነች በመስከረም አንድ ነው።

*ሰላም ለአጻቢእከ*

18// አምስት በወዲያ አምስት በወዲህ ሆነው በጥፍር ልብሶች ለተሸለሙ ጣቶችህ ሰላምታ ይገባል። ኤልያስ ሆይ በምድር ነገስታት እና በእየሱስ ክርስቶስ ፊት የነፍስና የስጋ ሞገስን ስጠኝ። አባት ሆይ አንተ የሞገስ ነብይ ነህ።

*ሰላም ለገቦከ*

19. ማረፊያን፣አልጋን፣ምንጣፍን ላልፈለገው ጎንህ ሰላምታ ይገባል፤የማትተኛ ዘወትርም የማታንቀላፋ ኤልያስ ሆይ ያለጊዜው ከመሞት ወጥመድ ማለፊያ ሁነኝ። ዘወትርም የምገረፍ አልሁን።

*ሰላም ለከርስከ*

20. መብል መጠጥ፣የካህኑ የአሮን ልብስም ለማያስጨንቀው ለሆድህ ሰላምታ ይገባል። ከዕዝራና ከሄኖክ ጋር አንድ የምትሆን ብፁዕ ኤልያስ ሆይ መጽሐፍህ ምስክር እንደሆነ ሀገርህ የተድላና የደስታ ሀገር አይደለችምን?

*ሰላም ለልብከ*

21. በመሬት እየኖረ እንደብፁዓን ፃድቃን የላዩን ለሚያስብ ልቦናህ ሰላምታ ይገባል። እንደ አምላክ በቃልህ ሁሉን የቻልህ ኤልያስ ሆይ ሰባ ሁለቱም የአክዓብ ልጆች ሁሉ በቃልህ ታምመው የጠፋ አይደለምን?

*ሰላም እብል ለኩልያትከ*

22. በሕይወት የምትኖር የሕያዋን አለቃ ኤልያስ ሆይ መንታ ለሆነው ኩላሊትህ ሰላምታ ይገባል ፤ አባት ሆይ ከሩቁ ሰማይ እሳትን በጠራህ ጊዜ፥ መሥዋዕትህን ፤ከድጋዩ ጋርም እንጨቱን በላ ። ከውኃው ጋርም መሬቱን ላሰ።

*እኤምሀ በህሊናዬ*

23 በሕሊናዬ የተቀደሰ ሕሊናህን ሰላም እልሀለሁ።ለውስጣዊ አካልህም ሁሉ ምስጋናን አቀርባለሁ።አሮጌውን የለበስህ አዲሱንም የተጎናጸፍህ ኤልያስ ሆይ ባለሟልነትን ባገኘህ ጊዜ የዝናምን ኃይል አቆምህ ለሶስት ጊዜ ያህልም የሰማይ እሳትን አወረድህ።

*ሰላም ለእንብርትከ*

24 ሞት ያልሰረቅህ መቃብርም ያላጠፋህ መዝገብ ኤልያስ ሆይ ለእንብርትህ ሰላምታ ይገባል።የአንደበቴን ሰላም ዕጠብቅ ዘንድ በደልን የሚያስተሰርይ አድርግልኝ በአዲስ ሕዝቦች መካከል እግዚአብሔርን ሽቶ እንደቀባች አንደ ጥበበኛዋ ማርያምም አድርገኝ።

*ሰላም በኅቊኤከ*

25//መታጠቂያ ቁርበት ለሆነ ለወገብህ ሰላምታ ይገባል። የመለኮት ቃል ምሳርህም አካዝያስ ዛፍን የቆረጠው ነው።ሰውነትህ ጸጉር ነው።ኑሮህም በገዳም ነው።በምግባርም በስም አንድ የምትሆኑ ኤልያስ እና ዮሐንስ ሆይ ዛሬ በበዓላችሁ ቀን ባርኩን።

*ሰላም እብል ለዘዚአከ*
616 views "ወለተ ሥላሴ" "አነ ዘክርስቶስ" , 16:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 19:12:45 #ማርያም መግደላዊት

☞ወር በገባ በ6 ቀን የምትታሰው የመድኃኔዓለምን ትንሳኤ ቀድማ ያየች የተመረጠች የቅድስ ማርያም መግደላዊት ወርሐዊ መታሰቢያዋ ነው☞ማርያም መግደላዊት አስቀድሞ ጌታ 7 አጋንንትን ያወጣለት ደግ እናት ናት፡፡
ከዚያ ጀምራ ጌታን ተከተለች፡፡
☞እነዚህም ክፍ አጋንንት መንፈሰ ትዕቢት፤ መንፈሰ ጽርፈት(ስድብ)፤መንፈሰ
ቅንዓት፤ መንፈሰ ትውዝፍት(ምንዝር ጌጥ የማድረግ) መንፈሰ ዝሙት፤ መንፈሰ
ሐሜትና መንፈሰ ሐሰት ነበሩባት፡፡
☞ከሁሉ ሐዋርያቶችም እንኳን በፊት ለመጀመሪያ ጊዜ ትንሳኤውን የገለጠላት
እጅግ ዕድለኛ ሴት ነች፡፡
☞---ከሣምንቱ በፊተኛው ቀን መግደላዊት ማርያም ገና ጨለማ ሳለ ማልዳ
ወደ መቃብሩ መጣች ድንጋዩም ከመቃብሩ ተፈንቅሎ አየች -- ማርያም ግን
እያለቀሰች ከመቃብሩ በስተውጭ ቆማ ነበር ስታላቅስም ወደ መቃብሩ ዝቅ
ብላ ተመለከተች ሁለት መላእክት ነጭ ልብስ ለብሰው የኢየሱስ ሥጋ ተኝቶበት
በነበረው አንዱ በራስጌ ሌላው በግርጌ ተቀምጠው አየች -- ኢየሱስም ቆሞ
አየች እነሱም አንቺ ሴት ስለምን ታለቅሻለሽ?አሉት፡፡ አርሷም ጌታዬን
ወስደውታል ወዴት እንዳኖሩት አላውቅም አለቻቸው፡፡ ይህን ብላ ወደ ኃላ ዘወር
ስትል ኢየሱስ ቆሞ አየችው ኢየሱስም እንደሆነ አላወቀችም አንቺ ሴት ሰለምን
ታለቅሻለሽ ማንንስ ትፈልጊያለሽ አላት፡፡
☞እርሷም የአትክልት ጠባቂ መስሎት ጌታ ሆይ አንተ ወስደኽው እንደ ሆነህ
ወዴት እንዳኖርኸው ንገረኝ እኔም ወስጄ ሽቱ እቀባው ዘንድ አለቸው፡፡
☞ኢየሱስም ማርያም አላት፡፡ እርሷም ዘወር ብላ በዕብራይስጥ ረቢኑ አለቸው
ትርጓሜውም መምህር ሆይ ማለት ነው፡፡ ኢየሱስም ገና ወደ አባቴ አላረግሀምና
አትንኪኝ ነገር ግን ወደ ወንድሞቼ ሄደሽ እኔ ወደ አባቴና ወደ አባታችሁ ወደ
አምላኬ አምላካችሁ ዐርጋለሁ ብሏል ብለሽ ንገሪያቸው አላት፡፡
☞መግደላዊት ማርያም መጥታ ጌታ እንዳየች ይህን እንዳላት ለደቀ መዛምርቱ
ነገረቻቸው፡፡(ዮሐ 20 1-8)
☞ከጌታ ዕርገት በኃላ በጽርሐ ጽዮን መንፈስ ቅዱስን ከሐዋርያት ጋር ተቀብላ
ወንጌልን ሰብካለች፡፡
]ብዙ ሴቶችም ወደ ሃይማኖት መልሳለች፡፡
☞ማርያም መግደላዊት ቁጥሯ ከ36 ቅዱሳን እንስት ወገን ነው፡፡
☞ይቺ ሴት ስለ ክርስቶስ እየመሰከረች ስታስተምር ስድብና ግርፋት ደርሶባት
ከዚያም ከብዙ ተጋድሎ በኃላ በዚህ በነሐሴ 6ቀን ተጋድሎዋን ፈጽማ
በሰማዕትነት አርፋለች፡፡
☞(መድብለ ታሪክ)
☞የቅድስት መግደላዊት ማርያም የጸሎቷ በረከቷ አይለየን፡፡
☞ሲራክ ተክለጻዲቅ የተዋህዶ ልጅ

ጆይን እያላችሁ
https://t.me/Orthodoxtewahdoc
650 views "ወለተ ሥላሴ" "አነ ዘክርስቶስ" , 16:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 19:09:13 ††† እንኳን ለጻድቅና ሰማዕት አባ ቴዎድሮስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፣ አደረሰን። †††

††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††

††† አባ ቴዎድሮስ †††

†††አባ ቴዎድሮስ በ4ኛው መቶ ክ/ዘመን የነበረ ግብፃዊ አባት ነው:: ተወልዶ ባደገባት የእስክንድርያ ከተማ ብሉያትንና ሐዲሳት በወቅቱ ከነበሩ አበው ሊቃውንት ተምሯል:: ጊዜው ምንም መናፍቃን የበዙበት ቢሆን በዛው ልክ እነ ቅዱስ እለ እስክንድሮስና ቅዱስ አትናቴዎስን የመሰሉ ቅዱሳን ሊቃውንት ነበሩና ከነሱ የሚገባውን ወስዷል::

አባ ቴዎድሮስ "አባ" ያሰኘው ሥራው:- ሲጀመር ገና በወጣትነቱ ድንግልናንና ምንኩስናን በመምረጡ ነበር:: ምንም እንኳ ሐብት ከእውቀት ጋር ቢስማማለትም ይሕ እርሱን ከምናኔ ሊያስቀረው አልቻለም:: ከከተማ ወጥቶ: በዓት ወስኖ በጾምና በጸሎት ተወሰነ::

በ340ዎቹ ዓ/ም አካባቢ ግን በምዕመናን ላይ ከባድ ችግር ደረሰ:: የወቅቱ ነገሥታት በስመ ክርስቲያን አርዮሳውያን ነበሩና ሕዝቡን ማስገደድ: አንዳንዴም የአርዮስን እምነት ያልተቀበለውን ማስገደል ጀመሩ:: በዚህ ምክንያትም ታላቁ የኦርቶዶክስ ጠበቃ ቅዱስ አትናቴዎስን ከመንበሩ አሳደዱት:: በምትኩም አርዮሳዊ ሰው ዻዻስ ተብሎ ተሾመ:: ይህን ጊዜ ነው እንግዲህ እውነተኛ እረኛ ያስፈለገው::

በበዓቱ የነበረው አባ ቴዎድሮስ አላቅማማም:: ቤተ ክርስቲያን ትፈልገዋለችና መጻሕፍትን ገልጾ ከቦታ ቦታ እየተዘዋወረ ምዕመናንን ያጸናቸው ጀመር:: መናፍቃኑን ተከራክሮ ምላሽ በማሳጣት ሕዝቡን ከኑፋቄ በመጠበቅ የሠራው ሥራ ሐዋርያዊ ቢያሰኘውም ለአርዮሳዊው ዻዻስ (ጊዮርጊስ ይባላል) ሊዋጥለት አልቻለም::
በቁጣ ወታደሮችን ልኮ አባ ቴዎድሮስን ተቆጣው:: እንዳያስተምርም ገሰጸው:: አባ ቴዎድሮስ ግን እሺ ባለማለቱ ግርፋት ታዘዘበት::

ወታደሮች እየተፈራረቁ ሲገርፉት ረድኤተ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ነበርና ከዛ ሁሉ ግርፋት አንዲቷም አካሉ ላይ አላረፈችም:: በዚህ የተበሳጨው አርዮሳዊ ዻዻስ የአባ ቴዎድሮስን እጅና እግር ከፈረስ ጋሪ በኋላ አስረው በኮረኮንች መንገድ ላይ በፍጥነት እንዲያሮጧቸው አዘዘ::

ፈረሶቹ መሮጥ ሲጀምሩ የአባ ቴዎድሮስ አካሉ ይላላጥ ጀመር:: ትንሽ ቆይቶ ግን እጆቹ ተቆረጡ:: በኋላም ራሱ ከአንገቱ ተለይታ መንገድ ላይ ወደቀች:: አካሉ በሙሉ መሬት ላይ ተበታተነ:: እግዚአብሔር ቅድስት ነፍሱን ተቀብሎ አሳረጋት::

††† ለቅዱሱም 3 አክሊል ከሰማይ ወርዶለታል:-
1.ስለ ፍጹም ምናኔውና ድንግልናው
2.ስለ ሐዋርያዊ የወንጌል አገልግሎቱ
3.ስለ ሃይማኖቱ ደሙን አፍስሷልና
"እምአባልከ ተመቲራ ለእንተ ሠረረት ርዕስ:
እግዚአብሔር አስተቄጸላ በአክሊል ሠላስ" እንዳለ መጽሐፍ::
ምዕመናን ሥጋውን ሰብስበው በዝማሬና በማኅሌት በክብር ቀብረውታል::

††† አምላካችን ከቅዱሱ በረከት ይክፈለን::

††† ሰኔ 6 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ አባ ቴዎድሮስ ሰማዕት
2.አባ ገብረ ክርስቶስ
3."40" ሰማዕታት

††† ወርሐዊ በዓላት
1.ቅድስት ደብረ ቁስቋም
2.አባታችን አዳምና እናታችን ሔዋን
3.አባታችን ኖኅና እናታችን ሐይከል
4.ቅዱስ ኤልያስ ነቢይ
5.ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሣርያ
6.ቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊ
7.ቅድስት ሰሎሜ
8.አባ አርከ ሥሉስ
9.አባ ጽጌ ድንግል
10.ቅድስት አርሴማ ድንግል

††† "መልካሙን ገድል ተጋድያለሁ:: ሩጫውን ጨርሻለሁ:: ሃይማኖቴን ጠብቄአለሁ:: ወደ ፊት የጽድቅ አክሊል ተዘጋጅቶልኛል:: ይህንም ጻድቅ: ፈራጅ የሆነው ጌታ ያን ቀን ለእኔ ያሰረክባል:: ደግሞም መገለጡን ለሚወዱት ሁሉ እንጂ ለእኔ ብቻ አይደለም::" †††
(2ጢሞ. 4:7)

††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††

" ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::  አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/
https://t.me/zikirekdusn
895 views "ወለተ ሥላሴ" "አነ ዘክርስቶስ" , 16:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-16 00:25:31 " አባታችን አቡነ ኪሮስ ሆይ ከዚህ አለም በሞት በተወሰድን ጊዜ ልባችን ዕረፍትን ሲሻ በእቅፍህ ላይ አሳርፈን ።
መልክአ ኪሮስ

አሜን በእውነት
/@Orthodoxtewahdoc
61 views "ወለተ ሥላሴ" "አነ ዘክርስቶስ" , 21:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-16 00:18:31 ✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
"የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል" ምሳ 1፥33
        
✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
ስንክሳር ዘወርኃ ግንቦት /፰/8/

https://t.me/Orthodoxtewahdoc
የያዕቆብ ሌሊት ይሁንልን
81 views "ወለተ ሥላሴ" "አነ ዘክርስቶስ" , edited  21:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ