Get Mystery Box with random crypto!

ዘ-ሐበሻ የዕለቱ ዜና - Zehabesha News

የቴሌግራም ቻናል አርማ zehabesha_official — ዘ-ሐበሻ የዕለቱ ዜና - Zehabesha News
የቴሌግራም ቻናል አርማ zehabesha_official — ዘ-ሐበሻ የዕለቱ ዜና - Zehabesha News
የሰርጥ አድራሻ: @zehabesha_official
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 13.95K
የሰርጥ መግለጫ

@Zehabeshanewsbot
Contact us - @@EthiopiaI
ዘ-ሐበሻ የኢትዮጲያና ኢትዮጲያዊነትን ሁለንተና የሚቃኝ፣ የሀገርንና የህዝብን ጉዳዮች በብዙ መንገዶች ተደራሽ የሚያደርግ፣ በርካታ ዝግጅቶችና አቀራረቦች ያሉት የሚድያ ተቋም ነው።

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2023-05-01 09:23:30 #ኢትዮጵያ

የፀጥታ እና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል ፥ ከሀገር ውጭ የሚገኙትን ፖለቲከኛው አቶ ልደቱ አያሌውን ፣ በቅርቡ ከልዩ ኃይል ጋር በተያያዘ በአማራ ክልል የተፈጠረውን አለመግባባት በስምምነት እንደፈታ የተነገረለት የምስራቅ አማራ ፋኖ አመራር ምሬ ወዳጆን ጨምሮ በሀገር ውስጥ በተደጋጋሚ ጊዜ በቁጥጥር ስር ውለው የነበሩ የሚዲያ ሰዎች እና በውጭ ሀገር ያሉ በርካታ የሚዲያ ሰዎችን " ህገ መንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለማፍረስ እንዲሁም #በሽብር_ወንጀል " እፈልጋቸዋለሁ ብሏል።

ግብረ ኃይሉ በአማራ ክልል እየወሰድኩ ነው ባለው እርምጃ " ፅንፈኛ ናቸው " ላላቸው ኃይሎች የሚዲያ እና ፕሮፖጋንዳ ክንፍ በመሆን እየሰሩ ናቸው ያላቸውን አካላት ነው #በወንጀል እንደሚፈልጋቸው ያሳወቀው።

በውጭ ሀገር ያሉትን ተፈላጊ ግለሰቦች በዐለም አቀፉ የፖሊስ ድርጅት እንዲሁም ከሚኖሩባቸው ሀገር መንግስት የፀጥታ እና ደህንነት ተቋማት ጋር በተመሰረቱ የትብብር ማዕቀፎች ተላልፈው እንዲሰጡ እየሰራሁ ነው ብሏል።

በሌላ በኩል የፀጥታ እና ደህንነት  ግብረ ኃይሉ በአማራ ክልል " በህቡዕ አደረጃጀት " ውስጥ ሲንቀሳቀሱና የሽብር ተግባር ሲፈጽሙ አገኘኃቸው ያላቸውን 47 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ማዋሉን አሳውቋል።

ከእነዚህ 47 ግለሰቦች ውስጥ ረዳት ፕ/ር ሲሳይ አውጋቸው፣ ዶ/ር ወንድወሰን አሰፋ፣ በተደጋጋሚ ጊዜ ለእስር ተዳርጋ የተፈታችው መምህርት መስከረም አበራ ይገኙበታል።

ግብረ ኃይሉ የተያዙት ግለሰቦች የአማራ ክልል ከፍተኛ አመራሮችን " ለመግደል፣ ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል በመናድ የክልሉን መንግሥታዊ መዋቅር በመቆጣጠር የፌደራል መንግሥትን ለመጣል " በአገር ውስጥ እና በውጭ አገራት ተደራጅተው ሲንቀሳቀሱ ስለደረስኩባቸው ነው ብሏል።

ግብረ ኃይሉ ለመገናኛ ብዙሃን ያሰራጨው መግለጫ ከላይ ተያይዟል።
1.9K views06:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-01 09:22:26 " የአዲስ አበባ ጸጥታ ቢሮ ይህን ጥያቄ ይዛችሁ አደባባይ አትወጡም አለን " - አቶ ካሳሁን ፎሎ

የኢትዮጵያ ሰራተኞች ማህበራት ኮንፌደሬሽን (ኢሰማኮ) መንግስት የገቢ ግብርን እንዲቀንስ ለመጠየቅ ዛሬ አዲስ አበባ ውስጥ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ አቅዶ የነበር ቢሆንም መንግሥት ሰልፉን እንዳይደረግ መከልከሉን አሳውቋል።

የኮንፌደሬሽኑን ፕሬዝዳንት ካሳሁን ፎሎ እንዳሳወቁት ፤ ዛሬ የሚከበረውን የሰራተኞች ቀን (ሜይ ዴይ)ን ተተርሶ ነበር ሰልፉ እንዲደረግ ታቅዶ የነበረው።

የሰልፉ ዋነኛ ዓላማ ፤ ሰራተኛው በኑሮ ውድነቱ መኖር ባለመቻሉ መንግሥት የገቢ ግብርን እንዲቀንስ ለመጠየቅ ሲሆን በተጨማሪም ዝቅተኛ የደሞዝ ወለል እንዲወሰን፣ የኤጄንሲ ሰራተኞች 20/80 ክፍያ ገቢራዊት እንዲሁም የመደራጀት መብትን ለመጠየቅ ነበር።

ነገር ግን የመንግሥት ፀጥታ ቢሮ ይሄ ሰልፍ እንዳይካሄድ መከልከሉን ኢሰማኮ አሳውቋል።

የኢሰማኮ ፕሬዝዳንት ካሳሁን ፎሎ ፤ በአዲስ አበባ ብቻ ከአንድ መቶ ሽህ በላይ ሰራተኞች ይሳተፉበታል የተባለው ሰልፍ በከተማዋ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ መከልከሉ ገልጸዋል።

" ማክሰኞ ሚያዚያ 17 የከተማ አስተዳደሩን ስለ ሰልፉ አሳውቀናል ፤ ከሰላምና ጸጥታ ቢሮ ጋርም ስንነጋገር ነው የሰነበትነው ነገር ግን ካላንደር በዘጋው ቀን ድምጻችንን እንዳናሰማ ተከልክለናል " ብለዋል።

" ሰልፉን ለማድረግ ፈቃድ አያስፈልግም፡፡ እኛ ለራሳችን ደህንነታችንን እንዲጠብቁን አሳውቀናል፡፡ የአዲስ አበባ ጸጥታ ቢሮ ይህን ጥያቄ ይዛችሁ አደባባይ አትወጡም አለን፡፡ ህግ እናስከብረለን ስላሉ ሰራተኛው እንዳይጎዳ አስቀረነው " ሲሉ ተናግረዋል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ ትላንት ምሽት ባወጣው ማሳሰቢካ ደግሞ የላብ አደሮች ቀንን አስመልክቶ በአዲስ አበባ ከተማ ምንም አይነት የአደባባይ ኩነቶችና ሰልፍ እንዲሁም ፖሊስም ሆነ የአስተዳደር አካላት የሚያውቁት ምንም ዓይነት ስብሰባ የለም ብሏል።

መረጀውን ከአልዓይን ፣ የኢትዮጵያ ሰራተኞች ማህበራት ኮንፌደሬሽን (ኢሰማኮ) እና ከአ/አ ፖሊስ የተገኘ ነው።
1.9K views06:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-28 09:43:02 መሀል ሜዳ
በትናንትናው ዕለት ሰሜን ሸዋ መሀል ሜዳ ጎሳ ተብሎ በሚጠራ አካባቢ በጥይት የተገደሉት የአማራ ብልፅግና ፓርቲ ኃላፊ አቶ ግርማ የሺጥላ ጋር ህይወታቸው ያለፈ የፀጥታ ሀይሎች የቀብር ስነ ስርዓት እንደሚፈፀም ተሰምቷል።የአቶ ግርማ ስርዓተ ቀብር መቼ እንደሚፈፀም አልተገለፀም።

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በአንፆኪያ ገምዛ ወረዳ የኢኮኖሚ ጉዳዮች ዘርፍ ኃላፊ በመሆን በታህሳስ 1988 ዓ.ም የአመራርነት ስራን የጀመሩት አቶ ግርማ፤ በዚያው ዓመት ሐምሌ ወር ላይ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ ሆነው ተሹመዋል። በዚህ የኃላፊነት ቦታ ላይም ለሰባት ዓመት ገደማ ቆይተዋል።

በጥር 1995 ዓ.ም. ከወረዳ ወደ ዞን በመሸጋገርም፤ የቀድሞው ብሔረ አማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ብአዴን) የሰሜን ሸዋ ዞን ጽህፈት ቤት የአደረጃጀት ጉዳይ ኃላፊ መሆን ችለዋል። ለአንድ ዓመት ገደማ በዚህ ኃላፊነት ቦታ የቆዩት አቶ ግርማ፤ በጥር 1996 ዓ.ም የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሹመት አግኝተዋል።

በ2002 ዓ.ም. የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ከደብረብሃን ዩኒቨርስቲ በምጣኔ ሃብት (ኢኮኖሚክስ) ትምህርት ዘርፍ ያገኙት አቶ ግርማ፤ በዚያው ዓመት የሰሜን ሸዋ ዞን አስተዳደር የህዝብ ግንኙነት አማካሪ ሆነዋል። እስከ ግንቦት 2003 ዓ.ም ድረስ በዚሁ ቦታ ሲያገለግሉ ከቆዩ በኋላ፤ የሰሜን ሸዋ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ ሆነው ተሹመዋል።

በምክትል አስተዳዳሪነት ደረጃ ለአራት ዓመታት ገደማ የቆዩት አቶ ግርማ፣ ዞኑን የመምራት ኃላፊነት በመስከረም 2008 ዓ.ም ተረክበዋል። የሰሜን ሸዋ ዞንን ለሁለት ዓመት ገደማ የመሩት አቶ ግርማ፤ በ2012 ዓ.ም በቢዝነስ አድሚኒስትሬሽን የሁለተኛ ዲግሪያቸውን በአዲስ አበባ ከተማ ከሚገኘው የኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርስቲ ይዘዋል።
2.7K views06:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 23:26:32 <<…የክልሉ መንግሥት የማያዳግም እርምጃ ይወስዳል፡፡>>የአማራ ክልል መንግስት

ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የተሰጠ መግለጫ

በዛሬው ዕለት ሚያዚያ 19 ቀን 2015 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ የብልፅግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ አባል እና የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ በተከበሩ ግርማ የሺጥላ፣ በግል ጥበቃዎቻቸው እና በቤተሰቦቻቸው ላይ የመንግሥትና የድርጅት ሥራዎችን በአካባቢው ላይ ሠርተው ከመሃል ሜዳ ወደ ደብረ ብርሃን እየመጡ በነበረበት ሰዓት መንዝ ጓሳ ላይ በታጠቁ ኢ-መደበኛ ኃይሎች ጥቃት ተፈጽሟል፡፡

በዚህም ግርማ የሺጥላን ጨምሮ እስካሁን በደረሰን መረጃ የአምስት ሰዎች ሕይወት አልፏል፡፡ በደረሰው ልብ ሰባሪ ጥቃት የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የተሰማውን መሪር ሐዘን እየገለፀ ለቤተሰቦቻቸውና ወዳጆቻቸው እንዲሁም ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን ይገልጻል፡፡

እንዲህ አይነት አጥፊዎች እያደረሱት ያለው መረን የለቀቀ የሽብር ድርጊት ክልሉን እየመራ ያለውን መንግሥትና መላውን ሕዝብ የበለጠ ሊያጠናክር እንጂ በጥፋት ሃይሎች ሴራና ፍላጎት የሚሳካ ምንም አይነት ተልዕኮ የለም፡፡

ስለሆነም ይህንን የሽብር ሥራ እየሠሩ ያሉ እንዲህ አይነት ኃይሎች ላይ የክልሉ መንግሥት የማያዳግም እርምጃ ይወስዳል፡፡ የጥቃቱን አድራሾችም ለሕግ ያቀርባል፡፡ ማንኛውም በእንደዚህ አይነት ድርጊት የተሳተፉ ኀይሎችንንና ተባባሪዎችን ሁሉ ከያሉበት ለሕግ በማቅረብ አስፈላጊው ፍትሕ እዲረጋገጥ ይደረጋል፡፡

በመሆኑም መላው የክልላችን ሕዝብ የተፈጠረውን የሽብር ድርጊት ከማውገዝ ጀምሮ ወንጀለኞች ለሕግ ቀርበው ፍትሕ እንዲረጋገጥ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግና እንዲረጋጋ ጥሪ እናቀርባለን፡፡

የጥፋት ኃይሎች ከዚህ በላይ ዓላማ ያላቸው እና ክልሉን የማፍረስ ተልዕኮ ይዘው የሚንቀሳቀሱ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን ከዚህ በኋላ የክልሉ መንግሥት እንደማይታገስ እና ጥብቅ እርምጃ እንደሚወስድ እናረጋግጣለን፡፡

የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት
ሚያዚያ 19 ቀን 2015 ዓ.ም
ባሕር ዳር
3.1K views20:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 23:26:32 <<…የክልሉ መንግሥት የማያዳግም እርምጃ ይወስዳል፡፡>>የአማራ ክልል መንግስት

ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የተሰጠ መግለጫ

በዛሬው ዕለት ሚያዚያ 19 ቀን 2015 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ የብልፅግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ አባል እና የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ በተከበሩ ግርማ የሺጥላ፣ በግል ጥበቃዎቻቸው እና በቤተሰቦቻቸው ላይ የመንግሥትና የድርጅት ሥራዎችን በአካባቢው ላይ ሠርተው ከመሃል ሜዳ ወደ ደብረ ብርሃን እየመጡ በነበረበት ሰዓት መንዝ ጓሳ ላይ በታጠቁ ኢ-መደበኛ ኃይሎች ጥቃት ተፈጽሟል፡፡

በዚህም ግርማ የሺጥላን ጨምሮ እስካሁን በደረሰን መረጃ የአምስት ሰዎች ሕይወት አልፏል፡፡ በደረሰው ልብ ሰባሪ ጥቃት የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የተሰማውን መሪር ሐዘን እየገለፀ ለቤተሰቦቻቸውና ወዳጆቻቸው እንዲሁም ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን ይገልጻል፡፡

እንዲህ አይነት አጥፊዎች እያደረሱት ያለው መረን የለቀቀ የሽብር ድርጊት ክልሉን እየመራ ያለውን መንግሥትና መላውን ሕዝብ የበለጠ ሊያጠናክር እንጂ በጥፋት ሃይሎች ሴራና ፍላጎት የሚሳካ ምንም አይነት ተልዕኮ የለም፡፡

ስለሆነም ይህንን የሽብር ሥራ እየሠሩ ያሉ እንዲህ አይነት ኃይሎች ላይ የክልሉ መንግሥት የማያዳግም እርምጃ ይወስዳል፡፡ የጥቃቱን አድራሾችም ለሕግ ያቀርባል፡፡ ማንኛውም በእንደዚህ አይነት ድርጊት የተሳተፉ ኀይሎችንንና ተባባሪዎችን ሁሉ ከያሉበት ለሕግ በማቅረብ አስፈላጊው ፍትሕ እዲረጋገጥ ይደረጋል፡፡

በመሆኑም መላው የክልላችን ሕዝብ የተፈጠረውን የሽብር ድርጊት ከማውገዝ ጀምሮ ወንጀለኞች ለሕግ ቀርበው ፍትሕ እንዲረጋገጥ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግና እንዲረጋጋ ጥሪ እናቀርባለን፡፡

የጥፋት ኃይሎች ከዚህ በላይ ዓላማ ያላቸው እና ክልሉን የማፍረስ ተልዕኮ ይዘው የሚንቀሳቀሱ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን ከዚህ በኋላ የክልሉ መንግሥት እንደማይታገስ እና ጥብቅ እርምጃ እንደሚወስድ እናረጋግጣለን፡፡

የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት
ሚያዚያ 19 ቀን 2015 ዓ.ም
ባሕር ዳር
2.9K views20:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 18:26:47
ሰበር

የአማራ ብልፅግና ኃላፊ አቶ ግርማ የሺጥላ ዛሬ በትውልድ ቦታ ሰሜን ሸዋ መሀል ሜዳ በጥይት ተደብድቦ ህይወቱ አልፏል።
3.2K views15:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 11:00:17 የአማራ ክልል ፕሬዝደንት መቀሌ ገብተዋል

አቶ አደም ፋራህ የተመራና የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮችና ሌሎች ባለስልጣናት የተካተቱበት ቡድን ወደመቀሌ ተጓዘ።

በቡድኑ ውስጥ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ፣ የአፋር ክልል፣ የኦሮሚያ ክልል፣ የደቡብ ክልል፣ የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ የጋምቤላ ክልል፣ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል፣ የሶማሌ ክልል፣ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድሮች ይገኙበታል።

በተጨማሪም የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ የድሬዳዋ ከተማ ከንቲባ ከድር ጁሀርና ሚኒስትሮች እና ሌሎች የሥራ ኃላፊዎች አብረው ተጉዘዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ለሰሜኑ ጦርነት የሠላም ስምምነት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት የዕውቅና መርሀ-ግብር ሲከናወን የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች ወደመቀሌ በማቅናት መቀራረቡን እንዲያጠናክሩ ተናግረው እንደነበር የሚታወስ ነው።
(ኢፕድ)
3.5K views08:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 10:52:44 ዘ-ሐበሻ የዕለቱ ዜና - Zehabesha News pinned «በአማራ ክልል ተነስቶ የነበረውን ውጥረት ተከትሎ ለእስር የተዳረጉ ሰባት ጋዜጠኞች በአስቸኳይ እንዲፈቱ ሲል አምኒስቲ ኢንተርናሽል አሳስቧል። የጋዜጠኞቹ እስር የሚዲያ ነጻነት እና ሐሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት ላይ የተወሰደ ጥቃት ነው ያለው ድርጅቱ፤ ድርጊቱን የፈጸመው የሚመለከተው የመንግሥት አካል ጋዜጠኞቹ በፍጥነት እንዲፈታ እና የቀረበባቸውን ክስ እንዲያነሳ ብሏል። የሰብአዊ መብት ተሟጋች…»
07:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 10:52:38 በአማራ ክልል ተነስቶ የነበረውን ውጥረት ተከትሎ ለእስር የተዳረጉ ሰባት ጋዜጠኞች በአስቸኳይ እንዲፈቱ ሲል አምኒስቲ ኢንተርናሽል አሳስቧል።

የጋዜጠኞቹ እስር የሚዲያ ነጻነት እና ሐሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት ላይ የተወሰደ ጥቃት ነው ያለው ድርጅቱ፤ ድርጊቱን የፈጸመው የሚመለከተው የመንግሥት አካል ጋዜጠኞቹ በፍጥነት እንዲፈታ እና የቀረበባቸውን ክስ እንዲያነሳ ብሏል።

የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቱ፤ ‹‹ጋዜጠኞች እና የመገናኛ ብዙኀን ባለሞያዎች፣ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ፤ ለሕዝብ ተገቢውን መረጃ እንዲያደርሱ እና የመንግሥት ኃላፊዎችን ተጠያቂ ማድረግ እንዲችሉ፣ ሥራቸውን ያለምንም ስጋት፣ ጣልቃ ገብነት እና ትንኮሳ ሊሠሩ ይገባል።›› ብሏል።

አምነስቲ ኢንተርናሽናል አያይዞ ሦስት ወራት ያስቆጠረውና መንግሥት በተለያዩ ማኅበራዊ ሚድያዎች ላይ የጣለውን ማእቀብ እንዲያነሳና፤ የዜጎች ሐሳብን በነጻነት የመግለጽ እና መረጃ የማግኘት መብትን እንዲያከብር ጥሪ አስተላልፏል።(አዲስ ማለዳ)
3.3K views07:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 22:58:08 <<የነዳጅ ዕጥረት ያጋጠመ ለማስመሰል በሚሞክሩ ማደያዎች ላይ እርምጃ ይወሰዳል>> ባለስልጣኑ

የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን አንዳንድ የነዳጅ ማደያዎች ሆነ ብለው የነዳጅ ዕጥረት ያጋጠመ ለማስመሰል መሞከራቸውን በክትትል እንደደረሰበት ገልጧል፡፡

በሀገር ውስጥ በቂ የነዳጅ አቅርቦት መኖሩ እየታወቀ የነዳጅ ዕጥረት ይከሰታል የሚሉ አዋኪ መልዕክቶች ሆነ ተብሎ የሚነዙ መሆኑን ሕብረተሰቡ እንዲገነዘብ ባለስልጣኑ አስታውቋል፡፡

በቀጣይም በነዳጅ ማደያዎች ላይ የአገልግሎት አሰጣጥ መዘግየት እና ዕጥረት መፍጠርን የመሳሰሉ ችግሮች በሚፈጥሩ አካላት ላይ ክትትል በማድረግ አስተማሪ እርምጃ እንደሚወስድ ነው የገለጸው፡፡

በአንዳንድ የነዳጅ ማደያዎች ላይ የሚስተዋሉ ሠልፎች ምክንያት ኤሌክትሮኒክ የነዳጅ ግብይት ተግባራዊ መደረጉን ተከትሎ በአሽከርካሪዎች በኩል ግብይት ለመፈፀም የሚያስችል አካውንት ካለመክፈት ጋር የተያያዘ እንጅ የነዳጅ ዕጥረት አለመሆኑንም ነው ባለስልጣኑ ያረጋገጠው ሲል ፋና ዘግቧል፡፡
3.3K views19:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ