Get Mystery Box with random crypto!

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

የሰርጥ አድራሻ: @zemedkunbekelez
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 398.62K
የሰርጥ መግለጫ

"ይህ የቴሌግራም ቻናሌ ግንቦት1/2011ዓም የተከፈተ ነው። የእኔን የስልክ ወጪ ጨምሮ አገልግሎቴን መደገፍ የምትፈቅዱ ጓደኞቼ በ
👉🏿 https://donorbox.org/zemedemedia እና
👉🏿 https://www.paypal.com/paypalme/ZemedkunB በኩል ማገዝ ትችላላችሁ። በተረፈ ለቤተ ክርስቲያኔና ለኢትዮጵያ ሀገሬ የሚጠቅመውን ሁሉ አበረክት ዘንድ አብዝታችሁ ጸልዩልኝ።

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 264

2022-09-26 18:46:20
አዲስ አበባ – ኢትዮጵያ…!!

"…ዛሬ በደመራው በዓል ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ሰንበት ተማሪዎች ከምር አሰለቀሱኝ። ብቻዬን ነው መርዶ እንደሰማ ሰው ስቅስቅ ብዬ እንዳለቀስ ያደረጉኝ። የደስታ ልቅሶ። የደስታ እንባ። አባቴም እናቴም ሞተው በዚህ መጠን አላለቀስኩም። ከምር ተባረኩልኝ። የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን የተዋሕዶ አምላክ ብድራቱን ይክፈላችሁ።

"…ልዕልት ዕሌኒ ቅዱስ መስቀሉን ከተቀበረበት ሥፍራ ቆፍራ እንዳወጣችው ነው እናንተም ዛሬ የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ከተቀበረበት ሥፍራ አውጥታችሁ በኦነጉ የኢትዮጵያ ሚንስትር በቀጄላ ፊት ያውለበለባችሁት። የብልጽግናው መንግሥት የኦሮሙማ ወታደሮች ህዝቡን በሃገሩ ሰንደቅ ዓላማ እንዳያጌጥ ቢያደርጉትም፣ ቲሸርት ሳይቀር አውልቅ ብለው ቢያስጨንቁትም። ከዐውደ ምህረቱ ላይ ሰንደቋን እንዳትታይ ቢያደርጓትም እናንተ ግን በጥብዓት ገለጣችኋት። በቀጄላ መርዳሳ፣ በቅርቡ በዐቢይ አህመድ ሚስት በጎንደሬዋ ዝናሽ ታያቸው ጎትጓችነት ጴንጤ በሆነችውና ከጥብቅ ኦርቶዶክሳዊ ቤተሰቦች በተገኘችው በአዳነች አበቤ ፊት ለፊት ኢትዮጵያን ገለጣችኋት።

"…ኡፍፍፍ እንዴት ብዬ ደስታዬን ልግለጠው? ቃላቶች ሁላ ሽባ ሆኑብኝ። ከኃጢአት የራቀ ረጅም የአገልግሎት ዘመን ይስጣችሁ። ዕድሜ፣ ጤና፣ ሃብቱን አንዱም ሳይጎድል እግዚአብሔር ይስጣችሁ። ሰላማዊቷ ተዋሕዶም የደመራ በዓሏን በመላው ኢትዮጵያ በሰላም ማክበሯን እንደቀጠለች ነው።

"…አዛኜን እውነቴን ነው ኢትዮጵያማ ትነሣለች።
43.8K views15:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-26 12:17:05
እግዚአብሔር ይመስገን…?

"…የመስቀል ደመራ ክብረ በዓል ዝግጅት በኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ታጅቦ እንዲህ ባለ ደማቅ ድባብ በጉራጌ ዞን ባሉ ወረዳዎች በሙሉ ሊከበር በዝግጅት ላይ መሆናቸው ተነግሯል። Kune Demelash kassaye -Arba Minch እንደዘገበው።

"…ሌሎቻችሁስ…?
12.0K views09:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-26 11:44:16
ተወዳጆች ሆይ…!!

"…እናንት ባለ ማዕተቦች፣ የጥንታዊቷ፣ ሐዋርያዊቷ እና ብሔራዊቷ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ልጆች ሆይ…!! በእልፍ መከራ ውስጥም ቢሆን፣ በድቅድቅ ጨለማ፣ በውቅያኖስ ማዕበልና ሞገድ ወጀብም መሃል እያለፋችሁም እንኳ ቢሆን መከራ ሰቀቀኑን ሁሉ የምትችሉበት ሰፊ ትከሻ ሰጥቷችሁ እንኳን ለ2015 ዓም ለብርሃነ መስቀሉ የደመራ በዓል በሰላም፣ በጤና፣ በፍቅር እና በአንድነት አደረሰን አደረሳችሁ። አሜን…!!

"…ከዚህ በመቀጠል የዛሬውን የደመራ በዓል በተመለከተ ከየስፍራው የሚደርሱኝን አጫጭር መረጃዎችን ወደ እናንተ ሳደርስ አመሻለሁ። እናንተም በአካባቢያችሁ። በአጥቢያችሁ የምታዩትን መንፈሳዊ ትርኢትም ሆነ የተለየ መረጃ ስታገኙ ላኩልኝ።

"…ቆይቼ ደግሞ ጉዞ ወደ መስቀል አደባባይ ሲጀመር የቴሌግራም ቻናሌን የአስተያየት መስጫ የፎቶ፣ የድምፅ እና የቪድዮ መላኪያ ሰንዱቁን እከፍትላችኋለሁ።

"…ኦርቶዶክሳውያን ሰላማውያን ናቸው። ታርደው እንኳ የማያንጎራጉሩ ሰላማውያን። ሰላም ማለት እራሱ ኦርቶዶክስ ማለት ነው። የሰላም ባለቤት የሰላማዊው ኢየሱስ ክርስቶስ አማኞች የተዋሕዶ ልጆች ውብ የሆነውን የአደባባይ በዓላቸውን በሰላማዊ ሁኔታ ያከብሩታል። እናም ለሰላሙ፣ በዓሉ በሰላም እንዲያልፍ ሁላችንም አሻራችንን እናሳርፍ።

"…ማስታወሻ… !!

• በኦሮሚያ የምትገኙ ኦርቶዶክሳውያን የተዋሕዶ ልጆች በሙሉ። ምንአልባት የክልሉ መንግሥት ሹመኞች አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ሰንደቅ ዓላማ ማየት አንፈልግም ያለበለዚያ እናርዳችኋለን ሊሏችሁ ይችላሉ። ከመስቀል በዓል በኋላ ለሚመጣው ለእሬቻው መስዋዕት ሊያደርጓችሁ ስለሚፈልጉ " ጊዜው እስኪያልፍ" ጥንቃቄ ብታደርጉ መልካም ነው ብዬ እመክራለሁ። ያልፋል። የማያልፍ ነገር የለም። ግን መዝግቡት።

"…ቆይቼ እመለሳለሁ…!!
18.2K viewsedited  08:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-25 19:37:25
… ነጭ ነጯን ከዘመዴ ጋር …!!

• https://rumble.com/v1lh4m5--september-25-2022.html

"… ዛሬ ከምሽቱ 2:00 ሰዓት ጀምሮ በመረጃ የሳታላይት ቴሌቭዥን በኩል የሚተላለፈው ሳምንታዊው መደበኛ መርሀ ግብራችን ልክ በሰዓቱ ይጀምራል።በ https://mereja.tv ዌብሳይታችን ላይም ተከተሉን።

• በዛሬው መርሀ ግብራችንም እንደተለመደው ነጭ ነጯን እውነት እውነቷን፣ ሃቅ ሃቋን፣ እንቅጭ እንቅጯን ብቻ እናወጋለን። ዛሬ የማንዳስሰው ነገር የለም።

• ጌዜ ሰዓት ከተረፈን ትደውላላችሁ…  በጨዋ ደንብ እንወያያለን…!!

• በተረፈ የእኔን የስልክ ወጪን ጨምሮ አገልግሎቴን ለመደገፍ፦
https://donorbox.org/zemedemedia
https://www.paypal.com/paypalme/ZemedkunB በኩል መለገስ ትችላላችሁ። ተመስግናችኋል።

"… ሰብሰብ ብላችሁ እየተወያያችሁ ጠብቁኝማ። ኣ

"… ሻሎም !  ሰላም !
43.9K views16:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-25 13:29:19
"…አትደነቅ፣ አትገረም፣ ወቾ ጉድ ብለህ አትደመም። ይሄ ከዘመኑ ነው። ዘመን ያመጣው ጣጣ ነው። በምድራችን ላይ በዚህ ዘመን ያልተለወጠ ነገር የለም። ገናም ከዚህ የባሰ ብዙ ነገር እናያለን። እናም ብዙም አይግረመን ለማለት ነው። አይጦች ድመትን መፍራት ያቆሙበት ዘመን ነው ብለህ አትገረም ወዳጄ። ዘመኑ ነው። በአይጦች ዘመን ድመት ፈሪ ነው።

"…ለማንኛው ዛሬ ማታ ምሽት ሁለት ሰዓት ላይ እግዚአብሔር ቢፈቅድ ከረጅም ጊዜ ቆይታ በኋላ "ነጭ ነጯን ከዘመዴ ጋር " የሚለውን መርሀ ግብሬን ይዤ በመረጃ ቴቪ የቀጥታ ስርጭት ወደ እናንተ ብቅ እላለሁ ብዬ ወስኛለሁ። ከሃገረ አማሪካ ጋዜጠኛ ኤልያስ ክፍሌ ቴክኒኩን ይመራዋል። ከሃገረ ጀርመን ከራየን ወንዝ ማዶ እኔ ዘመዳችሁ ብቅ ብዬ ነጭነጯን እግታችኋለሁ። ምሽት ፪ ሰዓት ያገናኘን።

"…ሻሎም…! ሰላም…!
45.4K viewsedited  10:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-24 23:35:22
የክብርት ፕሬዘዳንታችን ጉዳይ…!!

"…ክብርት ፕሬዘዳንታችን ሳህለወርቅ ዘውዴ በንግሥት ኤልሳቤጥ የቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ ክብርት ፕሬዘዳንታችን ፈጸሙ ተብሎ በማኅበራዊ ሚዲያው ላይ ሲመላለስ የነበረውና ክብርቷም ተናገሩት ተብሎ አየሩን ሁሉ አጨናንቆ ይዞ የነበረው ጉዳይ ትክክል እንደይደለ ታውቋል። ሁኔታው ለሰሚውም ደስስ ይላል። "በተለይ ይሄ ክብርም ለእኛ ይገባናል፣ ኤምባሲዬ በሚያዘጋጀው መኪና በራሴ መንገድ ወደ ቀብር ሥርዓቱ እሄዳለሁ በማለት ተናገሩ። ያሉትም ተፈጽሞላቸው በሥርዓተ ቀብሩ ላይ በራሳቸው ፕሮቶኮል ተገኝተዋል መባልን ለሚሰማ አፍሪካዊም፣ ኢትዮጵያዊም ሰው የሚሰማው ስሜት ደስታውም ጭምር እጅግ ወደር የሌለው የኩራት ስሜት እንደሚሳም ይታወቃል።

"…ክብርት ፕሬዘዳንታችን እንዲህ በማለታቸው ምክንያት ሌሎች በአውቶቡስ ሄዱ የተባሉ የአፍሪካ መሪዎች በመላ አፍሪካውያን ዘንድ ሲሰደቡም ከርመዋል። ሆኖም ግን ነገሩ ወዲህ ነው። ክብርት ፕሬዘዳንታችንም ከሌሎቹ የተለየ የፈጸሙት የተለየ ጀብድ የለም። እርሳቸውም ልክ እንደሌሎቹ የአፍሪካ መሪዎች በቀረበላቸው አውቶቡስ ተራቸውን ጠብቀው፣ በሥነሥርዓት ተሰልፈው፣ ተሳፍረውም ወደ ቀብር ሥርዓቱ በመሄድ ሟች ንግሥት ኤልሳቤጥን አፈር አልብሰው፣ እርማቸውንም አውጥተው በሰላም በመጡበት አውቶቡስ ከሌሎቹ የአፍሪካ፣ የቻይና ተወካይ እና ከካናዳው መሪ ጋር ተሳፍረው አብረው እያወጉ መመለሳቸው ነው የተነገረው። እርግጥ ነው ይሄ ማታ ላይ አሁን የመጣው ዜና ይደብራል፣ የሞቀ ስሜት ላይም በረዶ ቀዝቃዛ ውኃም ይቸልሳል። ነገር ግን የሆነው ይሄው ነው ነው የሚለው ወንድሜ ጴጥሮስ አሸናፊ።

"…ደኅና እደሩልኝ…!!
9.7K viewsedited  20:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-24 20:01:58
"…ባለፈው በወርሀ ነሐሴ በሰሜን ወሎ በተለይ በቅዱስ ላሊበላ ገዳምና በአካባቢው የልማት ጉዳይ ላይ ይመካከሩ ዘንድ ከሃገረ ስዊድን ጥሪ ተደርጎላቸው በስዊድን ሃገረ ስብከት ሊቀጳጳስ በአረጋዊው በብፁዕ አቡነ ኤልያስ እምቢተኝነት ምክንያት ከጉባኤው ተስተጓጉለው የቀሩት ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ ዛሬ በሃገረ ኢትዮጵያ በባህርዳር ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬታቸውን ተቀብለዋል። ደስ ይላል።

"…ብፁዕ አቡነ ኤርሚያስ ባህር ዳር ከተማ ሲገቡ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ አብርሃም፣ የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ፍሬው ተገኘ፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችም ከአየር ማረፊያው ጀምሮ ለብፁዕነታቸው አቀባበል አድርገውላቸዋል።

"…ሽልማቱ እንዳለ ሆኖ ነገርየው ስለተደጋገመ እኔ ግን ጥያቄ ላነሣ ነኝ። ሽልማቱ ለኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን አባት የተበረከተ መሆኑ ሃቅ ነው። ሃገሪቱም ታላቋ ኢትዮጵያ፣ ሸላሚዎቹም የኢትዮጵያ ምሁራን፣ ክልሉም የዐማራ ክልል ነው። እናም ይሄን ግዙፍ የሆነ ሽልማት ታላቅ ለሆነችው ቤተ ክርስቲያን አባት ሲሸልሙ በሥፍራው የታላቋ ሃገር የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ በግልፅ እንዳይኖር የተደረገው ምን ታስቦ ነው? ያውም በልቅሶና ሠርጉ ላይ ባንዲራ በማይለየው በዐማራ ክልል። ኦሮሚያ ቢሆን እንኳን እሺ ፈርተው ነው ይባላል። በየትኛውም ዓለም እንዲህ ባለ ከፍ ያለ ሥነ ሥርዓት ላይ የሃገር ባንዲራ በክብር ነው የሚገለጸው። በኢትዮጵያ ግን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የወያኔን የክልል የሽንት ጨርቆች በማጉላት የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ከካሜራ እይታ ለማራቅ የመጋጋጥ ነገር እየተስተዋለ ነው። ልክ እንደ ኦሮሚያ ክልል በየሥፍራው የአርጀንቲናን ባንዲራ መዋቢያ ማድረጉስ ምን የሚሉት ፈሊጥ ነው?

• ይቅርታ ስላልገብቶኝ ነው።
44.4K views17:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-24 16:33:08
"…መጀመሪያ ወደ ጥያቄ ከመገባቴ በፊት የአዲስ አበባ ክለቦች ብዛት ስንት ናቸው? እሱን መልሱልኝ።

"…ቀጥሎ ወደ ጥያቄዬ ልግባ። ትናንት የአ/አ ከተማ ዋንጫ የጥሎ ማለፍ ውድድር ተካሂዶ ነበር። በክብር እንግድነትም የአሩሲዋ እመቤት የከተማዋ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አበቤም ተገኝታ ነበር። መገኘቷ ባልከፋ ነበር። የሚገርመው ነገር ለቡናና ጊዮርጊስ ክለቦች የዋንጫ ጨዋታ ላይደለ ለጥሎ ማለፍ ለሚጫወቱ ክለቦች የ20 ሚልዮን ብር ቼክ በከተማ አስተዳደሩ ስም መዥረጥ አድርጋ መስጠቷን ማወጇ ነበር።

"…ቆይ ግን ሴትየዋን እንዲህ በህዝብ ገንዘብ ላይ ወሳኝ ሰው። ደግ ደግ፣ ጻድቅ ጻድቅ፣ ቸርቸር የሚያጫውታት በምን አግባብ ነው? ክለቦቹ ገቢም ስፖንሰርም አላቸው። አንድ ተጫዋች ለማስፈረም ብቻ በሚሊዮን የሚቆጠር በጀት በጅተው የሚንቀሳቀሱ ናቸው። በብር መክፈል ብቻ ሳይሆን በዶላር የሚከፍሉት አሰልጣኝና ተጫዋች የመቅጠር አቅምም ያላቸው ክለቦች ናቸው። እናሳ ዛዲያ ምን ዓይነት ሕግና ደንብ ቢኖር ነው ለጥሎ ማለፍ ለሚጋጠሙ ክለቦችን 20 ሚልዮን ብር የህዝብ ገንዘብ መዥረጥ አድርገው እንዲሰጡ መብት የሚሰጣቸው?

"…ለዋንጫ ያለፈው የመቻል ክለብስ? ከመቻል ጋር ተጋጥሞ እንደ ቡና የወደቀው ክለብስ? እነሱስ ሽልማት ስጦታው አይገባቸውምን? እንደምንሰማው ከሆነ መቻል አኩርፎ፣ ለዋንጫም አልጫወትም ብሎ በስንት ውይይት ነው አሉ ፈቃደኛ የሆነው። ምን ጉድ ነው የገጠመን ግን?

"…ግን ለመሆኑ የከተማ አስተዳደሩ ካቢኔ ይሄን ጉዳይ ያውቀዋልን? በምን የሕግ አግባብ ነው ሴትየዋ በደረሰችበት ሁሉ ሚልዮን ብሮችን የሀዘን ቤት ንፍሮ ይመስል ያዙ እያለች የምታዘግነው። የዐማራ ገበሬ፣ ጥምር ጦሩ በነፍሱ ይጋደላል እዚህ ደግሞ የካድሬ ቅንጡ ለቅሪላ ገፊ 20 ሚልዮን ይበትናል። ዘረኛ በለኝ አሉህ ደግሞ።

•ኧረ በሕግ አምላክ…!
58.7K views13:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-24 15:19:17
ጥያቄ ነው…?

"…ቆይ ግን ይህቺ ኢትዮጵያ የምንላት ጥንታዊት ሃገር የምስኪኑ ዐማራ ብቻ ዕዳ ናት ወይ? አልገባኝም። …ዐማራው ከጥንት ጀምሮ ለዚህች ታላቅ ሃገር ህይወቱን፣ ሃብቱን፣ አካሉንና ንብረቱን እንዲህ እየገበረ ማቆየቱ ይታወቃል። አሁንም እየገበረ ነው። ቆይ እሱ ዐማራው ከሌላው ኢትዮጵያዊ የተለየ ከኢትዮጵያ የሚያገኘው ጥቅም አለ ወይ? ለምንድነው የሌላው ክልል ህዝብ ከዚህ ሃገር ወዳድ ህዝብ ጎን የማይቆመው? እስከመቼስ ድረስ ነው ይሄ ህዝብ እንዲህ ሆኖ በዚህ መንገድ የሚዘልቀው?

"…ደጀን ህዝብ ማለት ይሄ ነው። ወተት፣ እንቁላል፣ ዶሮ፣ እንጀራ፣ አምባሻ፣ ዳቦ፣ እርጎ ሳይቀር ለጥምር ጦሩ የሚያቀርብ ምስኪን ደግ ህዝብ። ይህን በማድረጉ ግብር አይቀርለት፣ ማዳበሪያ አይቀንስለት፣ የተለየ ጥቅም የለውም። ግን እስከመቼ ነው ይሄ ምስኪን ህዝብ እንዲህ እየሆነ የሚኖረው?

"…ህወሓት ስትወረው ከጨው እስከ ቡሃቃ ሊጥ ዘርፋ ሙልጩን ታወጣዋለች። ከብቱን፣ ዛፉን ሳይቀር ጨፍጭፋው ትሄዳለች። እስከዚያው እሷ እስክት መጣና እስክታዋርደው ድረስ ደግሞ የሀገር መከላከያ ሠራዊት የጥምር ጦሩ፣ የዐማራ ልዩ ኃይል፣ የዐማራ ሚኒሻንና አንዳንዴም የዐማራ ፋኖን ቀጥ አድርጎ ሲቀልብ ይኖራል? የእግዚአብሔር በረከት የማይለየው ህዝብ ስለሆነ ነው እንጂ ይሄ መንግሥት ያቃተውን ኃይል የዐማራው ገበሬ ራሱንም ቀልቦ፣ የሃገሪቱንም መከላከያ ኃይል ቀልቦ እንዴት ይዘልቀዋል? መቼም ይሄ ነገር በራስ ተነሳሽነትና በበጎ ፈቃዱ እንጂ በብአዴን ካድሬ ትእዛዝ እና ግዳጅ እንደማይሆን ተስፋ አደርጋለሁ። ሃገር ስትኖር ነው ሁላችንም የምንኖረው የምንል ከሆነ እየተጋገዝን። ወያኔ ዐማራን እና አፋርን ብታልፍ ዥለጣዋ ለአንተም ይቀርልህ መስሎህ ከሆነ ተሳስተሃል።

• ኧረ ጎበዝ እየተጋገዝን…?
59.8K views12:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-24 13:06:26 ከላይኛው የቀጠለ…

ለመደገፍ እምብዛም አጋዥ ለመሆን ፈቃደኞች አይደሉም። በሀገር ማኩረፍ ልክም ተገቢም ባይሆን ነገር ግን ደግሞ የወያኔን ሕገ መንግሥት ታቅፎ ወያኔን እዋጋለሁ ለሚል አገዛዝ ምን ተብሎ ይደገፋል። እኔ በዳያስጶራውም አልፈርድበትም።

"…ብድርም፣ እርዳታም ያጣው የሰባኪው የዐቢይ አሕመድ መንግሥት አሁንም በሰፊው የብር ህትመቱ ላይ ቀጥሏል። ብር ሲታተም ደግሞ ብር ወደ ወረቀትነት ክብር ይወርዳል። ብርን ያስከበረው እንደወረቀትም እንዳይቆጠር፣ ዋጋና ክብር እንዲኖረው ያደረገው እኮ ኢኮኖሚው በሚፈቅደው መልኩ ሥራ ላይ መዋሉ ነው እንጂ ሲጠርርብህ ሩጠህ ብር ማተሙ እኮ አይደለም። ባለሙያዎች እንደሚናገሩት ”የብር የመግዛት አቅም አንሷል የምንለው በጥቁር ገበያ እና በባንኮች የብር ምንዛሬ መካከል የሰፋ ልዩነት ሲታይ ነው። ይህ የሚያሳየው ደግሞ በገበያ ውስጥ ያለው የውጭ ምንዛሪ ፍላጎትና አቅርቦት ከፍተኛ አለመመጣጠን ስለሚታይበት ነው” በማለት ያስረዳሉ።

"…ለዚህ ነው አንድ ዶላር አንድ መቶ ብር፣ አንድ የኩዌት ዲናር ደግሞ ሦስት መቶ ስምንት ብር እየተመነዘረ የሚገኘው። የፓውንድ፣ የዩሮ ምንዛሪ ስንት እንደሆነ አላወቅኩም። ይሄ ከባድ አደጋ ነው። ብር መታተሙን የምታውቁት ከንቲባ ወሮ አዳነች አቤቤ በየዕለቱ በየደረሰችበት ሥፍራ ሁሉ፣ የእናቷ ቆሎ ይመስል ከመንግሥት ካዝና እየዘገነች በየዕለቱ ሰጠሁ፣ ለገስኩ የምትለውን ሚልዮን ብሮች ማየቱ በቂ ምስክር ነው። የድግስ ስሟ ተቀይሮም "ማዕድ ማጋራት" የሚል የዳቦ ስም ተሰጥቷታል። የትኛውም የብልጽግና ስብሰባ "ካለ ማዕድ ማጋራት" ማከናወን አይቻልም። የራበው ካድሬ በሙሉ ካልበላ እንዴት ይሰብሰብ ብላችሁ ነው። የሆድ ጥያቄ ሚኒስትሮቹም ዘንድ በኃይለኛው አለ ማለት ነው። አዲስ አበባ ነዳጅ አታፈልቅም፣ ወርቅ አታመርትም ነገር ግን በዘመነ ታከለ ኡማና በዘመነ አዳነች አበቤ የከተማ አስተዳደሩ በዓለም ላይ ታይቶና ተሰምቶ በማይታወቅ መልኩ የማያልቅ ሚልዮን ብሮችን ሲበትንና የሌለ ለጋስ ሲሆን ይታያል። አይገርምላችሁም…?

"…የቀረው ቀርቶ፣ ሌላውን ሳንቆጥር በትናንቱ የቅዱስ ጊዮርጊስና፣ የኢትዮጵያ ቡና የቅሪላ ማልፋት መርሀ ግብር ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት ከንቲባ አዳነች አቤቤ እንደ ሌሎቹ የክብር እንግዶች ጨዋታውን ተከታትለው ዝም ብለው አልወጡም። ለሁለቱ ክለቦች 10 ሚልየን ብር ለግሰው፣ አስጨብጭበው ነው የወጡት። ገና እነ መድህን፣ ባንክ፣ መቻል፣ ሌሎቹም የአዲስ አበባ ክለቦች ልገሳውን ይጠብቃሉ ማለት ነው። እነ ኤልፓም ዝም አይሉም። ይሄ ነው እንግዲህ ሃገር መምራት። አስቂኝም፣ አሳዛኝም የሚያደርገው። ወታደሩ ባዶ ሆዱን ይሰዋል፣ አካሉ ይጎድላል ለፊርማ በሚልዮን የሚቆጠር ብር ተቀብሎ ቅሪላ ለሚያለፋ ጎረምሳ 20 ሚልዮን ብር ዘግና ትሰጣለች። ትንሽ እንኳ እኮ አይሸክካትም።

"…በዚሁ ከቀጠልን ብር ወረቀት ይሆናል። ክብሩን ያጣል። ነዳጅ ለመግዛት አቅም ያንሳል። ነዳጅ ከሌለ ደግሞ ምንም አይኖርም። ለግብርና ግብአት፣ ለጤና፣ ለመሠረተ ልማት የሚያስፈልጉ ግብአቶችን ማስገባት ያቅታል። 120 ሚልዮን ህዝብ መመገብ ያቅታል። አምራቹ ገበሬ ከሞተ፣ ከተፈናቀለ፣ ከተሰደደ ህንፃው ምግብ አይሆንም። ድንጋይ አትበላም። እርስ በራስህ ትበላላታለህ እንጂ። ለዐማራ ያላመረተውን እህል ይሰፍርበት ዘንድ ጣሳ እያደልክ ለኦሮሞ ትራክተርና የውኃ መሳቢያ ሞተር ስላደልክ ይሄን ክፉ ዘመን አትሻገረውም። ነገሩ ከባድ ነው። ቆም ብሎ ማሰብ፣ ካድሬን አስወግዶ ባለሙያ መመደብና ከዚህ ጭንቅ የሚወጣበትን መፍትሄ ለማምጣት ሥራ መጀመር ይሻላል ባይ ነኝ።

"…ትናንት ቢጨንቀው የኢትዮጵያ መንግሥት የፌደራር መንግሥት የሴት ሚኒስትሮች የእርሻ ማሳ ጎበኙ የሚል ዜና ይዞ ወጥቶ ሲያሯሩጥ አየሁ። https://www.facebook.com/123960474361367/posts/pfbid02XitfwWo2UQqm7YG9jFoC8qw5UVGxbJgCgzZii1772GQKCDnoP6eutzrz83vTyNXWl/ ወለጋ እኮ ምርት የለም። ሰሜን ጎንደር፣ ዋግኽምራ፣ ሰሜን ወሎ ምርት የለም። እዚህ ደብረዘይት እና አሩሲ ላይ ድሮም ጥንትም የነበረ የኖረ እርሻ እየጎበኙ፣ ፎቶም እየተነሡ ራስን ማታለል ሞኝነት ነው። ሴት ሚኒስትሮቹ እርሻውን ስለጎበኙ እኮ ምርቱ አይጨምርም። እንደው ቢጨንቅ፣ ግራ ቢገባቸው እኮ ነው።

"…በኢትዮጵያ የሥራ መነሻ ደሞዝ 2,500 ነው ይባላል። የቤት ኪራይ መነሻ ዋጋ ደግሞ 4,500 ነው። ተመልከቱ ሁለት ልጅ ያለው አይደለም አንድ ብቻውን የሚኖር ወንደላጤ እንኳ እንዴት ነው ኑሮን የሚዘልቀው? የምግብ ዋጋ ስንት ነው? ዳቦ እንኳ በአቅሟ ስንት ነው የገባችው? ህክምናን ትታችሁ የትራንስፖርት፣ የልጆች ወጪ ሲጨመርበት ደግሞ አስቡት። ብዙ የመንግሥት ሠራተኞች ምሳ መብላት እንዳቆሙ እየሰማን እኮ ነው። ባዶ ሆዱን አንጀቱን ቋጥሮ የመጣው ሰውዬ ያለ ጉቦ፣ የለ እጅ መንሻ አልሠራም ቢል ምን ትፈርዱበታላችሁ? ነገርየው ከባድ ነው።

"…ለምሳሌ የአዲስ አበባ ፖሊስ አባላትን ጉዳይ እዚህ ላይ ላንሣ። የአሩሲዋ እመቤት ከንቲባ አዳነች አበቤ ለመንግሥት ሠራተኞች የቤት ክራይ ድጎማ አድርጋለች። ይሄ ድጎማ ግን የአዲስ አበባን ፖሊስን ለይታ ተወችው። አሁን ፖሊስ ነፍሴ ችግር ላይ ነው። የአዲስ አበባ ፖሊስ የሆነ ሰው መልቀቂያ ከተከለከለ 5 ዓመት አለፈው። መልቀቅ አይችልም። በዚህ ባለው ደሞዝ ደግሞ መኖር ከብዶታል። በተለይ አባላቱ ላይ የከፋ ነው ተብሏል። ሁሌ እስታንድ ባይ ብለው ያለ እረፍት ነው የሚያሠሩት። በእንዲህ ዓይነት ሰቀቀን መኖር ከጀመሩ ድፍን ሁለት ዓመት እንዳለፋቸው ይናገራሉ። መኖር አቃተን፣ ኑሮውን መቋቋም አልቻልንም ነው የሚሉት። ቢያንስ መልቀቂያ የሚከለክል ሕግ በሌለበት ሃገር መልቀቂያ ተከልክለን እየተሰቃየን ነው ያለነው ነው የሚሉት። የአዲስ አበባ ፖሊስ ሆነው የመብት ጥያቄ የሚያነሡ በሙሉ ታፔላ ተለጥፎባቸው ይታሰራሉ። ይሄ አደጋ አለው።

"…ፖሊስ እየራበው አይሠራም። የሚሠርቅ፣ የሚዘርፍ ቡድን የቋቁማል። ከዚያ በሬህን ከሠረቀህ ጋር ለፍለጋ ስትሯሯጥ ትኖራለህ። በትግሬዎች መታሰር የከበሩ መርማሪ ፖሊሶች፣ የጣቢያ ኃላፊዎች የትየለሌ ናቸው ይባላል። ትግሬዎቹ ገንዘብ አላቸው ተብሎ ስለሚታሰብ ስንቱን ምስኪን ጁንታ ነህ ብለው አስረው በአፅሙ አስቀርተውታል። ብር ሲጠርራቸው ትግሬ እየፈለጉ ልናስርህ ነው ብለው ስንቱን ትግሬ ባዶ ኪሱን አስቀርተውታል። እናም ፖሊስ ራበኝ ሲል አደጋ አለው። የዛሬውን የኢቢሲ ዘገባ ተመልከቱ። በኦሮሚያ ታርጋ መዝረፍ ቀላል ነው። https://www.facebook.com/541629952535552/posts/pfbid0zcQtRbfmBkRdt497aG6uQag45VQ5mmYXzpZCiP7KBTy3xo5QAqj9ALuBA334zkHil/

"…በጎንደር፣ በባህርዳር፣ በደብረ ታቦር፣ በወልድያ፣ በደሴ፣ በአዲስ አበባ የተከማቸው ቁስለኛ ወታደርም እየቆየ ሲሄድ አደጋ መፍጠሩ አይቀርም። የመድኃኒት ወጪውም ከባድ ነው። ቤተሰብም ደሞዝ ይጠብቃል። የጡረታ ገንዘብም ይፈልጋል። እናም ሌላ አድቫንቴጅ እያሰቡ፣ ሰሜኑን በማድቀቅ ሽባ የሆነች ኢትዮጵያን እንዳሻን እንገዛለን ብሎ የሌለ የሴራ መንገድ ከመከተል ጦርነቱን በጊዜ አጠቃልሎ የተረጋጋ ኢኮኖሚና ሃገር ወደመፍጠሩ መሄዱ ይበጃል ባይ ነኝ።

"…ቆይቼ ደግሞ እመለሳለሁ።
12.9K viewsedited  10:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ