2022-09-08 18:20:43
በ2013 ዓም የዛሬ ሁለት ዓመት እንዲህ ብዬ ጽፌ ነበር እስቲ መልሳችሁ አንብቧት። ቆይቼ የአስተያየት መስጫ ሰንዱቁን እከፍትላችኋለሁ።
~ጷጉሜን ፫
የፊደል ገበታ ቀን።
*~★★~*
~ የፊደል ገበታ ያለበት ፎቶ ብቻ ዛሬ ፌስቡክን ተቆጣጥሮት እንዲውል እናድርገው። ማኅበራዊ ሚዲያውን በእሱ እናጥለቅልቀው።
ETHIOPIA | ~ ዛሬ ደግሞ ጳጉሜን 3 ነው። በዚያ ላይ ዓመታዊው የቅዱስ ሩፋኤል ክብረ በዓል ነው። እናም የፊደል ገበታ ቀናችንን ሞቅ ደመቅ አድርገን እያከበርን በዚያውም የቅዱስ ሩፋኤልን በዓል ሰብሰብ ብለን ስንዘክር፣ ስንዘምርም እንውላለን።
•••
የኢትዮጵያ ጌጥ፣ የሀበሻ ሁሉ መኩሪያ ነው ሀ ሁ የፊደል ገበታችን። የኢትዮጵያውያንም። የኤርትራውያንም መኩሪያ ነው የፊደል ገበታችን። ክብርና ምስጋና ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን ይድረሳትና ልጆቿ አበው ብራና ፍቀው፣ ቀለም በጥብጠው፣ አእምሮአቸውን ተጠቅመው ይኸው እኛንም በዓለም ላይ የራሳቸው ፊደል ካላቸው ሀገራት በቀዳሚ ተርታ ላይ እንድንመደብ አደርገው አስቀመጠውናል። ያለ ድጋፍ በራሱ የሚቆም ፊደል ባለቤቶች አድርገው አንደኛ አደረጉን። ክብር ለአባቶቻችን።
•••
ፊደላችን የቀደመ የኢትዮጵያዊነታችንም ሆነ የኦርቶዶክሳዊ ማንነታችን መገለጫችን ነው። የቀደሙቱ አባቶቻችን ፊደልን ፈጥረው፣ አሳድገው፣ አበልጽገውም፣ አስፋፍተው ኢትዮጵያን ሞላዋን አጥለቅልቀዋትም ነው ለእኛ ያስረከቡን። ሀበሻ ሆኖ በኢትዮጵያ ፊደል የማይጠቀምና የማይኮራ ሰው የለም። ሀበሻ ሆኖ በአማርኛና በግዕዝ ፊደላት የሚሸማቀቅ፣ የሚያፍር፣ ካለ እሱ ሶዬ ወይ የባንዳ የልጅ ልጅ ነው ወይም ደግሞ ፀረ ኢትዮጵያ የሆነ የጠላት ቅጥረኛ ነው። እኛ ግን በፊደላችን እንኮራለን። ከፍከፍም እንለን።
•••
ብዙዎች የፊደል ገበታችንን አሳምረው ይጠቀሙበታል። የአማርኛ ቋንቋን ለመቃወም ራሱ እሱኑ የአማርኛ ቋንቋ አሳምረው የሚጠቀሙ ጥቂቶች አይደሉም። የትግሬው ህወሓትም፣ የኦሮሞው ኦነግም ሁሉ እንዲሰማቸው ሲያለቃቅሱ የሚውሉት በሚጠሉት የአማርኛ ቋንቋ ነው። እየጠሉት የፊደል ገበታውን የሚጠቀሙ ሰዎች ደግሞ በጣም ያስቁኛል ያሳዝኑኛልም።… ቆንጅዬ የዐማራ ሚስት በአማርኛ ጀንጅኖ፣ አማላጅ በአማርኛ ልኮ አግብቶ ትዳር መሥርቶ፣ ዐማራዋን ቆንጆ ሚስቱን እሷን ታቅፎ እየተኛ፣ ቆንጅዬ ቆንጅዬ ልጆችን አከታትሎ በላይ በላዪ አስወልዶ እየኖረ ሲነጋለት ጠዋት ሚድያ ላይ ቀርቦ ዐማራንና አማርኛን ሲሳደብ፣ ሲራገም የሚውል ስንትና ስንት ዓይነት ሰው አለ መሰላችሁ።
•••
ለምሳሌ ተመልከት እነ ጃዋር መሀመድ ሀብታምና ታዋቂ የሆኑት አማርኛን አቀላጥፈው በመናገራቸው ነው። መለስ ዜናዊ የሚጠላትን ሃገር ቀጥቅጦ የገዛው በአማርኛ እያወራ ነው። ያውም በሚያፈዝ፣ በሚያደነግዝ ምላሱ ቋንቋውን እየቀሸረ። እነ ጃዋር በአማርኛ ቅኔ ይዘርፋሉ። እነ ፕሮፌሰር ሕዝቅኤል ጋቢሳ፣ እነ ግርማ ጉተማ፣ እነ ፀጋዬ አራርሳ ዐማራንና አማርኛን እየጠሉ፣ እየተጸየፉ አማርኛን ከዐማራው በላይ አቀላጥፈው የሚናገሩ ናቸው። በዚህም ደግሞ ተጠቀሙ እንጂ አልተጎዱም። ነገር ግን ሰዎቹ በተፈጥሮአቸው ምቀኞች ስለሆኑ፣ የበታቸኝነት ስለሚያጠቃቸው የኦሮሞው ህዝብ አማርኛን አውቆና ተምሮ በመላ ሀገሪቱ ተዘዋውሮ በፈለገው የሥራ መስክ ተቀጥሮ እንዳይበላ በካቴና ጭምር አስረውታል። እነሱ ግን እንዳሻቸው ሆነው ይኖራሉ።
… አንድ የኦሮሞ ተወላጅ ከኦሮሚያ ውጪ በመላ ኢትዮጵያ ተዟዙሮ በፈለገበት ሥፍራ ተቀጥሮ ሥራ መሥራት እንዳይችል አድርጎ ነው የትግሬው ገዢ አይተ መለስ ዜናዊ ጠፍሮ ያሰረው። ኦሮሞ በላቲን ቋንቋ እየጻፈ፣ እያወራ፣ እዚያው ክልሉ ውስጥ ታጥሮ እንዲቀመጥ ነው ያደረገው። በምትኩ የትግሬ ልጆች አማርኛ ኤ እያመጡ የኦሮሞ አስተዳዳሪ ሊቀመንበር ሁሉ እንዲሆኑ ነው ያደረጋቸው። እግዚአብሔር ይይለት።
•••
ተወደደም ተጠላም አማርኛ ከኢትዮጵያ አልፎ የአፍሪካ የሥራ ቋንቋ ይሆናል። እኛም ላቲንን ለላቲኖቹ እንመልስና በራሳችን ቋንቋ እንጠቀም። ክብር ለሚገባው ለኢትዮጵያው የፊደል ገበታ መጀመሪያ ራሳችን ክብርን እንስጥ።
ሀ ሁ ሂ ሃ ሄ ህ ሆ
ለ ሉ ሊ ላ ሌ ል ሎ
ሐ ሑ ሒ ሓ ሔ ሕ ሖ
መ ሙ ሚ ማ ሜ ም ሞ
ሠ ሡ ሢ ሣ ሤ ሥ ሦ
ረ ሩ ሪ ራ ሬ ር ሮ
ሰ ሱ ሲ ሳ ሴ ስ ሶ
ሸ ሹ ሺ ሻ ሼ ሽ ሾ
ቀ ቁ ቂ ቃ ቄ ቅ ቆ
በ ቡ ቢ ባ ቤ ብ ቦ
ቨ ቩ ቪ ቫ ቬ ቭ ቮ
ተ ቱ ቲ ታ ቴ ት ቶ
ቸ ቹ ቺ ቻ ቼ ች ቾ
ኀ ኁ ኂ ኃ ኄ ኅ ኆ
ነ ኑ ኒ ና ኔ ን ኖ
ኘ ኙ ኚ ኛ ኜ ኝ ኞ
አ ኡ ኢ ኣ ኤ እ ኦ
ከ ኩ ኪ ካ ኬ ክ ኮ
ኸ ኹ ኺ ኻ ኼ ኽ ኾ
ወ ው ዊ ዋ ዌ ው ዎ
ዐ ዑ ዒ ዓ ዔ ዕ ዖ
ዘ ዙ ዚ ዛ ዜ ዝ ዞ
ዠ ዡ ዢ ዣ ዤ ዥ ዦ
የ ዩ ዪ ያ ዬ ይ ዮ
ደ ዱ ዲ ዳ ዴ ድ ዶ
ጀ ጁ ጂ ጃ ጄ ጅ ጆ
ገ ጉ ጊ ጋ ጌ ግ ጎ
ጠ ጡ ጢ ጣ ጤ ጥ ጦ
ጨ ጩ ጪ ጫ ጬ ጭ ጮ
ጰ ጱ ጲ ጳ ጴ ጵ ጶ
ጸ ጹ ጺ ጻ ጼ ጽ ጾ
ፀ ፁ ፂ ፃ ፄ ፅ ፆ
ፈ ፉ ፊ ፋ ፌ ፍ ፎ
ፐ ፑ ፒ ፓ ፔ ፕ ፖ
•••
ይሄ ነው የእኔ ፊደል። ያልተሠረቀ፣ ያልተበረዘ። የማንነቴ መገለጫ። ወዳጄ የሰው ወርቅ እኮ አያደምቅ ነው ከነ ተረቱ። መኩራትስ በራስ ነው። ማን እንደራስ ወርቅ? ክብር ለአባቶቻችን። ከብር ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን።
•••
¶ድልና ትንሣኤ ለኢትዮጵያ ሀገሬና ለተዋሕዶ ሃይማኖታችን ! ውድቀትና ጥፋት፤ ለሁለቱም ጠላቶች። አራት ነጥብ።
•••
" እኔ ግን እላለሁ! እምዬ ኦርቶዶክስ አንቺ እናትዓለም፤ የእነ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ፣ የእነ ቅዱስ አትናቴዎስ እና ቅዱስ ቄርሎስ የእነ ቅዱስ ጊዮርጊስ፣ የእነ ቅድስት አርሴማ፣ የእነ አቡነ ተክለሃይማኖት፣ የእነ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ፣ የአባ ሳሙኤል ዘዋልድባ፣ የቅድስት ክርስቶስ ሠምራና የአቡነ አረጋዊ ሃይማኖታቸው የሆንሽ ንጽህት፣ ቅድስት፣ ርትዕት ተዋሕዶ ሃይማኖቴ ሆይ! ብረሳሽና ብከዳሽ ቀኜ ትርሳኝ። ትክዳኝም። ባላስብሽና ባልሟገትልሽ ባልሞትልሽም ምላሴ ከጉሮሮዬ ይጣበቅ። ሳለጎበድድና ሳለከዳሽ እንድኖርም አምላክሽ ይርዳኝ። ይህን ባላደርግና ሳልጮህልሽ ዝም ብዬ ብሞት ስሜ ከህይወት መጽሐፍ ይደምሰስ።
"ጌታ ሆይ! ከዚህ በፊት በሆነው፤ አሁንም እየሆነ ባለው እና ወደፊትም በሚሆነው ነገር፤ ክብሩን ሁሉ አንተ ውሰድ።" አሜን !
"ድንግል ሆይ እናቴ ! አዛኝቱ ዛሬም እንደትናንቱ ቅደሚ ከፊት ከኋላዬ "
• ይህንንም ራሴው እኔ ዘመዴ በእጄ ጻፍኩት። +4915215070996 ደግሞ የቴሌግራም፣ የቫይበር፣ የኢሞና የኋትስአፕ መልእክቶችን የምቀበልበት የእጅ ስልኬ ነው።
•••
ሻሎም ! ሰላም !
ዘመድኩን በቀለ ነኝ።
ጷጉሜን 3/2013 ዓም
ከራየን ወንዝ ማዶ።
101.0K viewsedited 15:20