Get Mystery Box with random crypto!

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

የሰርጥ አድራሻ: @zemedkunbekelez
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 398.62K
የሰርጥ መግለጫ

"ይህ የቴሌግራም ቻናሌ ግንቦት1/2011ዓም የተከፈተ ነው። የእኔን የስልክ ወጪ ጨምሮ አገልግሎቴን መደገፍ የምትፈቅዱ ጓደኞቼ በ
👉🏿 https://donorbox.org/zemedemedia እና
👉🏿 https://www.paypal.com/paypalme/ZemedkunB በኩል ማገዝ ትችላላችሁ። በተረፈ ለቤተ ክርስቲያኔና ለኢትዮጵያ ሀገሬ የሚጠቅመውን ሁሉ አበረክት ዘንድ አብዝታችሁ ጸልዩልኝ።

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 265

2022-09-24 13:05:49 "…ትናንት ከሰዓት በኋላ ላይ በሃገረ ኩዌት በሥራ ላይ ያለች አንዲት አብሮአደግ እህቴ ትደውልልኛለች። የተለመደውን የቤተሰብ ጉዳይ አወጋን። ሴቷ ፌስቡክም፣ ቴሌግራምም የምትከታተል አይደለችም። ለሃገሪቱም የፖለቲካ ጉዳይ ባዳ ናት። ሲጀመርም መስማትም፣ ማየትም የማትፈልግ ዳተኛም፣ ቸልተኛም እህት ናት።

"…እንዲያና እንዲህ እያልን ስለ አንዳንድ ጉዳዮች ስናወጋ ቆየን። የሚገርመው ነገር ግን ይህቺ የምላችሁ እህት አሁን በኢትዮጵያ ውስጥ እየተካሄደ ስላለው ጦርነት እንኳ የምታውቀው አንዳች ነገር የለም። እንደ አዲስ ነው የምትጠይቀኝ። ቆይቶ ግን እየፈነጠዘች እንዲህ አለችኝ። "…ይኸውልህ ዘመዴ በቅርቡ ወደ ኢትዮጵያ ለመሄድ በዝግጅት ላይ ነኝ። የሚገርምህ ትናንት የኩዌት ዲናር ዘርዝሬ ወደ ኢትዮጵያ ልኬ ነበር። አንዱ የኩዌት ዲናር በኢትዮጵያ በስንት እንደሚመነዘር ታውቃለህ? አለችኝ። አላውቅም አልኳት። አንዱ ዲናር በ308 የኢትዮጵያ ብር አለችኝ። እና አንቺ ስንት ላክሽ አልኳት? 300 ዲናር አለችኝ። ትፈነጥዛለች አይገልፀውም።

"…300 ዲናርን በ308 የኢትዮጵያ ብር አባዛሁት። የመጣልኝ ድምር 92,400 ብር ሆነ። ነገር ዓለሙ ለማይገባት እህቴ በ300 ዲናር 92 ሺ ብር ማግኘቷ ቢያስደስታትም ሃገር ግን ወዴት እያመራች፣ የብር የመግዛት አቅም እንዴት በአፍጢሙ እየተደፋ፣ በአናቱ እየተፈጠፈጠ እየመጣ እንደሆነ አልሀገባትም። እንዲያው ሰሞኑን ሊጨምር ይችላል ስለተባልኩ ይዤዋለሁ ሁላ አለችኝ። በመጠኑ እየሆነ ያለውን ነገር ነግሬያት፣ አደጋው ለሃገር ከባድ እንደሆነ ነግሬያት፣ በፈንጠዝያዋ ላይ ውኃ ቸልሼባት ተለያየን። እንግዲህ ጓደኞቼ ነገርየው በዚሁ ከቀጠለ በቅርቡ አንድ የኩዌት ዲናር በ5 መቶ ወይም በ1ሺ የኢትዮጵያ ብር መመንዘሩ አይቀርም ማለት ነው። ዶላር፣ ፓውንድና ዩሮም እንደዚያው።

"…አሁን ስለ ጦርነቱ መጻፍ ፍረጃው ከባድ ነው። በዚያ በኩል ፀረ ህዝበ ትግራይ ያስብላል። ያስፈርጃል። በእኛ በኩል ደግሞ ተማረከ፣ ደመሰስን፣ ወቀጥነው የሚል ሃረግ ካልተጨመረበት በቀር ጁንታ፣ የወያኔ ተላላኪ ተብሎ ያሰድባል። እንደመፍትሄ የያዝኩት በዚህ መንገድ የጀመሩት ይቀጥሉበት። እነ ደርቤ ይዘግቡት። እኔ ግን በተቻለ መጠን የጦርነቱ ጉዳት በሃገርና በህዝብ ላይ እያደረሰ ያለውን ጉዳትና ውድመት በስሱ እየዳሰስኩ እሱ ነገር ላይ ባተኩር ይሻለኛል ብዬ ምርጫዬን አስተካክያለሁ። የከፋ ነገር ሲመጣ፣ ውሸት ሲበዛ ግን የደረሰኝን መረጃ ይፋ አላደርግም ማለት አይደለም።

"…የዩክሬንና የሩሲያን ጦርነት ተመልከቱ። ዩክሬን ነዳለች፣ ፈርሳለች። ተቃጥላለች። ህዝቧ ተሰዷል። ነገር ግን ጦርነቱ ሊቆም አልቻለም። አሜሪካ እና የአውሮጳ ኅብረት ዩክሬንን ታይቶ በማይታወቅ በጀት እና የጦር መሣሪያ አቅርቦት ለአፍታም ያህል ስላልተለዩዋት ሃገሪቷ ብትዳሽቅም የስንቅና ትጥቅ አቅርቦቱ ስላለ በጥቂት ሰውም ቢሆን ጦርነቱ ቀጥሏል። በኢትዮጵያም እንደዚያው ነው። ህወሓት ላለፉት 50 ዓመታት አንድ ቀን አደጋ ይደርስብኛል በሚል እሳቤ በትግራይ የጦር መሣሪያ የመማምረት ያህል ስትቀብር ነው የኖረችው። በሩ ቢዘጋብኝ ተተኳሽ ላይኖረኝ ይችላል በሚል ትግራይን የጦር መሳሪያ ዲፖ አድርጋ ነው የቆየችው። የስንቅ ችግሯን ከነ ነዳጁ ምዕራባውያኑ እየቻሉት ውጊያው ቀጥሏል። ነዳጅና ስንቁ ሲያልቅ ደግሞ ጥቂት ፋታ ተወስዶ እረፍት ይደረግና ይገባበታል። እናም አዙሪቱ ይቀጥላል። ምንአልባት ተዋጊ ሲያልቅ ካልቆመ በቀር ህወሓት እያለች ጦርነቱ አይቆምም።

"…አቅም ያላት ሩሲያ እንኳ አሁን በቻይና፣ በኢራንና በኮርያ መረዳት ጀምራለች። የዩክሬን ሩሲያ ጦርነት ጦርነት በአጭሩ ካልተቋጨ ዳፋው ለዩክሬንና ለሩሲያ ብቻ አይደለም የሚተርፈው። ለመላው ዓለም እንጂ። አውሮጳም፣ አፍሪካም፣ በተለይ ነዳጅ እንጂ አንድ ቁና እህል ማምረት የማይችለው የዓረቡ ዓለም ከፍተኛ ድቀትና ውድቀት ትርምስም ይገጥመዋል።

"…እዚህ በምኖርበት ሃገር በጀርመን እንኳ ከፍተኛ ስጋት ነው ያለው። በሱፐርማርኬት ያልጨመረ ነገር የለም። መጪው ክረምት ነው ብርዱን ለማለፍ እንዴት እንደሚኮን ፈጣሪ ይወቀው ተብሏል። ሩሲያ ጋዝ ስላቋረጠች ስጋቱ ጨምሯል። ባለፈው ጊዜ አሜሪካ የህጻናት ወተት አጥታ ከአውሮጳ ሃገራት ለምና መውሰዷ ሲነገር ሰምቻለሁ። ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ በአውሮጳ ነዳጅ ተወዷል። ለዜና አያበቁትም እንጂ ህዝብ በመንግሥት ላይ ዘወትር ሰልፍ እንደወጣ ነው። በሆሊውድ መገኛዋ በሎሳንጀለስ ከተማ ኗሪው ነጩም ጥቁሩም ህዝብ እንደ ኢትዮጵያ ጎዳና ተዳዳሪ በላስቲክ ቤት በከተማ መሃል ተኮልኩሎ የ8 ደቂቃ ቪድዮ አይቼ ደንግጫለሁ። በኮቪድ የደቀቀው፣ ቀጥሎ በሩሲያ ዩክሬን ጦርነት የሚንኮታኮተው ዓለም፣ ተጨማሪ የኢራን እስራኤል፣ የአሜሪካና የቻይና፣ የኮሪያና የአሜሪካ፣ የአውሮጳና የሩሲያ ጦርነት ሳይጨመርበት እንኳ የሚጠብቀው ከፍተኛ ዓለምአቀፍ የኢኮኖሚ ቀውስ ነው። የኒዩክለር ጦርነት ከተጨመረበት ደግሞ አስቡት። እጅጉኑ ይከፋል።

"…በኢትዮጵያም ጦርነቱ በዚሁ ከቀጠለ እና በአጭር ጊዜ ውስጥ ካልተቋጨ አደጋው ደግሞ ከአውሮጳም በእጅጉ የከፋ ነው። ህወሓት በጊዜ እንዲደመሰስ ደግሞ ምዕራባውያኑ አይፈልጉም። ልክ እንደ ዩክሬን ነው ሊረዱት የሚፈልጉት። አገዛዙ ደግሞ በአብዛኛው አፍቃሬ ህወሓት እና የህወሓት ዲቃላ ፍጡርም ስለሆነ ህወሓትን በአጭር ጊዜ ማሸነፍ አይፈልግም። አንዳኛ ሰሜኑ ኦርቶዶክስ በዚህ አጋጣሚ መመንመን፣ መድቀቅ፣ መውደም አለበት ከሚልም ሃይማኖታዊ ፍላጎትም የተነሣ ነው። ሁለቱ ህዝቦች ከደቀቁ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ዳግም አይገቡም፣ መጪውን ክፍለዘመን በተረኝነት እኛ ብቻችንን እኛን የምትመስል ኢትዮጵያን ፈጥረን እየገዛን እንኖራለን ከሚል ዕሳቤም የተነሣ ጦርነቱን በጊዜ መቋጨት አይፈልጉም። ታዲያ ለጦርነቱ ወጪው ይቀጥላል። በብሔራዊ ባንክ የሚገኘው ተጠባባቂ የውጭ ምንዛሪም ተሟጦ ያልቃል። እንደ ቸገረው፣ እንደጠረረበት ግለሰብ መንግሥትም ከተገኘበት ልበደር ይላል። በዚህ ዘመን ደግሞ አበዳሪ የለም። ሁሉም ችግር ላይ ነው። ቆይቶ መንግሥት የቤት ዕቃ ልሽጥ ይላል። አየር መንገድ፣ ባንክ፣ ቴሌ ለመንግሥት የቤት ዕቃ ማለት ነው። እሱን ልሽጥ ይላል። ሽጦም የሚገዛው ቦንብ፣ ጥይትና ታንክ ስለሆነ መጨረሻ ላይ አጨብጭቦ ይቀራል። አያዋጣም።

"…አሁን ለጊዜው መከላከያ ሠራዊቱን፣ ጥምር ጦሩን የጎንደር፣ የጎጃም፣ እና የወሎ ህዝብ ወተት፣ እንጀራ፣ እርጎ፣ ዳቦ፣ ጠላና ጠጅ፣ ኮረፌም ጭምር ስንቅ እያቀበለው እየተዋጋ ነው። እስከመቼ የሚለው አይታወቅም። ለተዋጊው ኃይል ይድረስ አይድረስ ባላውቅም ኦሮሚያም ለበዓል ለጥምር ጦሩ ሰንጋ ልኬአለሁ ብሏል። መንግሥት ያቃተውን ስንቅ ማቅረብ ህዝቡ እስከመቼ ይችለዋል? የሚያዛልቅ አይደለም። በውጭ ያለው ዳያስጶራ ደግሞ የኢትዮጵያን ጦር በስንቅ እንዳያግዝ " ትዕቢተኛው፣ ሥጋ ለበሱ ሰይጣን፣ እግረ ደረቅ፣ ኮቴ መናናው፣ የብርሃን ልብስ ለብሶ የተገለጠው ዲያብሎሱ ዐቢይ አሕመድ አቦይ ስብሃትን የመሰለ አራጅ አሳራጅ በይፋ ፈትቶ ለቅቆ በዳያስጶራው ላይ ቀዝቃዛ በረዶ ውኃ ቸልሶበት ለጨጓራ በሽታ ዳርጓቸዋል። ዐቢይ ዳያስጶራውን ውሻ አድርጎ ነው ቅስሙን ሰብሮ የለቀቀው። በሰሜን ዕዝ ላይ ወንጀሉን ያቀነባበረ ዋነኛ ሰው ከነጀሌዎቹ በይፋ ለቅቆ ዳያስጶራውን እናንተ ገንዘብ ስንጠይቃችሁ አምጡ እንጂ ስለሌላው ሥራችን አይመለከታችሁም በማለት ኩም አድርጎ አንገታቸውን አስደፍቶ አዋርዶ ካባረራቸው በኋላ ዳያስጴ እንደ ድሮው የዐቢይን መንግሥት
12.4K views10:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-24 12:52:57
"…አንድ የኩዌት ዲናር እየተመነዘረ ያለበትን የኢትዮጵያ ብር ስሰማ የጻፍኩት ማስታወሻ ነው። የብር የመግዛት አቅም በአፍጢሙ እየተደፋ መሆኑን በማየቴና ቀጥሎ ከባድ የሆነ ታይቶ የማይታወቅ የኢኮኖሚ ቀውስ እንዳይገጥመን በመስጋት እንደ ዜጋ በጊዜ ወደ መፍትሄ ብናመራ ብዬ የጫጫርኳት ጦማር ናት። በዚህ መልኩ መወትወቴን ደግሞ እቀጥላለሁ።

"…ያልቸገራችሁ፣ አገዛዙም የተመቻችሁ የብልፅግና ካድሬዎች ግን ቢቻል ጮጋ ብላችሁ እለፉት። ከተቻለም ሃሳብ ስጡበት። አልያ ግን ስድብ እሳደባለሁ፣ ነውሬን እተፋዋለሁ ብላችሁ ፔጄ ላይ በአፋችሁ ለመፀዳዳት ብትመጡ እቀስፋችኋለሁ። ሰምታችኋል። ይሄ የመወያያ መድረክ ነው። የአስተያየት መስጫውን ሰንዱቅ እንደሌሎች አልቆልፈውም። ሁሉም ሰው ይተንፍስ። ይወያይ። ስድብ ግን ካካ ነው። እፉ ነው።

"…ቆይቼ አንብባችሁ ስትጨርሱ የአስተያየት መስጫ ሰንዱቁን እከፍትላችኋለሁ። በጨዋ ደንብ እንወያይ። ተመስግናችኋል።



http://t.me/ZemedkunBekeleZ
18.2K views09:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-23 12:35:17 "…አሁን በዘመነ ብልጽግና ሴተኛ አዳሪነት ከምንግዜውም በላይ የተስፋፋው ዝም ብሎ አይደለም። በኦሮሚያ የሚገደለው አባወራውና ወንድ ወንዱ ነው። አባወራው ሲገደል፣ ሲታረድ ቤተሰብ ይበተናል። ቤተሰብ ሲበተን ደግሞ ለማኝና ሴተኛ አዳሪነት ይስፋፋል። አሁን በየከተማው ለልመና እጅ ዘርግተው፣ ለሴተኛ አዳሪነት ተሰልፈው የምታዩዋቸው እንቡጥ ጽጌረዳ ህጻናት አብዛኞቹ በወተት ፊታቸውን ታጥበው እያደጉ የነበሩ ህፃናት ናቸው። እነሱ ናቸው ምድሪቱን የሞሉት። ገበሬ ገድሎ ድሃን ማብዛት የዘመኑ ፍልስፍና እየሆነ ከመጣ ሰንብቷል። በዐማራ ክልልም እንደዚያው ነው። ወንድ ወንዱ ወደ ጦርሜዳ ሄዷል። ተመላሽ የለም። ቀዬው በሴቶችና በህጻናት ተሞልቷል። ይሄም ከባድ አደጋ ነው። ጦርነቱ በአጭር ጊዜ እንዲያልቅ ዕቅድ ስላልተያዘለት መከራው ገና ይከብዳል።

"…በትግራይ ትምህርት የለም። ሥራ የለም። ግብርና የለም። ባንክ የለም። ኢንተርኔትና ስልክ የለም። ነዳጅ የለም። ሱቅ የለም። ሸቀጣ ሸቀጥ የለም። ያለው መዋጋት ብቻ ነው። መግደል፣ መገደል፣ መዝረፍ፣ መሞት ብቻ ነው። ሌላ አማራጭ የለም።

"…በቀዬ በመንደሩ የቀረው፣ ያልዘመተው ዐማራ ደግሞ ለመከላከያው፣ ለዐማራ ልዩ ኃይል፣ ለዐማራ ፋኖ፣ ለዐማራ ሚኒሻ የማያቋርጥ ስንቅ እያቀረበ ይገኛል። ዐማራው መከላከያውን እና የጥምር ጦሩን ቀጥ አድርጎ ይዞታል። ወተት፣ እርጎ፣ አሬራ እየጠጣ እንዲዋጋ እየደገፈው ነው። የሚቆስለው ወታደርም የሚታከመው በዚያው በዐማራ ክልል ነው። የክልሉ በጀት በስንቅና በመድኃኒት አልቋል። ጦርነቱ ይቀጥላል። ዐማራ፣ አፋርና ትግሬም ሙልጩ ይወጣል።

"…መነሻዬ የብር የመግዛት አቅም መውደቅ ከፊታችን ከባድ አደጋ መደቀኑን ለማሳየት ነው። ህክምና ውድ ሆኗል። ሸቀጣ ሸቀጥ ውድ ሆኗል። ሌባው፣ ማጅራት መቺው በርክቷል። ሰዉ ከባድ የአዕምሮ ውጥረት ላይ ወድቋል። ይሄን የኮቴ መናና፣ የእግረ ደረቅ፣ የአሲዳም፣ የሰላቢ አገዛዝ መድኃኔዓለም በጊዜ መፍትሄ ካልሰጠው በቀር ከባድ ትርምስምስ ያለም ነገር እንደሚጠብቀን ለመናገር ጠንቋይም፣ ኢዩ ጩፋንም መሆን አይጠይቅም።

"…አንድ ዶላር መቶ ብር ተመነዘረ ሲባል ጮቤ የምትረግጡ ለቃቃሚ የአዕምሮ ዝግመት የተጠናወታችሁ ዳያስጶራዎችም እፈሩ። ሚልዮን ብሮች ብትሰበስቡ፣ ብታከማቹ ምን ዋጋ አለው? ምንም ዋጋ የለውም። እንደ አድቫንቴጅ ቆጥረህ ህንፃ ብትገነባ አትኖርበትም። አትስገብገብ። ይልቁኑ ለውጥ የሚመጣበትን መንገድ፣ ሃገሪቱ ከዚህ ማጥ የምትወጣበትን መንገድ መፈለግ እንጂ ዶላሬን በመቶ ብር ዘርዝሬ እከብራለሁ ብለህ አትወራጭ። እመነኝ አትበላውም። አትኖርበትም። የራበው ህዝብ መሃል አንተ ጠግበህ የምትኖር ከመሰለህ ተሳስተሃል። ገበሬ ከሌለ፣ ምርት ከሌለ የከተማ ሰው ብሩን በባንክ እንዳጨቀው ሳይበላው ቋንጣ ሆኖ በቤቱ ደርቆ ይኖራል። መስገብገቡን ተዉትና ለለውጥ ተዘጋጁ። መሃሉ ዳር የመሆኛው ጊዜ ስለቀረበ አብዝተን እንጸልይ።

"…ይሄ ሃሳቤ የሚያበሳጫችሁ እንደሚኖር እረዳለሁ። እገምታለሁም። ነገር ግን ቅር የሚልህ ካለህ መፍትሄው እውነታውን ተረድቶ ለለውጥ መዘጋጀት ነው። አልያም በአናትህ መተከል ነው። ባንክህ ውስጥ ያለው ብር፣ በኪስህ ይዘህ የምትዞረው የኃጢአት ብር አንተንም፣ ቤተሰብህንም ይዞ ነው የሚጠፋው። እናም ቁጭ ብለህ በፅሞና ስለመጪው ጊዜ አስብ።

"…ጦርነቱ ቀጥሏል። በራያ፣ በአዲአርቃይ፣ በማይፀብሪ፣ በመተማ፣ በወልቃይት፣ በአፋር በራማ በተንቤን ጦርነቱ ቀጥሏል። በወለጋም የዐማራ እርድ እንደቀጠለ ነው። ጦርነቱ በዐማራ ክልል ነው። ውድመቱም፣ የትግሬም የጥምር ጦሩም የሬሳ ክምር በዐማራ ክልል ውስጥ ነው። ገበሬው እየወደመ ነው። የማያልቅ የድል ዜና ዘገባውም እንደቀጠለ ነው። ዶላር ግን መቶ ብር እየተዘረዘረ ነው።

"…ቆይቼ ደግሞ ብቅ እላለሁ…!!
86.5K viewsedited  09:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-23 12:35:17 "…የኢትዮጵያችን ብር የመግዛት አቅሙ እየተዳከመ መምጣቱ እየተነገረ ነው። ፩ የአማሪካ ዶላር በጥቁር ገበያው ፻ የኢትዮጵያ ብር እየተመነዘረ እንዳለም እየተነገረ ነው። ይሄ መጥፎ ዜና ነው። እንዲያም ሆኖ ሃገሪቷ አሁንም በከባድ የእርስ በእርስ ጦርነት ላይ ትገኛለች። ለጦርነቱ የሚያስፈልገው ግብአት ደግሞ ከሟች ወታደሮች በቀር ሁሉም ነገር በዶላር በውጭ ምንዛሪ የሚገዛ ነው። ጀቱ፣ ድሮኑ፣ ታንኩ፣ ጥይቱ፣ ጥቁር ክላሹ በሙሉ በዶላር ተገዝቶ የሚመጣ ነው።  ይሄ የምታስገባው፣ የምትገዛው እንጂ የምትሸጠው ወደ ውጪም ልካ የውጭ ምንዛሪ የምታስገባበት ሀብት ለሌላት ሃገር ደግሞ ይሄ ወጪ እጅግ ከባድ ነው። ጥይትና ቦንብ በዶላር ተገዝቶ መጥቶ ሰው ይገደልበታል። መሠረተ ልማት ይወድምበታል። በዕዳ የተሠራ ድልድይ፣ ሆስፒታል፣ ትምህርት ቤት ይወድምበታል። ይሄ ማለት በዶላር ጨዋታ፣ ዶላርንም ማንደድ ማለት ነው።

"…አሁን መንግሥት ተብዬው ይሄን አደገኛ ዘመን ለማለፍ በመሃይም ዕውቀቱ ዊኒጥ ዊኒጥ ለማለት እየሞከረ ነው። የመንግሥቱ ባለ ሥልጣናት አብዛኛዎቹ የህወሓት ዘመን ካድሬዎችና የትምህርት ዝግጅት አላቸው የሚባሉቱ እንኳ ከኮብል ስቶን ማምረቻው ሲቪል ሰርቪስ ኮሌጅ በፋብሪካ ቅርፅ ተመርተው የወጡ አንድ አይነት እንከፎች ስለሆኑ ይሄን እየመጣ ያለውን ከባድ አደጋ የሚያቆሙት አይመስልም። በቀላሉ በቀድሞዎቹ የኢህአዴግ ካድሬዎች በአሁኖቹ ሚኒስትሮች አቅም አይቻልም። እነሱ አሁን እንደመፍትሄ ይዘው እየሠሩበት ያለው ብርን አትሞ በገበያ ውስጥ በሰፊው ማሰራጨትን ነው። ይሄ ደግሞ በራሱ እጅግ አደገኛ ወደሆነ የውድቀት መንገድ እንደሚወስድ በዘርፉ የተሰማሩ የኢኮኖሚ ባለሙያዎች ይናገራሉ።

"…አሁን በኢትዮጵያ ጥቂቶች ብዙ ሀብት እና ብር እንዳላቸው እየተነገረ ነው። ጥቂቶች ዘወትር ውስኪ ሲጠጡ፣ ዘወትር ቁርጥ ሲበሉ፣ እጅግ ውድ ዘመናዊ መኪና ያውም ውድ ቤንዚን የሚጠቀም ሲያሽከረክሩ ይታያሉ። አጭር፣ ረጅም፣ ወፍራም፣ ቀጭን፣ ጠይም፣ ጥቁር፣ ቀይ፣ የቀይዳማ፣ ፀጉረ ረጅም፣ ተማሪ፣ ወጣት፣ ቃ ያለች እያሉ በገንዘባቸው የደኸዩ ሴቶችን እያማረጡ ነው። ፋብሪካም ሥራም ሱቅ በደረቴ እንኳ ሳይሠሩ በአኗኗር ግን አላሙዲንን የሚያስቀኑ ግለሰቦች መፈጠራቸውም እየተነገረ ነው። በሰፊው ብዙ ብር በጥቂቶች እጅ እንዲከማች ተደርጓል። ሌላው ህዝብ ደግሞ ባዶ እጁን እያወናጨፈ፣ እየተወራጨ ብቻውን እያወራ በመንገድ ላይ ሲጓዝ ይታያል። የቤት ኪራዩ፣ የልጆች የትምህርት ቤት ክፍያው፣ ዩኒፎርሙ፣ ቀለቡ፣ ትራንስፖርቱ፣ አስቤዛው ለወላጆች ብቸኛው የእብደት መንስኤ ሆኗል። አንድ ደብተር በ፸ ብር ተገዝቶ እንዴት እንደሚዘለቅ አስቡት። ደሞዙ ፪ሺ ብር ለሆነ ሰው ደግሞ በተአምራት ካልሆነ በቀር እንዴት እየኖረ እንደሚገኝ ማሰቡ በራሱ ይከብዳል።

"…፲፫ ሚልዮን ተማሪዎች ዘንድሮ ለመማር አልተመዘገቡም ተብሏል። አስቡት ይሄ ሁላ ተማሪ ትምህርት ጠልቶ አይደለም። ቢቸግረው፣ ቢጨንቀው እንጂ። ብዙ የድግስ ወጪ የበዛበት የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር በራሱ ዘንድሮ ለተማሪዎች ቦርሳ፣ ደብተር፣ ዩኒፎርም ለፕሮፓጋንዳም ቢሆን ደጉ መንግሥት፣ ጠሐዩ መንግሥታችን ለማስባል ይሰጥ የነበረውንም ዘንድሮ አልችልም ብሎ እንደከለከለ ነው የሚነገረው። በፀጥታ ምክንያት በዩኒቨርስቲዎች መማር የነበረባቸው ተማሪዎች ትምህርት ላይ ስላልሆኑ ተስፋ ይቆርጣሉ። ተስፋ መቁረጥ ደግሞ ወደ ከባድና አደገኛ ወንጀለኝነት እንዲያመሩ ያደርጋቸዋል። ዘረፋ፣ ንጥቂያ፣ የዚህ ውጤት ነው። ይሄ በከተሞች ነው። በኦሮሚያ ሲሆን ደግሞ ይለያል። በኦሮሚያ በይፋ ውትድርና ትሰልጥናለህ። መሳሪያ ይሰጥሃል። ከዚያ ሸኔ የሚባል ድርጅት ትቀላቀላለህ። ከዚያ ደሞዝህን ባንክ ዘርፈህ ትበላለህ። ዐማራ ገድለህ፣ ዘርፈህ ኑሮህን ትገፋለህ። ይሄ የሚቻለው፣ የሚፈቀደውም በኦሮሚያ ብቻ ነው። ከኦሮሚያ ውጪ ባንክ ዘርፎ መኖር አይፈቀድም። ክልክል ነው። ወንጀል ነው። በትግራይ ያው የምታዩት ነው።

"…አሁን በኢትዮጵያ ውስጥ ቢያንስ የማይርባቸው ሰዎች አሉ። እነዚህ ሰዎች የገዢው ፓርቲ አባላትና የገዢው ፓርቲ የሥጋ ዘመዶች ናቸው። ቤት ይሰጣቸዋል። አበል በየጊዜው ያገኛሉ። ከፍ ያሉቱ ደግሞ በይፋ ዘርፈው እንዲበሉ ይፈቀድላቸዋል። ጉቦ መቀበል የተባረከላቸው የማያስጠይቅ ወንጀልም እንዳይሆንባቸው የተፈቀደላቸው አሉ። ከመሬት ሽያጭ አንሥቶ ጉዳይ ለማስፈጸም ሁላ በይፋ ብር ተምነው ከህዝቡ እየዘረፉ እንዲኖሩ የተፈቀደላቸው አሉ። ከፀጥታው ዘርፍ አንሥቶ በመንግሥቱ ላይ የተለየ ተቃውሞ እንዳያስነሱ እየዘረፉ እንዲበሉ የተፈቀደላቸው አሉ። እንኳን በቢሮክራሲው ውስጥ ያሉት ይቅርና ከቢሮክራሲው ውጪ ያሉቱ አክቲቪስቶቻቸውን እንኳ ከጎንደር፣ ከጎጃምና ከወሎ አዲስ አበባ ድረስ አምጥተዋቸው የቤት ኪራይ፣ የጫትና የወር ቀለብ እንዲሰፈርላቸው በማድረግ ዘና ፈታ ብለው እንዲኖሩ ተደርገዋል። አሁን በመላው ዓለም የገባው ችግር ያልገባው ብልፅግናዎች ቤት ብቻ ነው።

"…የፕሮቴስታንት ፓስተሮች የዲፕሎማት መታወቂያ ስለታደሉ ዲፕሎማት ደግሞ ስለማይፈተሽ በኃይለኛው የመዓድን እና የዶላር ንግድ ላይ መሰማራታቸው እየተነገረ ነው። የኦሮሞ እስላሞች ከቀረጥ ሁላ ነፃ እየተደረጉ እንደሆነ እየተሰማ ነው። እስልምናው ባንክም ስለከፈተ ለገንዘብ አጠባው አመቺ መደላድል እየተፈጠረ መሆኑም እየተነገረ ነው። ለጊዜው እነዚህ ሁለት ኃይሎች በእምነት ቢለያዩም በጥቅም አንድ ሆነዋል። ተጠቃሚ ቢሏችሁ ተጠቃሚ አይምሰሏችሁ። ለጊዜው እነ ዮናታን ቤት ችግር የለም። ሁለቱም ባንክ አላቸው። ባንኩ ውስጥ ደግሞ ገንዘብ አለ። ገንዘብ ካለ ለጊዜው ራብ የለም። አንድ ማክያቶ ከተቆራጭ ኬክ ጋር 250 ብር ለመክፈል አይቸገሩም።

"…የቲማቲም ኪሎው 80 ብር መግባት ሲገርምህ ጥቂት ቆይቶ ምሳ ለመብላት ብር እንዲህ በጋሪ ይዘህ ለመሄድ የምትገደድበት ዘመን ከፊትህ ተገሽሯል። ብር ከወረቀት እኩል የማይለይበት ዘመንም ከፊትህ ነው። ቤትህን፣ ርስትህን፣ የቤት ዕቃህን በመሸጥ የምትሻገረው ዘመን አይደለም። ምርት ያለው በጠቅላይ ሚንስትሩ የፌስ ቡክ ፔጅና በአገዛዙ የሚድያ ልሣናት ላይ ብቻ ነው። አረንጓዴ እርሻ፣ ኩታገጠም የስንዴ ማሳ፣ አቡካዶው በዐቢይ አህመድ ፌስቡክ ላይ ተንዠርግጎ ስታየው ትደመማለህ። ያውም አሜን ሃሌሉያ አንተ ብሩክ የሆንክ ሰው ዘመንህ እንዲህ እንደፎቶው ይለምልም፣ አረንጓዴ ይሁን ከሚል ምርቃት ጋር የኢትዮጵያን ልማት የምታየው በጠሚው የፌስቡክ ፔጅ ላይ ነው።

"…አምራቹ ገበሬ ተገድሏል። ታርዷል። ተፈናቅሏል። ሩቅ ሳትሄዱ እዚህ ደብረ ብርሃን ብቻ ጎራ ብላችሁ ብታዩ የወደፊቷ ኢትዮጵያ የከተማ ሰው ከፊቱ የተደቀነውን አደጋ በሚገባ ይማርበት ነበር። እርግጥ ነው መናፈሻና ህንፃ እየተገነባ ነው። ወደ መናፈሻ የሚኬደው ግን የበሉት ምግብ እንዲንሸራሸር፣ አዕምሮን ለማደስ፣ ለማሳረፍ፣ በልምላሜውም ህሊናን ለመመገብ ነው። እንጂ መናፈሻ ለራበው ሰው አይሆንም። አይጠቅምም። አየሩ አይበላ። አበባው አይበላ። እና አምራች ገበሬውን ገድለህ፣ እህሉን በጎተራው አቃጥለህ፣ በሬውን አርደህ በልተህበት ከሰማይ መና መጠበቅ ነውርም፣ ኃጢአትም ነው።
81.4K views09:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-23 12:27:25
"…ሩቅ አይደለም። እዚሁ ጎረቤት ሃገር ነው። አንድ ኪሎ ቲማቲም 80 ብር መግዛት ከጀመርክ ቀጥሎ አንድ ምሳ ለመብላት ብር በዚህ መልኩ ይዘህ መዞር ግድ ሊልህ ነው ማለት ነው። ቀልድ አይደለም። ያውም የሚያሳልፍህ ካገኘህ ነው። ምልከታዬን ከታች አስቀምጬዋለሁ። ቆይቼ የሃሳብ መስጫ ሰንዱቁን እከፍትላችኋለሁ። የመሰላችሁን መተንፈስ ነው። የእኔ ቤት እንዲህ ነው። ሰንዱቅ ቆልፎ ብቻህን መለፍለፍ ቀሽምነት ነው። መልካም ንባብ…
84.7K views09:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-22 16:38:19 "…ሰሞኑን የኦህዴድ ብልጽግና በወለጋ ሆሮ ጉዱሩ ዞን በጀርዴጋ ጃርቴ ወረዳ ላይ የዐማራም የኦሮሞም ተወላጆችን ይሰበስባል። ይሰበስብና እንዲህ ይላቸዋል። ኦሮሞ የሆናችሁ ለጊዜው ከአካባቢው ዞር በሉ። የሚመጣው ኃይል ማን ኦሮሞ፣ ማን ዐማራ እንደሆነ ለማጣራት መድከም የለበትም። ነገሩ ሲበርድ ሃገር ሲረጋጋ ትመለሳላችሁ። ዐማሮች ግን በጊዜ ከዚህ ብትጠፉ ይሻላችኋል። የሚያድናችሁ፣ የሚታደጋችሁ ማንም ኃይል የለም በማለት ቃል በቃል ለተሰብሳቢው ህዝብ ይነግሯቸዋል።

"…መሸ ነጋ፣ ሁለተኛም ቀን ሆነ። የአካባቢው የኦሮሞ ተወላጆች በተባሉት መሠረት ዕቃቸውን ሸክፈው በተሰጣቸው ኮድ መሠረት አካባቢውን ለቀው ወጡ። ዐማሮቹ ግን መሄጃም የለን፣ የትም አንሄድም ብለው ባሉበት የሚመጣውን ለመቀበል ተዘጋጅተው ይጠባበቁ ጀመር። የዐማሮቹን ጽናት እና ቁርጠኝነት ያየው የኦህዴድ ብልፅግና ሌላ መመሪያ አወጣ። "ማንም የዐማራ ተወላጅ ከወንዝም ቢሆን ከቧንቧ ከቦኖ ውኃ መቅዳት አይችልም" አለ። ፈርተው ሴቶች ከቤት ዋሉ።

"…መሸ፣ ነጋ፣ ሦስተኛም ቀን ሆነ። ወንድ ወንዶቹ ዐማሮች ሁላችንንም ጨፍጭፈው ያለዘር ከሚያስቀሩን እናንተ ሴቶችና ህጻናት አካባቢውን ለቃችሁ ተሰደዱ፣ ብለው ማቲውንና ሴቶችን ከወረዳው አሸሹ። አሸሹናም እነሱ ወንዶቹ ብቻ በመንደሩ ቀሩ። ቆይቶ የህዝቡን መሰደድ የተመለከተው የወረዳው ኦህዴድ መጣ። መጣና የቀሩቱን ወንዶቹን መሣሪያ አምጡ አላቸው። ሕጋዊ ነን። ለምን እንሰጣለን። በአስተዳደሩ ውስጥ በመዋቅር የታቀፍን ሚኒሻዎች እኮ ነን ብለው ይመልሳሉ። ኦህዴዶቹ ኃይል ለመጠቀም ሞከሩ። ዐማሮቹም ለመሞት የቆረጡ ስለነበር በአቋማቸው ፀኑ።

"…መሸ ነጋ አራተኛም ቀን ሆነ። አሁን ፍርዬ ከአዲስ አበባ የኢንተርኔት ኔትወርክ አቋረጠች። የፍርዬ ዋነኛ ሥራም ይሄ ነው። ኔትወርክ ሲቋረጥ ሸኔ የሚባለው የሽሜ ተለዋጭ ኃይል ጭፍጨፋ እንዲጀምር ኮድ መስጠታቸው መሆኑ ነው። ኔትወርኩ ሲጠፋ መሣሪያ የሌላቸው ባገኙት መንገድ መሸሽ ጀመሩ። መሣሪያ ያላቸው ግን የመጣው ይምጣ ብለው የሚሆነውን መጠባበቅ ያዙ። ቀደም ብሎ ኦህዴድ መከላከያውን በትእዛዝ አስወጥቶታል። የኦሮሚያ ልዩ ኃይልም በስፍራው የለም። ቢኖርም ከኦነግ የተለየ የሚያመጣው ነገር የለም። ቆይቶ ባለ ጉድሩዎቹ ሹርቤዎቹ የኦነግሽሜ ጦር ከነዘመናዊ መሣሪያቸው ወደ ጃርዴጋ ጃርቴ ግልብጥ ብለው መጡ። ፈሰሱም።

"…መሸ ነጋ፣ አምስተኛ ቀን። ዛሬ ሐሙስ ከማለዳው  12:00 ጀምሮ የተፈራው ደረሰ። በሆሮ ጉድሩ ወለጋ ዞን ጃርዴጋ ጃርቴ ወረዳ ላይ ኦነግሽሜ የተኩስ እሩምታ በዐማሮቹ ላይ ከፈተ። እስከ አሁን እኔ ራሴ ደውዬ ያናገርኳቸው ዐማሮች እንደነገሩኝ ከሆነ ከ5 በላይ ዐማሮች ወድቀዋል። ተረሽነዋል። አንድ የ7 ልጆች አባት፣ አንድ ሌላ የ5 ልጆች አባት እና አንድ ወጣት ተማሪ መገደላቸውን ነግረውኛል። የሁለቱ ሬሳ እስከአሁን አልተገኘም። ግድያውም ተኩሱም ግን እንደቀጠለ ነው።

"…በሰሜን ጦርነቱ እየተካሄደ ያለው በዐማራ ምድር ላይ ነው። ትግሬም ራሱ በድሮንም፣ በጀትም የሚያልቀው በዐማራ ምድር ላይ ነው። ትግሬም የሚታኮሰው የሚጨፋጨፈውም በዐማራው ምድር ላይ ነው። ዐማራው ደግሞ ለጦርነቱ ከወተት አንሥቶ እስከ ሰንጋ ድረስ ለሃገር መከላከያው ሳይሰለች፣ ሳይሰስት፣ ሳያቋርጥ እያቀረበ ነው። ትግሬዎቹ ሲወሩትም የሚዘርፉት፣ ከሊጥ አንሥቶ እስከ ሽሮ በርበሬ የሚያወድሙበት ዐማራውን ነው። እሱ እየተራበ እስኪወረር ጥምር ጦሩን፣ ሲወረር ደግሞ በወያኔ በዐጽሙ እስኪቀር ድረስ እየወደመ ያለው ዐማራው ነው።

"…በወለጋም ይኸው እየታረደ ያለው ያው ዐማራው ነው። ያውም የወሎ እስላም ዐማራ። ዐማራውን እስላም መሆኑ ከመገደል አያድነውም። ዐማራ መሆኑ ነው የሚያስገድለው። ዐማራውን ክርስቲያን መሆኑም አያድነውም። አሁን አሁንማ የዐማራው መታረድ አንድም ሰው አያስደነግጥም። ነጮቹም ቢሆኑ ሁለት ትግሬ ሲሞት የሚያነሡትን አቧራ 5ሺ ዐማራ ሲታረድ እንኳ አይተነፍሱም። ዐማራው ወይ የፖለቲካ መሪ የለው። ወይ ድርጅት የለው። እንዲሁ ያለ እረኛ ሜዳ ላይ የቀረ ህዝብ። ደግሞ እኮ ዐማራውን የሚታገለው ራሱ ዐማራው መሆኑ ነው። እንደዚህ ለፍቺ ያስቸገረ ህልም የሚመስል ጊዜ ከዚህ በፊት በዚያች ምድር እንደነበር ሰምቼም አንብቤም አላውቅም። ይኸው ነው እንዲህ መርዶ ከመንገር በቀር ለሚታረደው ዐማራ ምንም ልታደገው የማልችል አቅመቢስ መሆኔን ሳውቅ ነው የጠፋሁት።

"…ሰው በዚህ ዘመን፣ በዚህ መጠን እና ልክ እንዴት አንድ ነገድ የሆነ ተቆርቋሪ፣ ተሟጋች፣ አይዞህ ባይ አዳኝ መሲህ አንድ ፍሬ እንኳን ጀግና እንዴት ያጣል? እፁብ ነው። ድንቅ ነው።
98.0K viewsedited  13:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-22 16:32:37 "…የሚደርስላቸው ሰው አለ ብዬ አይደለም። ዐማራ ወገን አለው ብዬ አይደለም። ብአዴን፣ ዐብን ድምጽ ይሆናቸዋል ብዬም አይደለም። የዐማራው አክቲቪስት ድምፅ ይሆናቸዋል ብዬ አይደለም። ግን ግን ለማንኛውም ግን እስቲ ጭንቀቶቻቸውን ስሟቸው።
94.0K viewsedited  13:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-22 16:25:38
"…ሱፊያን የሱፍ ይባላል። የ20 ዓመት ወጣት ነው። ዛሬ በወለጋ ሆሮ ጉዱሩ በዐማራነታቸው ምክንያት ከተገደሉት አንደኛው የወሎ ዐማራ ኢትዮጵያዊ ነው። ወለጋ ደውዬ ነበር። ከሞት የተረፉት ያጫወቱኝንም ይሄው ከታች ጽፌላችኋለሁ።
93.0K views13:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-22 11:46:03 ሰላምታ…!!

"…እውነት ነው አዎን ከመንደሩ ጠፍቻለሁ። እውነት ነው ሃቅም ነው አዎን በመንደሩ ውስጥ እንደበፊቱ እንደ እብድ በየሰዓቱ በየደቂቃው መለፍለፍ አቁሜአለሁ። በጤንነቴ በኩል ግን ፍፁም ደኅና ነኝ። ጷጉሜን ፭ እና መስከረም ፩ የቅዱስ ዮሐንስ ዕለት ብቻ ነው ትንሽ ያመመኝ። ከዚያ በኋላ ፍፁም ደኅና ነኝ። ልጆቼ ትምህርትና ላይ ባለቤቴም ሥራ ላይ ናት። እኔ ነኝ የዘመናት ልፍለፋዬን አቁሜ አደብም ገዝቼ ግራ ቀኙን ዙሪያ ገባውን በአንክሮ እየታዘብኩ፣ እየገመገምኩ ቁጭ ብዬ ያለሁት። የብዙዎቻችሁ የጓደኞቼ መልእክትም፣ ሰላምታም ይደርሰኛል። ያሳሰባችሁ የጤንነቴ ጉዳይ ነው። በእሱ በኩል ፍፁም አታስቡ ሰላም ነኝ። እግዚአብሔር ይመስገን።

"…የጠፋሁት ዐውቄ ነው። ብኖርስ አሁን ሌሎች ከሚነግሯችሁ የተለየ ምን እነግራችኋለሁ? ብዬ ነው የጠፋሁት። ሞት፣ አሰቃቂ ግድያ፣ የቁስለኛ ወታደር፣ የሚኒሻ መዓት፣ የትግሬ ተዋጊ ህጻናት የሬሳ ክምር፣ ስደት፣ ራብ፣ መፈናቀል፣ የድሆች ልቅሶ፣ ዋይታ እና እሪታን ሰብስቤ እያመጣሁ እናንተን አቅመቢስ ደካሞች ከማድረግ በቀር ምንም የተለየ ነገር የምነግራችሁ ስለሌለኝ ነው የጠፋት። በእውነት ከምር ከዚህ የተለየ ምን እነግራችኋለሁ? ጭራሽ አዕምሮአችሁን ከማላሸቅ በቀር ምንም አዲስ ነገር ላልጨምርላችሁ ብዬ ነው ከዳር ቁጭ ብዬ ነገሮችን እኔ ራሴ እየታዘብኩ ያለሁት። እውነት ለመናገር ደግሞ የብዙዎቻችሁ እንባ ነጥፏል። ደርቋል። ሞቱንም፣ ሰቆቃውንም ከመልመዳችሁ የተነሣ ደንዝዛችኋል። እናም ምንም የተለየ ነገር የምነግራችሁ ስለሌለ ነው ጥጌን የያዝኩት።

"…በአርበኛ ዘመነ ካሴ መታሰር ጉዳይ ዙሪያም ለጊዜው ምንም አልናገርም። ትንፍሽም አልልም። ማብራሪያም፣ መበርበሪያም አልሰጥም። ለጊዜው ይለፈኝ። እናም የጠፋሁት ምንም አዲስ ነገር የምነግራችሁ ስለሌለኝ ነው። ሁሌ ሙሾ ማውረድ፣ ሁሌ ደረት ማስደቃት ደግሞ ይደብራል። ደስስም አይልም። ዘወትር ከጥንት ጀምሮ እስከ አሁን ዘመን ድረስ እንደ ድመት የራሱን ልጅ ቀርጥፎ ስለሚበላ ማኅበረሰብ ደግሞ ሁሌ ማላዘን ነውርም፣ ኃጢአትም፣ ወንጀልም ነው። ለዚያ ነው የጠፋሁት። ለዚያ ነው ከዳር ቆሜ እኔም እየሆነ ያለውን ሁሉ እየታዘብኩ ያለሁት።

"…ህወሓት፣ ብአዴንና ኦነግኦህዴድ ጠፍተው ትግሬ እና ዐማራ ህዝብ ለህዝብ ቢቀራረቡ ለኢትዮጵያ ይነጋላት ነበር። ነበር ነው ታዲያ። ምኞት። ነገር ግን ህወሓት ወላጃቸው፣ ልጆቿ ብአዴን፣ ኦነግ ኦህዴድም በህይወት እያሉ፣ ከኢትዮጵያም ምድር ሳይጠፉ ግን ስለ ሰላም ማሰብ ከባድ ነው። ምኞቱም ከምኞት አያልፍም። በትግል ሜዳ ላይ ያላችሁ ወታደሮች፣ በህክምና ጣቢያ በየሆስፒታሉ ስላለው የቁስለኛ እና የሬሳ መዐት የምታደርሱኝን እያየሁት ነው። ጦርነት ካለ ሞትና መቁሰል ተጠባቂ ነው። እኔ ግን እንደድሮው አተኩሬ አይቼ የልቤን ምት አላስጨምርም። ሌሎችም አይተው ጤና እንዲያጡ አላደርግም። በእልቂታችሁ ግን አዝናለሁ። ከዚያም ከዚህም በሚረግፈው ወገን ግን አዝናለሁ። የሞቱትን ነፍስ ይማር።

"…በካምፕ ከታጎሩት ስደተኛ ዐማሮች መካከል የሚበሉት፣ የሚጠጡት አጥተው እያለቀሱ የሚልኩልኝን ቪድዮና ፎቶም እያየሁ ነው። በብአዴን ሞት የተፈረደባችሁ ስለሆነ፣ አዳኝም ተቆርቋሪም የፖለቲካ መሪ ስለሌላችሁ የሞታችሁን ቀን ከመጠባበቅ ውጪ ምንም ልንረዳችሁ ባለመቻሌም እጅግ አድርጌ አዝናለሁ። ቢያንስ ህዝብ የሚልክላችሁን እርዳታ እንኳ የራሳችሁ ወገን የሆነው ብአዴን ዐማራው እንዲደርሳችሁ ካላደረገ ምን ልንረዳችሁ እንችላለን? መፍትሄው ፀጥ ብሎ ሳይፈራገጡ መሞት ብቻ ነው። ከመካከላችሁ ወንድ እስኪገኝ፣ ሱሪ የታጠቀ ጀግና እስኪፈጠር፣ መሲሀችሁ እስኪነሣላችሁ ድረስ እያለቀሳችሁ፣ ዋይዋይም እያላችሁ ቢሆን ከመኖር በቀር ሌላ አማራጭ ለጊዜው የላችሁም። እግዚአብሔር ይሁናችሁ።

"…እንደኔ ግምገማና ትዝብት የዘንድሮው ዓመት ሁሉንም ኢትዮጵያዊ በኑሮ እኩል የሚያደርግ ዓመት ይሆናል ብዬ እጠብቃለሁ። ቤተ ክህነቱም የሚንጫጫበት ዐዋጅ ወጥቶበታል። ህዝቡም ከፊቱ ድኅነትና የኑሮ ውድነት ተደቅኖበታል። ተረኛው አካል ጥጋብ ልቡንም፣ ማሰቢያ ጭንቅላቱንም ደፍኖበታል። እናም መከራው እንደ ድሮው ለይቶ የተወሰኑ ዘሮች፣ ነገዶች ቤት ስለማይገባ ሁሉም የሚንጫጫበት፣ ሁሉም የሚያጉረመርምበት ለለውጥም የሚነሣበት ዓመት ነው ብዬም እገምታለሁ። የኮረንቲ ንዝረቱ ሁሉንም ይነካል።

"…በተረፈ እንዲህ አልፎ አልፎ ብቅ እላለሁ። ሃሳቤንም አካፍላችኋለሁ። እንደበፊቱ ችክ ብዬ ግን አላደነዝዛችሁም። አልሟዘዝባችሁም። አዕምሮአችሁንም አልረብሸውም። በጩኸት አልበጠብጣችሁም። አላውካችሁም። አልፎ አልፎ እንዲሁ ብቅ እያልኩ መኖሬን እገልጽላችኋለሁ። በተረፈ እኔ ፌስቡክ የለኝም። አልጠቀምም። በፌስቡክ በስሜ የሚተላለፈውን መልእክት እየሰማችሁ በኮመንት መስጫው ሳጥን ውስጥ ስትሰዳደቡ የምትውሉ አትድከሙ። እኔ ፌስቡክ የለኝም። ዩቲዩብም የለኝም። ፌስቡክና ዩቲዩብ እኔን ኦርጅናሉን ዘመድኩን ከሜዳው በቀይ አባረው በስሜ የመጡ የተነሡ ሀሰተኛ ዘመድኩኖችን ግን በነፃነት እንዲፈነጩ ይፈቅዳሉ። ገንዘብ ሁላ ይከፍሏቸዋል። እኔ አይደለሁም። በስሜና በምስሌ ለምን እንዲጠቀሙ ታደርጋላችሁ ብዬም አመልክቻለሁ። ነገር ግን ምላሽ ከድርጅቶቹ የለም። ሆን ብለው ስለሆነ እኔም ንቄ ትቻቸዋለሁ።

"…በቅርቡ የጀመርኩትን ለመፈጸም በኢትዮ ቤተሰብም፣ በመረጃ ቲቪም ብቅ እላለሁ። አንደኛው የስደተኛውን ካህን ቤት ለመፈጸም ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ በአንድ ታላቅ ገዳም ጀምረን ስለፈጸምነው ፕሮጀክት ጉዳይ ነው። ሌሎቹንም በጊዜአቸው እናወራባቸዋለን። እወዳችኋለሁ። አከብራችኋለሁ። ደግሞ ብቅ እስክል እስክንገናኝ ባላችሁበት ሰላም ሁኑልኝ። መልካም የመስቀል በዓል ይሁንልን።

ሻሎም …!!  ሰላም…!!
103.3K views08:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-17 10:01:23
"…እስከዛሬ በህይወቴ ለሆስፒታል አልጋ የሚዳርግ ህመም ገጥሞኝ አያውቅም። ተከታታይ መርፌ ተወግቼ ኪኒንም ውጬ አላውቅም። የወደፊቱን ባላውቅም እስከአሁን ግን አምላኬ በዚያ መንገድ እንድጓዝ አላደረገኝም። እግዚአብሔር ይመስገን።

"…ከማኅበራዊ ሚዲያው የራቅኩት ከጷጉሜ 5 ምሽት ጀምሮ ነበር። ዛሬ 1ሳምንት እየሞላኝ ነው ማለት ነው። ከገጠመኝ ጊዜያዊ ህመም ለመዳን መድኃኒቱ ራሴን ከኢንተርኔትና ከስልክ አካባቢ ማራቅ ብቻ ነበር። አደረግኩት። ዳንኩም።

"…ቆይቼ ስመለስ የመልእክት ማስቀመጫ ሰንዱቆቼን ከፍቼ ለማንበብ ፩ ቀን ከግማሽ ነበር የፈጀብኝ። ለወትሮው ምኔም የማይጥማቸው ተሟጓቾቼ የምላቸው እንኳ ጭቅጭቄን የናፈቁ በሚመስል መልኩ "አንተ ሰይጣን ለልጆችህ ሲል ክፉ አይንካህ " በማለት ነበር ይጽፉልኝ የነበረው። የ4ተኛ ክፍል የሂሳብ መማሪያን አይተው የግዕዝ ቁጥርን የትመጣ አንብበው ያበዱም ሰዎች ገጥመውኛል። የአኖሌ እና በላይ ዘለቀን ታሪክ ገና ስላነበቡ እኮ ነው። ደፋሩ የኦሮሙማ ቡድን ቢቢሲ የአማርኛ ዜናን ዋቢ አድርጎ የጻፋቸው የመማሪያ መጻሕፍት የሚፈጥሩትን ትኩሳት ቆይቶ ማየት ነው።

"…ወሬ ኦዱ ብቻ እንዳይሆን ዘንድሮ መርሃ ግብሬን እንዴት ማቅረብ እንዳለብኝ ከወዲሁ በብዙ እያሰብኩ ነው። ሰማይ ዝቅ መሬት ከፍ ቢል ግን ከእውነት ንቅንቅ የለም። የኢትዮጵያ ትንሣኤ የመጀመሪያ ዓመት ነው የተባልነውን ይህን 2015 ዓም ዘመነ ሉቃስን ከነ ጭቅጭቅ ንትርኩ ብዙ የበረከት ሥራዎችንም በፈቃደ እግዚአብሔር ለመሥራት እኔና ጓደኞቼ እንሞክራለን። ለስደተኛው ካህንም ቤቱን እንገዛለታለን።

"… አንድ ገዳም ላይ ድምጼን አጥፍቼ የጀመርኩት የልማት ፕሮጀክትም በጥበብ ፍጻሜውን አግኝቷል። ማሽኑም ተተክሎ፣ ፋብሪካውም ተገንብቶ አልቋል። በቅርቡ አበሥራችኋለሁ። እኔ ግን ደኅና ነኝ።

"…እንደዚያ ነው…!!
211.9K views07:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ