2022-09-03 22:34:05
የሸዋፋኖ አሁናዊ መረጃ…!!
"…የሆነው ይሄነው። የሸዋሮቢቱ ከንቲባ ይገደላል። ከምሽቱ 3 ሰዓት ጠጥቶ ሰክሮ ወደቤቱ ሊገባ ሲል ይገደላል። ከመገደሉ በፊት ሰውየው ከግርማ የጂብጥላ መመሪያ እየተቀበለ የሸዋ ፋኖ ላይ ይደነፋ፣ ዐቢይ አሕመድን በሰላማዊ ሰልፍ ላይ ሰደባችሁ ብሎ በጅምላ ያስረሸነ ሰው ነበር። እንዲያም ሆኖ የሸዋ ሮቢት የብልጽግና ኃላፊዎች ከሁለት ተከፍለው መጨቃጨቅ ከጀመሩ እንደሰነበቱ ይነገራል። አንዱ ወደ ኦሮሞ ብልጽግና የሚያደላ ሲሆን ሌላው ደግሞ ብአዴን እንሁን ባይ ነው። ሟቹ ከንቲባ ወላዋይ ነው አሉ። እናም ከመገደሉ በፊት የፖለቲካ ክፍሉ እንደሚገደል መረጃው እንደደረሰው መነገሩ ተሰምቷል። ከዚያ ተገደለ።
"…የከንቲባው መገደል ለእነግርማ የጅብጥላና ታደሰ ገብረጻዲቅ ሰርግና ምላሽ ሆነላቸው። ፈነጠዙ። አሁን ነው የሸዋ ፋኖን መምታት፣ አሁን ነው የሸዋ ፋኖን መበተን ብለው አሰቡ። በዚያውም ለኦነግ ሸኔ መንገድ ለመጥረግ፣ በዚያውም የዐማራ ልዩ ኃይልና ፋኖና ሚኒሻውን እርስ በእርስ ለማገዳደል ቋመጡ። ቋመጡናም የዐማራ ልዩኃይልን ወደ ሸዋሮቢት ላኩት።
"…የሸዋ ፋኖም በግድያው ስለሌበት በከተማው ነበረ። የዐማራ ልዩ ኃይሎች ወደ ከተማዋ እንደገቡ በቀጥታ ወደ ፋኖ አለቆች ቤት አመሩ። በቀን 27/12/2014 ዓ,ም በየፋኖዎቹ ቤት የደረሰው የዐማራ ልዩ ኃይል ተኩስ ከፈተ። ቦንብ ሁላ መወርወር ጀመረ። ከወያኔና ከኦነግ ጋር የሚዋጋ እንጂ ወንድሞቹ ጋር የሚዋጋ አይመስልም ነው የሚሉት ታዛቢዎች። ፋኖዎቹ ዱብ ዕዳ ነው የሆኑባቸው። እንዳይተኩሱ የራሳቸው የዐማራ ኃይል ነው። ዝም እንዳይሉ ጨካኝ ወታደር ነው የመጣባቸው። እንደምንም ለመከላከል ሞከሩ። ነገር ግን ሌሎች ወደ ጫካ ቢያመልጡም ጥቂቶች ግን ቆስለው ታፈኑ። የታፈኑ ፋኖዎችም የሚከተሉት ናቸው።
1፦ ፋኖ ታደለ ወርቁ
2፦ ፋኖ ዮሐንስ
3፦ ፋኖ እንዳለ አረጋሃኝ
4፦ ፋኖ አማኑኤል ሲሆኑ፤ ፋኖ ታደለ ወርቁ በቦንብ ሦስት ቦታ ተመትቶ ከሸዋ ሮቢት ሪፈር ቢባልም የግርማ የሺጥላና የታደሰ ገብረጻዲቅ ህክምና አያስፈልገውም ቀላል ቁስል ነው ብለው ደብረ ብርሃን 1ኛ ፖሊስ ጣቢያ እንዲታሠር መደረጉ ተነግሯል። ፋኖ ዮሐንስ ወገቡ ላይ በጥይት ተመትቶ ደብረ ብርሃን ሆስፒታል በህክምና ላይ ይገኛል።
"…አሁን እነ ግርማ የሺጥላ ፋኖው ከኦነግ ጋር የሚዋጋበትን የጦር መሳሪያ በድንገት ደርሰው ዘርፈውበታል። የተወሰዱ ንብረቶችም አንድ ድሽቃ፣ አንድ መትረየስ፣ ሁለት ጥቁር ክላሽ፣ ሦስት ቦንብ፣ 7000 የመትረየስ ጥይት፣ 3000 የክላሽ ጥይት ወስደውባቸዋል። ልብበሉ ወያኔ ሞላሌ በደረሰች ጊዜ የመሃልሜዳ ህዝብ ከመሃልሜዳ ከተማ ሸሽቶ ሲሄድ ሲሰደድ የግርማ የጂብጥላ ወንድምና ከ4ሴቶች የሚወልዳቸው ልጆቹ ወያኔን ተቀብለው ያስተናገዱ ናቸው። ወያኔ እንደወጣች ግርማ የጂብጥላ ወንድሞቹን የመሃል ሜዳ የጸጥታውና አስተዳዳሪ አድርጎ ሹሟቸዋል። ይሄን ያዙልኝ።
"…እናም ዛሬ በቀን 28/12/201 ግርማ የሺጥላ የዐማራ ልዩ ኃይልንና የፌደራል ፖሊስን አንድ ላይ አቀናጅቶ ወደ ራሳ መስመር ልኳቸው ነበር። የራሳ ፋኖና ገበሬ ተዉ ወንድማማቾች ነን አንዋጋ ብለዋቸውም ነበር። ልዩ ኃይሉ ግን እምቢ ብሎ ከራሳዎች ጋር ጦርነት የከፈተ ሲሆን በጦርነቱም ሁለት ከልዩ ኃይል ሲሰዉ አንድ ከፋኖ ቆስሏል። ከፋኖ የቆሰለው ባዩ የሚባል የፋኖ አባል እንደሆነ አረጋግጫለሁ።
"…በቀጣይ ምንድነው የሚሆነው?
"…ከሸዋሮቢቱ ድንገተኛ የእነ ግርማ የጅብጥላ ወረራ በኋላ በቀጥታ የራሳ ፋኖና ገበሬ፣ የአባያጥር ፋኖና ገበሬ፣ የሸዋሮቢት ፋኖዎች ወደ ጫካ ገብተዋል። ወደ ጫካ የገቡት በሙሉ በዛሬው ዕለት ትግሬ ነው ለሚባለው ለሸዋው አስተዳዳሪ ሽምግልና ልከዋል። የታሰሩት ፋኖዎችና የተዘረፍነው መሣሪያ በአስቸኳይ ይመለስልን በማለት ነበር የላኩት። አይተ ታደሰም እሳት ለብሰው፣ እሳት ጎርሰው 'በሸዋ የታጠቀ ፋኖ አያስፈልግም፣ ገና ሁሉንም እንደመስሳቸዋለን ብለው" ሽማግሌዎቹን መመለሳቸው ተነግሯል።
"…እናንተ ምን አሰባችሁ? ብያቸው ነበር?
"…ሸኔ ከሚገድለን፣ ህወሓት ከምትገድለን እዚሁ ከብአዴን ጋር ተቷክሰን በክብር መሞትን መርጠናል። ሙሉ ሸዋ በቀጣይ ቀናት የሚሆነውን አብረን መጠበቅ ነው። ብለውኛል። ይሄን እያወራን ሳለም አንድ የበጃጅ ሹፌርን የዐማራ ልዩኃይል ልብስ የለበሱት የግርማ የጅብጥላ ሰራዊቶች ተኩሰው መትተውታል። ይሙት ይትረፍ አልታወቀም። የቀረውን እንዲሁ እየተከታተልኩ አሳውቃችኋለሁ።
"…ምነው ሸዋ…!!
86.2K views19:34