Get Mystery Box with random crypto!

ቦሌ ኮሚዩኒኬሽን/Bole Communication

የቴሌግራም ቻናል አርማ bolecommunication — ቦሌ ኮሚዩኒኬሽን/Bole Communication
የቴሌግራም ቻናል አርማ bolecommunication — ቦሌ ኮሚዩኒኬሽን/Bole Communication
የሰርጥ አድራሻ: @bolecommunication
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 911

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2023-04-10 23:03:37
“የሰንበት ገበያ-
በቦሌ ክፍለ ከተማ”
ሳምንታዊው የሰንበት ገበያ በቦሌ ክፍለ ከተማ በሚገኙ የገበያ ማዕከላት በዚህም ሳምንት ቀጥሎ በመካሄድ ላይ ነው፡፡
በክፍለ ከተማው በሚገኙት ሁሉም ወረዳዎች የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ ለሸማቹ ኅበረተሰብ እየቀረቡ ሲሆን፣ መጪዎቹን የትንሣኤና የኢድ አልፈጥር በዓላት ታሳቢ ባደረገ መንገድ እስከበዓላቱ መዳረሻ ድረስ አቅርቦቱ የሚቀጥል ይሆናል፡፡ በክፍለ ከተማው ከሆኑ የገበያ ማዕከላት መካከል አማካይ በሆኑት በወረዳ 4 ጎላጉል ሕንፃ አካባቢ፣ በወረዳ 5 ኮከብ ሕንፃ አጠገብና መገናኛ አደባባይ፣ እንዲሁም በወረዳ 7 ጉርድ ሾላና የረር አካባቢ የገበያው እንቅስቃሴው በስፋት ቀጥሏል፡፡
ሚያዚያ 1/2015
166 views20:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-09 16:53:04
የቦሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት በክፍለ ከተማው በ90 ቀናት ዕቅድ ተገንብተው የተጠናቀቁ ፕሮጀክቶችን ጎበኙ።
በቦሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ዓለምጸሐይ ሺፈራው የተመራው የአመራሮች ቡድን በክፍለ ከተማው በሚገኙ ወረዳዎች ግንባታቸው ተጠናቅቆ ለምረቃ ዝግጁ የሆኑ ፕሮጀክቶችን ተዘዋውሮ ጎብኝቷል።
መጋቢት 30/2015
210 views13:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-09 16:43:41
“የወጣቶች ሚና፣
ለሁለንተናዊ ብልጽግና የጎላ ሚና ይጫወታል”
ላለፉት ሦስት ቀናት በቦሌ ክፍለ ከተማ በሚገኙት አሥራ አንዱም ወረዳዎች ሲካሄድ የቆየው የአዲስ ምዕራፍ የወጣቶች ውይይት ተጠናቀቀ፡፡
በብሎክ ደረጃ በተካሄደው ውይይት መድረክ ላይ ወጣቶች ለአገራዊው ለውጥ ትልቅ አስተዋጽኦ ማበርከታቸው የተወሳ ሲሆን፣ ወጣቶች በአገር አቀፍ ደረጃ መንግሥት ያከናወናቸውን ዘርፈ ብዙ ሥራዎችና በጎ ጅምሮችና መልካም ተግባራትን በመገንዘብ ለተግባራቱ ቀጣይነት ድርሻቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ተመልክቷል፡፡ የውይይት መድረኩ በወጣቶች ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ተሳትፎ ዙሪያ ግልጽ ውይይት በማድረግ በቀጣይ ሥራዎች ዙሪያ የጋራ መግባባት የመፍጠር ዓላማ እንዳለው የተገለጸ ሲሆን፣ መሰል ውይይቶች በክፍለ ከተማና በከተማ ደረጃ እንደሚቀጥሉ ለማወቅ ተችሏል፡፡
መጋቢት 30/2015
175 views13:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-09 16:37:41
ቦሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የወሳኝ ኩነት ምዝገባና መረጃ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በ2015 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ግማሽ ባከናወነው የሥራ እንቅስቃሴ የአንደኝነት ደረጃ አገኘ።

ጽ/ቤቱ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ስድስት ወራት ምዘና ከፍተኛ የሥራ አፈጻጸም በማስመዝገቡ ከአሥራ አንዱ ክፍለ ከተሞች የአንደኝነት ደረጃ በማግኘት ተሸላሚ ሆኗል። መጋቢት 30/2015
169 views13:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-05 09:21:44
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ጥራቱ በየነ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 በ90 ቀናት ዕቅድ የተከናወኑ ሥራዎችን ጎበኙ፡፡

በጉብኝቱ በአስተዳደሩ ቅጥር ግቢ የተከናወኑ የምድረ ግቢ ማስዋብ፣ የሕንፃና የቢሮ እድሳት እንዲሁም የአገልግሎት አሰጣጥ ማዘመን ተግባራት ምልከታ የተደረገባቸው ሲሆን፣ የ90 ቀናት ዕቅድ አፈጻጸም በወረዳው ጥሩ መሆኑን የተናገሩት አቶ ጥራቱ፣ ቀሪ ሥራዎች በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲጠናቀቁ የአጭር ጊዜ ዕቅድ አዘጋጅቶ ለአመራሩ የሥራ ክፍፍል በመስጠትና የቅርብ ክትትል በማድረግ ፕሮጀክቶቹ ለአገልግሎት እንዲበቁ ማድረግ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡

መጋቢት 26/2015
24 views06:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-04 17:44:30
106 views14:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-04 17:44:18
106 views14:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-03 18:04:33
የሕዝብን ቅሬታ፣
በተግባር መፍታት!”
በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 ለረዥም ዓመታት ከፍተኛ የሕዝብ ቅሬታ ሲቀርብበት የነበረው የአስተዳደሩ መግቢያ መንገድ በአዲስ መልክ ተገንብቶ ለአገልግሎት ዝግጁ ሆነ።
የወረዳው አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳኜ አስፋው እንደገለጹት ወደ ወረዳው አስተዳደር ቅጥር ግቢ የሚያስገባው መንገድ ለእግረኞችም ሆነ ለተሽከርካሪዎች ምቹ ያልሆነ በመሆኑ ለበርካታ ዓመታት ነዋሪዎች ከፍተኛ ቅሬታ ሲያቀርቡበት የነበረ ሲሆን፣ የወረዳው አስተዳደር ከአዲስ አበባ መንገዶች ባለሥልጣን ጋር በመተባበር መንገዱን በአስፓልት ገንብቶ ለአገልግሎት ዝግጁ እንዲሆን አድርጓል። የመንገዱ መሠራት ለአገልግሎት ፈላጊዎችም ሆኑ የአስተዳደሩ ሠራተኞች ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥር ያስረዱት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፣ የወረዳው አስተዳደር ሌሎችም ቅሬታ የቀረበባቸውን የመልካም አስተዳደር ችግሮች የመፍታት ሥራውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አክለው አስታውቀዋል።
አስተያየታቸውን ለቦሌ ኮሚዩኒኬሽን የሰጡ ተገልጋዮች በበኩላቸው መግቢያው ወደ ወረዳው አስተዳደር ለሚመጡ ተገልጋዮች በተለይም ለአካል ጉዳተኞች በጣም አስቸጋሪ በመሆኑ ወደ ቅጥር ግቢው ገብተው ለመስተናገድ ይቸገሩ እንደነበር አውስተው፣ አሁን ላይ መንገዱ በአዲስ መልክ ተሠርቶ ለአገልግሎት በመብቃቱ ችግራቸው መፈታቱን አመልክተዋል።
መጋቢት 25/2015
94 views15:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-03 15:51:45 የውይይቱ ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት "ሰላም የልማትና የዕድገት መሠረት በመሆኑ ለሰላማችንና ለብልጽግናችን መረጋገጥ እንደትናንቱ ሁሉ ዛሬም ባለቤት ሆነን ድርሻችንን እንወጣለን" ብለዋል። የኑሮ ውድነትና የትራንስፖርት ችግር ለሰላም መደፍረስ መንስኤ ሊሆኑ ስለሚችሉ መንግሥት በትኩረት ሊሠራበት እንደሚገባ ያሳሰቡት ተሳታፊዎቹ፣ በሚዲያዎችና ሌሎች መንገዶች የአገርን ሰላም ለማደፍረስ የሚንቀሳቀሱ አካላትን መላው ኅብረተሰብ ከሰላምና ጸጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት ሴራቸውን ሊያከሽፉ እንደሚገባ አመልክተዋል።
ውይይቱን የመሩት የቦሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ዓለምጸሐይ ሺፈራው የቦሌ ክፍለ ከተማ ነዋሪዎች የአካባቢያቸውን ሰላም በማስጠበቅ፣ በልዩ ልዩ በዓላት አከባበር እንዲሁም በሕልውና ዘመቻው ወቅት በደጀንነት ያበረከቱት አስተዋጽኦ የማይዘነጋ መሆኑን ገልጸው፣ አሁንም ሕዝቡ የሰላም ባለቤት በመሆኑ ለክፍለ ከተማው፣ ለከተማውና ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ ከመንግሥት ጎን በመቆም የማይተካ ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ሕዝብ በአብሮነትና ተከባብሮ በመኖር የካበተ ልምድ እንዳለው ያወሱት የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ መላኩ ታምሩ በበኩላቸው፣ ይህንን እሴት ለመናድ በብሔርና በሃይማኖት የሚከፋፍሉ አካላትን መላው ነዋሪ ኅብረተሰብ እንደአንድ በመቆም ሊመክታቸውና የሰላም ዘብ መሆኑን በተግባር ሊያሳይ እንደሚገባ አሳስበዋል።
መጋቢት 25/2015
119 views12:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-03 15:51:40
"የሰላም ባለቤት የሆነው ሕዝብ፣
ለአብሮነትና ለመከባበር ባሕል መዳበር
ሚናው የጎላ ነው"
የቦሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር "የመከባበርና የአብሮነት ባሕል ለሰላም ግንባታ" በሚል መሪ ቃል ከክፍለ ከተማው ነዋሪ ኅብረተሰብ ጋር ውይይት አካሄደ።
ከሁሉም የክፍለ ከተማው ወረዳዎች የተውጣጡ የኅብረተሰብ ክፍሎች በተሳተፉበት በዚህ ውይይት ላይ በቀረበው ሰነድ እንደተገለጸው ሰላም ለልማት ቅድመ ሁኔታ በመሆኑ ልማትን ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ አብሮነትን በማጠናከር የሰላም ግንባታን ማፋጠን ወሳኝ ተግባር ነው። አሁናዊ የአዲስ አበባ ከተማ የሰላም ሁኔታን በተመለከተ በትምህርት ቤቶች፣ በእምነት ተቋማትና ሌሎች አካባቢዎች ተፈጥረው የነበሩ ችግሮችን ለመፍታት በአስተዳደሩ በርካታ እርምጃዎች መወሰዳቸው የተጠቀሰ ሲሆን፣ እነዚህን ችግሮች ለአፍራሽ ተልዕኮ ለመጠቀም የሚንቀሳቀሱ አካላትን ለመከላከል ኅብረተሰቡ ከጸጥታ አካላት ጋር በመተባበር ከፍተኛ ሚና መጫወቱ በሰነዱ ተመልክቷል።ሁኔታን በተመለከተ በትምህርት ቤቶች፣ በእምነት ተቋማትና ሌሎች አካባቢዎች ተፈጥረው የነበሩ ችግሮችን ለመፍታት በአስተዳደሩ በርካታ እርምጃዎች መወሰዳቸው የተጠቀሰ ሲሆን፣ እነዚህን ችግሮች ለአፍራሽ ተልዕኮ ለመጠቀም የሚንቀሳቀሱ አካላትን ለመከላከል ኅብረተሰቡ ከጸጥታ አካላት ጋር በመተባበር ከፍተኛ ሚና መጫወቱ በሰነዱ ተመልክቷል።
114 views12:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ