Get Mystery Box with random crypto!

ዘ-ሐበሻ የዕለቱ ዜና - Zehabesha News

የቴሌግራም ቻናል አርማ zehabesha_official — ዘ-ሐበሻ የዕለቱ ዜና - Zehabesha News
የቴሌግራም ቻናል አርማ zehabesha_official — ዘ-ሐበሻ የዕለቱ ዜና - Zehabesha News
የሰርጥ አድራሻ: @zehabesha_official
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 13.95K
የሰርጥ መግለጫ

@Zehabeshanewsbot
Contact us - @@EthiopiaI
ዘ-ሐበሻ የኢትዮጲያና ኢትዮጲያዊነትን ሁለንተና የሚቃኝ፣ የሀገርንና የህዝብን ጉዳዮች በብዙ መንገዶች ተደራሽ የሚያደርግ፣ በርካታ ዝግጅቶችና አቀራረቦች ያሉት የሚድያ ተቋም ነው።

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2023-04-11 23:30:14 ዛሬ በኮምቦልቻ ከተማ በፀጥታ ሀይሎችና በሰልፈኞች መካከል በተፈጠረ ግጭት 4 ሰዎች ህይወታቸው ሲያልፍ ከ10 በላይ መቁሰላቸው ታውቋል።

የኮምቦልቻ ከተማ ሰላምና ህዝብ ደህንነት ኃላፊ አቶ ሙህዬ ይማም ከእነ ሹፌራቸው ጉዳት ደርሶባቸው ሆስፒታል እንደገቡ ተሰምቷል።
1.6K views20:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 15:14:48
በዶ/ር ሊያ ታደሰ የተመራ ልዑክ መቐለ ገባ።

በጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ የተመራው የጤና ሚኒስቴር ልዑካን ቡድን ዛሬ መቐለ ገብቷል።

ልዑኩ ከክልሉ አስተዳደር ጋር በተለያዩ የጤና ጉዳዮች ዙሪያ እንደሚነጋገር ይጠበቃል።

ፎቶ ፦ ድምፂ ወያነ
2.5K views12:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 15:13:40 ተመድ በኢትዮጵያ የሰብዓዊ ምግብ ስርቆትን እየመረመርኩ ነው አለ!

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በኢትዮጵያ የሰብዓዊ ምግብ ስርቆትን እየመረመርኩ ነው አለ።የዓለም የምግብ ፕሮግራም ከሽራሮ መጋዘን ለ100 ሽህ ሰዎች የሚሆን የምግብ እርዳታ መዘረፉ ተነግሯል።በኢትዮጵያ የሚደርሰውን ምዝበራ ለመግታት አፋጣኝ እርምጃዎች ሊወሰድ ይገባል ተብሏል።የተባበሩት መንግስታት የምግብ እርዳታ ኤጀንሲ በኢትዮጵያ የነፍስ አድን ሰብዓዊ እርዳታን መሰረቁን ገልጿል።

የዓለም የምግብ ፕሮግራም የኢትዮጵያ ዳይሬክተር ክላውድ ጂቢዳር አሶሼትድ ፕረስ አገኘሁት ባለው ደብዳቤ "በአንዳንድ ገበያዎች የሚካሄደው መጠነ ሰፊ የምግብ ሽያጭ በጣም ያሳስበናል" በማለት የተዘረፈው እህል ገበያ ላይ መዋሉን ጠቁመዋል።"ይህም መልካም ስምን ብቻ ሳይሆን ተጨማሪ ለተቸገሩ ሰዎች ግብአቶችን ለማሰባሰብ አቅማችንን ያሰጋል" ብለዋል።

አክለውም "በሀገሪቱ ውስጥ የሚደርሰውን ምዝበራ እና ዝርፊያ ለመግታት አፋጣኝ እርምጃዎች መወሰድ አለባቸው" ብለዋል።ደብዳቤው ከቀናት በፊት የተጻፈና በድርቅ እና ግጭት ከሀገሪቱ 120 ሚሊዮን ህዝብ 20 ሚሊዮን ለሚሆኑት የሰብዓዊ እርዳታ ለሚያቀርቡ አጋሮች የተላከ ነው ተብሏል።

ጂቢዳር አጋር ድርጅቶች ተመሳሳይ ሁነት ገጥሟቸዋል ከሆነ መረጃ እንዲያጋሩም ጠይቀዋል።ደብዳቤው ስለ "ዝርፊያው" ዓይነት አይጠቅስም።ሆኖም ሁለት የእርዳታ ሰራተኞች እንደተናገሩት እርዳታው ከሽራሮ መጋዘን የተዘረፈና ለ100 ሽህ ሰዎች የሚሆን ነበር።
2.4K views12:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 15:09:41 #ደብረብርሃን

ወደ ደብረ ብርሃን ከተማ መግቢያ ላይ በከባድ መሳሪያ የታገዘ የተኩስ ልውውጥ እየተካሄደ መሆኑን የደብረ ብርሃን ዘ-ሐበሻ ቤተሰብ አባላት ጠቁመዋል።

አንድ የቤተሰባችን አባል ፤ በዚህ አይነት መንገድ ሰዎች ይጎዳሉ፣ ንፁሃን ይሞታሉ ፣ በአካባቢውም ተማሪዎች ይኖራሉና አስቸኳይ መፍትሄ ሊፈለግ ይገባል ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።

ሌላኛው የደብረብርሃን ቤተሰባችን የሚመለከተው አካል ሁሉ ችግሮች አሁን ካሉበት ተባብሰው የሰዎችን ህይወት እንዳይቀጥፉ የሚቻላቸውን ሁሉ ማድረግ አለባቸው ፤ የአማራ ክልል አካባቢዎች ከዚህ በፊት በነበረው አስከፊ ጦርነት ብዙ ዋጋን የከፈሉ በመሆናቸው አሁንም ተጨማሪ የንፁሃን ሞት ፣ መፈናቀል ፣ ጉዳት እንዳይፈጠር በሰከነ መንገድ መፍትሄ መፈለግ እንደሚገባ አሳስበዋል
2.2K viewsedited  12:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 14:42:26 ባህርዳር ከተማ በመንግስት የተገለፀውን "ልዩሃይልን የማደራጀት "ተግባር በመቃዎም ሰላማዊ ሰልፍ እየተደረገ ነው።
2.3K views11:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 14:00:15 ዘ-ሐበሻ የዕለቱ ዜና - Zehabesha News pinned «ወሎ ኮምቦልቻ ከተማ ለተቃውሞ አደባባይ የወጡ ሰልፈኞች ከፀጥታ ሀይሎች ጋር ተጋጭተው እስካሁን የ2 ሰዎች ህይወት ማለፉ ታውቋል።ሌሎች 8 ሰዎች መጎዳታቸው ተሰምቷል።ነገሮችን ማረጋጋት ይገባል።የፀጥታ ኃይሉ ታጋሽ መሆን አለበት።»
11:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 14:00:09 ወሎ ኮምቦልቻ ከተማ ለተቃውሞ አደባባይ የወጡ ሰልፈኞች ከፀጥታ ሀይሎች ጋር ተጋጭተው እስካሁን የ2 ሰዎች ህይወት ማለፉ ታውቋል።ሌሎች 8 ሰዎች መጎዳታቸው ተሰምቷል።ነገሮችን ማረጋጋት ይገባል።የፀጥታ ኃይሉ ታጋሽ መሆን አለበት።
2.3K views11:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 11:27:06 ዘ-ሐበሻ የዕለቱ ዜና - Zehabesha News pinned «በሰሜን ወሎ ዞን በተለዩ ወረዳና ከተማ አስተዳደሮች ተግባራዊ የሚደረግ የፀጥታ ኮማንድ ፖስት ውሳኔ ተላለፈ የሰሜን ወሎ ዞን የፀጥታ ኮማንድ ፖስት የዞኑን ሰላምና የህግ የበላይነት ለማረጋገጥ እንዲቻል ከሚያዚያ 3 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረጉ የሚከተሉትን ክልከላዎችን ውሳኔ አሳልፏል። ኮማንድ ፖስቱ ውሳኔ የሚተገበርባቸው አከባቢዎች ቆቦ ከተማ፣ ራያ ቆቦ፣ ራያ አለማጣ፣…»
08:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 11:27:02 በሰሜን ወሎ ዞን በተለዩ ወረዳና ከተማ አስተዳደሮች ተግባራዊ የሚደረግ የፀጥታ ኮማንድ ፖስት ውሳኔ ተላለፈ

የሰሜን ወሎ ዞን የፀጥታ ኮማንድ ፖስት የዞኑን ሰላምና የህግ የበላይነት ለማረጋገጥ እንዲቻል ከሚያዚያ 3 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረጉ የሚከተሉትን ክልከላዎችን ውሳኔ አሳልፏል።

ኮማንድ ፖስቱ ውሳኔ የሚተገበርባቸው አከባቢዎች ቆቦ ከተማ፣ ራያ ቆቦ፣ ራያ አለማጣ፣ ራያ ባላ፣ አለማጣ ከተማ፣ መርሳ ከተማ፣ ሐብሩ እና ጉባላፍቶ ወረዳ ይሆናሉ።

ጥብቅ ክልከላዎች:-

1. ከተፈቀደለት የመንግስት የፀጥታ ኃይል ውጭ የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ የተከለከለ ነው።
2. ኮማንድ ፖስቱ ባካተታቸው ወረዳዎች/ከተሞች ከዋናው አስፋልት መንገድ በግራ እና በቀኝ በአንድ ኪሎ ሜትር ርቀት የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ አይፈቀድም።

2. ድምፅ አልባ መሳሪያዎችን ስለታማ የሆኑ እንደ ጩቤ ፣ ገጀራ ፣ አንካሴ፣ መጥረቢያ፣ ወዘተ የመሳሰሉትን ይዞ መንቀሳቀስ ክልክል ነው።
3. በተከለከሉ ቦታዎች በእምነት ተቋማት፣ በገበያ እና ህዝብ በብዛት በሚሰበሰብባቸው ቦታዎች ፣ በሆቴሎች፣ መጠጥ ቤቶችና ግሮሰሪዎች፣ ልዩ ልዩ መዝናኛ ቦታዎች ጦር መሳሪያ ይዞ መገኘትና መንቀሳቀስ የተከለከለ ነው።

4. በክልከላው ቀጠና ውስጥ የሚገኙ ማንኛውም መጠጥ ቤቶችና ጭፈራ ቤቶች ከምሽቱ 2:00 ሰዓት ቡኋላ አገልግሎት መስጠት የተከለከለ ነው ።

5. በማንኛውም ቦታና ስዓት ጥይትም ሆነ ርችት መተኮስ በጥብቅ የተከለከለ ነው ።
6. የሠራዊቱን አልባሳት ከሰራዊቱ አባላት ውጭ መልበስ የተከለከለ ነው። ማለትም የልዩ ኋይል ፣ የፓሊስ ፣ የመከላከያ ሠራዊት ፣ የፌዴራል ፓሊስ አልባሳትን ከሚመለከታቸው አካላት ውጭ መልበስ ወንጀል ነው።

7. በክልከላ በተካተቱ ወረዳዎች/ከተሞች የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ባለ 3 እግር ባጃጆች ከንጋቱ 12:00 ሰዓት እስከ ምሽቱ 1:00 ሰዓት ብቻ የሚንቀሳቀሱ ይሆናል።

8. የህዝብና የጭነት ተሽከርካሪዎች ከንጋቱ 12:00 እስከ ምሽት 2:00 ሰዓት ብቻ የሚንቀሳቀሱ ይሆናል።
9. የእግረኛን እንቅስቃሴን በተመለከተ ኮማንድ ፖስት በታወጀባቸው ወረዳዎች እና ከተማ አስተዳደሮች ከንጋቱ 12:00 እስከ ምሽት 3:00 ብቻ ይሆናል።

9. በህግ የሚፈለጉ ወይም ተጠርጣሪዎችን ሽፋን የሰጠ ፣ የደበቀ ፣ ያስጠለለ፣ ስንቅ ያቀበለ፤ የሀሰተኛ መረጃ ሰጥቶ ያሰመለጠ ፣ የፀጥታ ሀይሎችን የህግ ማስከበር ተልዕኮ ያደናቀፈ እና ያወከ በህግ የሚጠየቅ ይሆናል።

10. በየደረጃው መንግስት ያልፈቀደው ማንኛውም አይነት ስብሰባ እና መንግስት ያልፈቀደው ሠልፍ ማድረግ፣ መቧደን፣ ወታደራዊ ስልጠና መስጠት የተከለከለ ነው።

11. አድማ መቀስቀስ፣ መንገድ መዝጋት እና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴን መግታት፣ ከመንግስት አካላት ውጭ መዋጮ ወይም ገንዘብ መሠብሰብ፤ ኬላ ማቋቋም፣ ህዝብን እረፍት መንሳት እንዲሁም መደበኛ ስራን ማስተጓጎል በጥብቅ የተከለከለ ነው።
12. ፀጉረ ልዉጥ/አጠራጣሪ ሰው ከቤቱ ያሳደረ ፣ያከራየ፣ በሆቴሉ አልጋ ያስያዙ እንዲሁም ለሚመለከተዉ የፀጥታ አካል ጥቆማ ያልሰጠ በህግ የሚጠይቅ ይሆናል።
13. የመንግስትን የታጠቀ ሀይል ያስከዳ፣ በተለያየ መንገድ አማሎ የጦር መሳሪያ የገዛ፣ የለወጠ፣ ባልተገባ መንገድ መታወቂያ የሠጠ፣ መንገድ የመራ ማንኛውም አካል በህግ ተጠያቂ ይሆናል።

14. የመንግስት የጸጥታ ሀይል ህግና ስርአትን ለማስከበር በሚያከናውናቸው ተግባሮች ዙሪያ ማንኛውም ሠው የመተባበር ግዴታ አለበት። የማይተባበር ከሆነ በህግ ይጠየቃል።

15. ማንኛውም አካል ለኮማንድ ፖስቱ ውሳኔዎች ተገዥ መሆን አለበት።
16.ማንኛውንም አይነት መረጃ ለዞኑ እና በየደረጃው ለተቋቋመው ኮማንድ ፖስት ወይም የመንግስት የጸጥታ ሀይል መጠቆም ይችላል።
2.6K views08:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 10:47:08 ‹‹ማክሰም፣ ማጠፍ፣ ማፍረስ፣ መበተን…›› ወዘተ……
የብልፅግና ፓርቲ መግለጫ

የብልጽግና ፓርቲ የሁሉም አቋሞቹ እና ተግባሩ መነሻ እና መድረሻ የኢትዮጵያ ህልውና፣ ታላቅነት፣ ብልጽግና እና የህዝቦቿ ሰላም ብቻ ነው፡፡ በዚህ የማይናወጥ ሀገራዊ እና ህዝባዊ መሰረት ላይ ቆመን ለመላ የሀገራችን ህዝቦች የጋራ ደጀን ፣መከታ፣ ክንድ እና የማይታጠፍ አለኝታ የሆነ ሀገራዊ ሰራዊት ለመገንባት ህገ መንግስቱን መሰረት ያደረገ ጥረቶች ማድረግ ከጀመርን ውለን አድረናል፡፡

በስድስተኛዉ ሀገራዊ ምርጫ ቅስቀሳ ወቅትም  የክልሎችን ልዩ ሃይል በህገ መንግስቱ መሰረት  መልሰን እንደምናደራጅ  አቋማችን ለህዝብ ግልጽ ማድረጋችን ይታወሳል፡፡ 

ስለሆነም አሁን ላይ ለብዥታ እና ተገቢውን መስመር ለሳተ የትርጉም አንድምታ የተጋለጠው ልዩ ሃይሎቻችንን መልሶ የማደራጀት እንቅስቃሴም አንዳንዶች በሚያሳዝን ሁኔታ አጣመው እንደሚለፍፉት እንግዳ ደራሽ የሆነ የቶሎ ቶሎ ቤት አይነት ውሳኔ ሳይሆን በብዙ ጥናት፣ በጥልቅ ውይይት፣ በሰከነ ንግግር እና በጋራ መግባባት የተደረሰበት ውሳኔ እንደሆነ መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡

በዚህ ጉዳይ ላይ ከህዝባችንም የክልል ልዩ ሃይሎች ህገ መንግስቱን መሰረት ባደረገ እና የዜጎችን ሰላም እና ደህንነት በተሻለ መልኩ በሚያስጠብቅ አኳሃን መልሶ የማደራጀት ስራ መሰራት እንዳለበት በተለያየ መልኩ ለመንግስትና ለፓርቲያችን ሲገልጽ ቆይቷል፡፡ በመሆኑም ውሳኔው የህዝቡን ፍላጎት ከግምት ዉስጥ ያስገባና ህገመንግስታዊ እንደሆነ መረዳት ያስፈልጋል፡፡

በህገ መንግስታችን ላይ በማያሻማ መልኩ እንደተመለከተው ሀገርን እና ህዝብን ከየትኛውም ጥቃት እና ጠላት የሚከላከል ሀገራዊ ሀይል የመገንባት ሃላፊነት እና ስልጣን የፌዴራል መንግስቱ ብቻ እንደሆነ በግልጽ ተመልክቷል፡፡ የክልል መንግስታትም የክልላቸዉን ሰላምና ጸጥታ የሚያስጠብቅ ክልላዊ ፖሊስ አደራጅተዉ እንደሚመሩ በህገ መንግስቱ ተደንግጓል፡፡

በዚህም መሰረት የክልል ልዩ ሀይሎችን እንደገና የማደራጀት አስፈላጊነት ልክ ያልነበረን ጉዳይ ልክ የማድረግ ውሳኔ እና ጥረት እንጂ ሌላ ምንም አመክንዮ እንደሌለው በውል ሊታወቅ ይገባል፡፡

አንዳንድ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች እና መሪዎቻቸው እንዲሁም ማህበራዊ አንቂዎች ነን የሚሉ ግለሰቦች ጉዳዩን አንድን  ክልል ብቻ ትጥቅ የማስፈታት ጉዳይ አድርገዉ የሚያቀርቡበትና ጉዳዩን ለመግለጽ የሚጠቀሙባቸው ‹‹ማክሰም፣ ማጠፍ፣ ማፍረስ፣ መበተን…›› ወዘተ የሚሉት አገላለጾች  ምንጫቸው- ከየት እና ምርጫቸው- እንዴት ሆኑ የሚለውን መተንተን ለዚህ አውድ ፋይዳው ብዙ ባይሆንም ግባቸው ግን ርካሽ የፖለቲካ ትርፍ ለማጋበስ እና ህዝብን ለማሳሳት በመሞከር ጊዜያዊ ቅቡልነት ለማግኘት የመጣር ፍላጎት እንደሆነ በቀላሉ መረዳት ይቻላል፡፡ ስለሆነም ከዚህ ሀገርን ዋጋ ከሚያስከፍል ህገ ወጥ እና መርህ አልባ እንቅስቃሴ እንዲቆጠቡ ፓርቲያችን ያሳስባል፡፡ 

ፓርቲያችን በጽኑ መግለጽ የሚፈልገዉ ዋና ጉዳይ ልዩ ሀይልን ትጥቅ የማስፈታት ሳይሆን የተሻለ የማስታጠቅ፤ የመበተን ሳይሆን በጠንካራ መሰረት ላይ የማደራጀት ስራ ላይ የመሆናችንን የማያሻማ እውነት ነው፡፡ የሁሉም ክልል ልዩ ሀይሎች በብዙ ሀገራዊ ፈተናዎቻችን እና ድሎቻችን ውስጥ መቼም ሊደበዝዝ የማይችል ደማቅ አሻራ እንዳላቸው ፓርቲያችን በጽኑ ያምናል፡፡

በምንም ስለማይተመነውና በነፍሳቸው ተወራርደው ስለሰጡት አገልግሎትም በተለየ አክብሮት እና ፍቅር ያመሰግናሉ፡፡

የልዩ ሀይሎቻችን በመከላከያ፣ ፌዴራል ፖሊስ እና የክልል ፖሊስ መዋቅሮች ውስጥ ተደራጅተዉ ሀገርን እና ህዝብን ማገልገል ለመላው የሀገራችን ህዝቦች የሚኖረው አስተዋጽኦ እጅጉን ሰፊ እና መሰረታዊ ለውጥ የሚያስገኝ እንደሆነ ሊታወቅ ይገባል፡፡ ልዩ ሀይሎቻችንን እስከዛሬ ስትሰጡት ከነበረው አገልግሎት በተሻለ አደረጃጀት፣ ትጥቅ እና ወታደራዊ ብቃት እንድታገለግሉ አስተማማኝ እድል የሚያጎናጽፋቸዉ በመሆኑ ህግ እና ስርዓትን በጠበቀ አኳሃን ለውሳኔው ተግባራዊነት የበኩላቸሁን እንድትወጡ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡

ይህ ውሳኔ በአማራ ክልል ላይ ብቻ የተወሰነ ውሳኔ አድርገው ለማቅረብ የሚጋጋጡ ዘገር ነቅናቂ ግጭት- ናፋቂ ሀይሎች የሚነዙት መርዛማ መረጃ ፍጹም ሀሰት እንደሆነ ፓርቲያችን በአጽንኦት ማሳወቅ ይፈልጋል፤ ውሳኔው ሁሉም ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች ተነጋግረው የተወሰነ ውሳኔ ብቻ ሳይሆን በተመሳሳይ የጊዜ መስመር በሁሉም ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች የሚተገበር መሆኑን አበክሮ ያስታውቃል፡፡ የክልል ልዩ ሀይሎች ህገመንግስታዊ በሆኑት የጸጥታ መዋቅሮች ገብተው እንዲያገለግሉ መደረግ እንዳለበት ከብልጽግና እኩል (አንዳንዴም በላይ) ሀሳብ ሲያነሱ እና ሲሞግቱ የነበሩ ፓርቲዎችና አመራሮችም ጭምር ዛሬ ላይ ከስጋው ጾማለሁ ከመረቁ ስጡኝ አይነት መግለጫ ለማውጣት መጋጋጣቸው ፓርቲያችንን እጅጉን አሳዝኖታል፡፡ ሆኖም ግን ብልጽግና ፓርቲ በተግዳሮቶች ውስጥም ቢሆን ከህዝባችን እና ከሁሉም የልዩ ሀይል አመራሮቻችና አባላት ጋር በስክነት በመወያየት እና የተፈጠረውን የተግባቦት ክፍተት በመሙላት ለሀገር እና ለህዝብ ዘላቂ ሰላም በሚበጀው ጎዳና መጓዙን ይቀጥላል፡፡

በዚህ አጋጣሚም ሻማ እንዲሸጥላቸው ጨለማ የሚናፍቁ እና የሚጠብቁ አንዳንድ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና መሪዎቻቸው ነገሮችን ከማባባስ እና ሞትን ለመጥመቅ- ግጭት ከመጠንሰስ እንዲቆጠቡ በአጽንኦት ለማሳሰብ እንወዳለን፡፡ ‹‹እዉነት እና ንጋት እያደረ ይጠራል›› እንደሚባለው ውሳኔው ነገ ከነገ ወድያ በሁሉም ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች ተግባራዊ ሆኖ በታሰበው መሰረት ተፈጻሚ ሲሆን ለሚታይ ግልጽ ውሳኔ ተገቢ ያልሆነ ዋጋ በመክፈል ሰላማችን እንዳይደፈርስ መላው የአማራ ህዝብ እና የልዩ ሃይል አባሎቻችን ነገሮችን በሰከነ መልኩ እንዲያዩ እና ለዚህ ሀገርን እና ህዝብን ለሚጠቅም ቀና ውሳኔ ቀና ምላሽ እንዲሰጡ በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡

ህብረ ብሄራዊ ክንዳችን- ለሁለንተናዊ ሰላማችን!
ሚያዝያ 2 ቀን 2015 ዓ.ም

የብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት
2.7K views07:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ