Get Mystery Box with random crypto!

ዘ-ሐበሻ የዕለቱ ዜና - Zehabesha News

የቴሌግራም ቻናል አርማ zehabesha_official — ዘ-ሐበሻ የዕለቱ ዜና - Zehabesha News
የቴሌግራም ቻናል አርማ zehabesha_official — ዘ-ሐበሻ የዕለቱ ዜና - Zehabesha News
የሰርጥ አድራሻ: @zehabesha_official
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 13.95K
የሰርጥ መግለጫ

@Zehabeshanewsbot
Contact us - @@EthiopiaI
ዘ-ሐበሻ የኢትዮጲያና ኢትዮጲያዊነትን ሁለንተና የሚቃኝ፣ የሀገርንና የህዝብን ጉዳዮች በብዙ መንገዶች ተደራሽ የሚያደርግ፣ በርካታ ዝግጅቶችና አቀራረቦች ያሉት የሚድያ ተቋም ነው።

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2023-03-25 11:01:19 ዘ-ሐበሻ የዕለቱ ዜና - Zehabesha News pinned «ፖሊስ ምን አለ? ካህኑን ማን ገደላቸው ? " ኃይሌ ጋርመንት " የሁርሲሳ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ቀዳሽ ካህን ቀሲስ ዐባይ መለስ " ማንነታቸው አልታወቀም " በተባሉ አካላት በተፈፀመባቸው ጥቃት ተገድለዋል። ካህኑን የሚያውቋቸው አገልጋዮች /ምዕመናን ስለነበረው ሁኔታ / ስለጥቃቱ ምን አሉ ? (ለማህበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ከተናገሩት የተወሰደ) ቃላቸውን የሰጡ ምዕመን አንድ ፦…»
08:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-25 11:01:09 #ተጨማሪ

የቀሲስ ዐባይ መለሰ ግድያ በስፋት ተሰማ እንጂ የሁርሲሳ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ባለችበት አካባቢ ብዙ ፈተና ይገጥማት እንደነበር አገልጋዮችና ምዕመናን ለ " ማህበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን " ተናግረዋል።

እዛው ቤተክርስቲያን አካባቢ ስልክ የተቀሙ ፣ ጩቤ በያዙ ሰዎች ማስፈራሪያ የደረሰባቸው ፣ ሻሽ ጠምጥመው ሲሄዱ #የተመቱ መኖራቸውን ጠቁመዋል።

ያለውን ችግር የሚመለከታቸው አካላት እንዲያዩ ጠይቀዋል።

አንድ ምዕመን ፤ " ቤተክርስቲያን አምልኮተ እግዚአብሔር የሚፈፀምባት መሆኗን ገልፀው ተልዕኮዋን ለማስፈፀም ሰላም ያስፈልጋታል " ብለዋል።

" የቤተክርስቲያን ኃላፊዎች ሆኑ ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ይህች ቤተክርስቲያን ከሚገባው በላይ እየተጎዳች ስለሆነ ጉዳቷን ለሚመለከተው አካል ማቅረብ የግድ ነው ፤ መስዋዕትነት መክፈልም ያስፈልጋል ምክንያቱም ቅዱስ ስጋ ክቡር ደሙን ካልተመገብን እኛ ሀገረ እግዚአብሔርን አናገኝም " ሲሉ ገልጸዋል።

መንግስት የመጀመሪያ ስራው ህግ ማስከበር መሆኑን የገለፁት እኚሁ ምእመን እንዲህ ያለ ጥቃት (በቀሲስ ዐባይ መለሰ ላይ የደረሰ) እንዳይደርስ ዜጎች ወጥተው እንዲገቡ ተገቢ የሆነ ጥበቃ ሊያደርግ ይገባዋል " ብለዋል።

" ትልቁ ችግር መንግስት ስራውን ባለመስራቱ ምክንያት ነው ይሄ ሁሉ ችግር እየተፈጠረ ያለው " የሚሉት ምዕመኑ " መንግሥት ከማንኛውም ነገር በፊት ቅድሚያ መስጠት ያለበት ሰላም ለማስከበር ነው ፤ ዜጎች የፈለጉበት ቦታ ሰርተው ፤ ጥረው ግረው እንዲኖሩ ዕልውናቸውንና ደህንነታቸው / ዕልውናችንን መጠበቅ ነው " ሲሉ አስገንዝበዋል።

" ይህ ባለመሆኑ ነው ሰው በወጣበት የሚቀረው እዚሁ ሰፈሩ ውስጥ ጥቃት የሚደርሰው ፤ መንግሥት እንዲያህ አይነት ድርጊት እንዳይፈፀም ስራው ባለመስራቱ ነው ችግር እየተፈጠረ ያለው ፤ መንግስት ስራውን ሊሰራ ይገባል " ብለዋል።
1.4K views08:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-25 10:59:31 ጠቅላይ ሚንስትሩ ወልቂጤ መግባታቸው ታውቋል።የጉራጌ የክልልነት ጥያቄ ላይ ከህዝቡ ጋር ለመምከር ነበር ወልቂጤ የገቡት ተብሏል።ዛሬ ደግሞ ህዝቡ የቤት ውስጥ አድማ እያደረገ ይገኛል።ወደ ስብሰባው ውስን የተመረጡ የሀገር ሽማግሌዎች የገቡ ሲሆን ከተማው በአድማ ፀጥ ረጭ ማለቱ ታውቋል።
ባለፈው ሀሙስ በቤተ መንግስት የተካሄደው ውይይት ባለመግባባት መጠናቀቁ ተነግሯል።
1.2K views07:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-25 10:59:05 ፖሊስ ምን አለ? ካህኑን ማን ገደላቸው ?

" ኃይሌ ጋርመንት " የሁርሲሳ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ቀዳሽ ካህን ቀሲስ ዐባይ መለስ " ማንነታቸው አልታወቀም " በተባሉ አካላት በተፈፀመባቸው ጥቃት ተገድለዋል።

ካህኑን የሚያውቋቸው አገልጋዮች /ምዕመናን ስለነበረው ሁኔታ / ስለጥቃቱ ምን አሉ ?

(ለማህበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ከተናገሩት የተወሰደ)

ቃላቸውን የሰጡ ምዕመን አንድ ፦

" ትላንት/መጋቢት 14 ቅዳሴ ቀድሰው በአጋጣሚ እኔ በውጪ አስቀድሼ ነበር ፤ ወደ ደጀሰላም ገባን ምግብ ተመግበን ተለያይተን ነው እነሱ ወደ ኃላ ነበሩ ከምግብ በኃላ እኛ እዚህ አካባቢ ነበርን ተሻግረው ቤታቸው ቆይተው የሌላ (ቄስ አሰፋ ይባላሉ) የእሳቸው ቤት ነው የፈረሰው የእሳቸው ቤት ፈርሶ ሊሻገሩ ገና ከቤታቸው ወጥተው ትንሽ እራመድ እንዳሉ ነው ተመቱ የሚባል ወሬ ሰማን።

ተደወለና ባጃጅ አምጡ ተብለን እስከቤታቸው ድረስ እንደምንም ተቋቁመውት ሄደዋል ከቤታቸው በኃላ አንድ ካህን አብረው ይዘዋቸው መጡ ቤተክርስቲያን አካባቢ ሲደርሱ ተሸነፉ ወደቁ ፤ እኔ ለማናገር ሞከርኩኝ ምንድነው ? ምን ሆነው ነው ? ምንድነው የተፈጠረው ? ስላቸው ምንም ሊመልሱልኝ አልቻሉም ወዲያው ተናነቃቸው ባጃጅ ላይ አስገባናቸው ወደ ክሊኒክ ወሰድናቸው እዛሪ ሪፈር ተባለ ወደ ጥሩነሽ (ሆስፒታል) ወስደው ሌሊት አረፉ የሚለውን ሰማሁ በጣም አዝኛለሁ። "

ቃላቸውን የሰጡ አገልጋይ ሁለት ፦

" ዘጠኝ ሰዓት ከለሊቱ አረፉ ይሉኛል የደብሩ ዋና ፀሀፊ ፤ እንዴት ? አልኳቸው ፈረሳ ነበረና እዛ ፈረሳ እኔ መጠምጠሜን አልያዝኩም፣ ጋቢም አልያዝኩም ማንም ያወቀኝ ሰው የለም ካህንም ልሁን ምዕመንም ልሁን አሉ፤ እሳቸው ግን ጋቢያቸውን ቆባቸውን አድርገው መጥተው እዛ ነው የደበደቧቸው አሉኝ። ቅዳሴ ውለዋል ቀድሰው እዛ ማዶ ፈረሳ አለ ሲባል ግን የኛ የማርያም አገልጋዮችም የፈረሰባቸው ነበረና እዛ ሄጄ አብሬም ልቀላቀል ፤ ባለኝ አቅም ልርዳቸው ብለው ነው ተነስተው የሄዱት፤ እጂ ቀድሰው ውለው ነው የሄዱት። "

ቃላቸውን የሰጡ ምዕመን ሶስት ፦

" የአሟሟታቸውን ሁኔታ ሲነግሩኝ በዕለቱ በ14 ማለት ነው ፤ ቅዳሴ ቀድሰው ቅዱስ ስጋውን ክቡር ደሙን ተቀብለው አቀብለው ወጣ እንዳሉ ነው ያልታወቁ ሰዎች መንገድ ላይ አደጋ ያደረሱባቸው የሚል ነው የተሰጠኝ መረጃ።

ቤት የላቸውም ፤ ስለቤቴ ብለው የተከራከሩትም ነገር የለም መንገድ ላይ እየሄዱ ነው የሌላ ሰው ቤት ፈርሶ ወደዚያ ለማስተዛዘን ሲሄዱ ነው ጥቃት የደረሰባቸው ብለው ነው የነገሩኝ አብረዋቸው የነበሩ ሰዎች። "

ቃላቸው የሰጡ ምዕመን አራት፦

" ባጃጅ ላይ ስናስገባቸው አንድ ነገር ብቻ ነው የተናገሩት ' እባካችሁ እዚሁ ቤተክርስቲያን አድርጉኝ አትውሰዱኝ ' ሲሉ ተነፈሱ ከዚያ መናገርም አልቻሉም ፤ ውሃም ስንሰጣቸው መቀበል አልቻሉም እዛም ስንወስዳቸው መረጃ ሊነግሩን አልቻሉም "

የካህኑ ልጅ ፦

" ቤት ሲመጣ ደም ደምቶ እራሱ ላይ ነጠላ አድርጎ ነው የመጣው ከዚያ በኃላ ምን ሆነህ ነው ስለው መተውኝ ነው ያለው ሌላ ቄስ ነበሩ መጡና ሃኪምቤት ወሰዱት።

ሃዘን ናፍቆት ነው የሚሰማኝ አባ አባቴ ስለው በጣም ነው የምወደው ስለዚህ ካለሱ ማንም የሚያሳድገኝ የለም። "

ቀሲስ ዐባይ መለሰ በምዕመኑ እጅግ የሚወደዱ፣ የሚከበሩ፣ ሰርተው የሚያሰሩ ያላቸውን ሁሉም አቅም ለቤተክርስቲያኗ የሚሰጡ ትልቅ አባት እንደነበሩ ምዕመናኑ ገልጸዋል።

ካህናት በአካባቢው ላይ የተፈፀመው ድርጊት ፍርሃት ላይ እንደጣላቸው የተገለፀ ሲሆን በእሳቸው ህልፈት ከፍተኛ ሀዘን ውስጥ እንዳሉ ተጠቁሟል።

ፖሊስ ስለጉዳዩ ምን አለ ? ከታች ያለውን ያንብቡ

የአዲስ አበባ ፖሊስ የቀሲስ ዐባይ መለሰን ግድያ በተመለከተ " መጋቢት 13 ቀን 2015 ዓ/ም አገልግሎታቸውን ጨርሰው ወደ የሚኖሩበት ሸገር ከተማ ልዩ ቦታው ኤርቱ ሞጆ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በመኖሪያ ቤታቸው አካባቢ በተፈጠረ ፀብ ጉዳት ደርሶባቸው በጡሩነሽ ቤጁንግ ሆሰፒታል በህክምና ሲረዱ ቆይተው በትላንትናው ዕለት መጋቢት 14 ቀን 2015 ዓ/ም ህይወታቸው አልፏል፡፡ " ብሏል።
" ወንጀሉ በአዲስ አበባ ከተማ ክልል ኃይሌ ጋርመንት አካባቢ የተፈፀመ እንደሆነና ጉዳዩ ፖለቲካዊ ትርጉም እንዲሰጠው ለማስመሰል በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ እየተሰራጩ የሚገኙት መረጃዎች ትክክለኛ አይደሉም " ሲል ገልጿል።
የቀሲስ ዐባይ አስክሬን ለተጨማሪ ምርመራ አቤት ሆስፒታል መላኩን የገለፀው የአዲስ አበባ ፖሊስ ቀሪ የፖሊስ ምርመራ እየተካሔደ መሆኑን በሽገር ከተማ አሰተዳደር የፉሪ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ የወንጀል መከላከል ሀላፊ ምክትል ኮማንደር ዳንኤል ኃ/ማርያም ገልፀዋል ብሏል።
1.3K views07:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-16 08:58:06 የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ ተከታዩን የሰላም ጥሪ አቅርቧል ፦

1. ሦስቱ የቀድሞ ሊቃነ ጳጳሳትን በተመለከተ በስምምነቱ መሠረት ወደ ጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ መጥተው በበዓታቸው ተወስነው እየኖሩ ስለሆነ ደመወዛቸው እንዲከፈላቸው እንዲደረግ፣

2. ሃያ አምስቱን ግለሰቦችን በሚመለከት ምንም እንኳን በሕ-ወጥ አድራጐታቸው የቀጠሉ ቢሆንም ቤተ ክርስቲያኗ ለሀገሪቱ ሰላም ካላት የጸና አቋም አንጻር አሁንም በድጋሚ ለመጨረሻ ጊዜ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ፊት በተደረሱት 10 የስምምነት ነጥቦች መሠረት ከዛሬ መጋቢት 6 ቀን 2015 ዓ.ም. ጀምሮ ባሉት አምስት ቀናት ውስጥ የሰላም ጥሪውን ተቀብለው በጽሑፍ ለመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ሪፖርት እንዲያደርጉና በቤተ ክርስቲያ ቀኖና መሠረት ከብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ቀኖናቸውን ተቀብለው እንዲፈጽሙ፣

3. የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድና የኦሮምያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ፕሬዝደንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ ለሰላም ስምምነቱ ላደረጉት አስተዋጽኦ ቤተ ክርስቲያኗ ምስጋናዋን ያቀረበች ሲሆን በቀጣይ በተደረሰው 10 የስምምነት ነጥቦች መሠረት ሕገ-ወጦቹ ግለሰቦች የሰላም ጥሪውን ተቀብለው ለሕግ ተገዥ እንዲሆኑ የበኩላቸውን መንግሥታዊ ሚና እንዲወጡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያኗ ጥሪዋን በድጋሚ አስተላልፋለች።

4. በተደረሰው ስምምነት መሠረት በሕገ-ወጥ መንገድ አህጉረ ስብከትና መንበረ ጵጵስና ሰብረው የያዙ ግለሰቦችን በተመለከተ በየደረጃው ያሉ የመንግሥት አካላት ተገቢውን የሕግ ማስከበር ሥራ በመሥራት ከቤተ ክርስቲያን ይዞታ በማስወጣት ለቤተ ክርስቲያናኗ ሕጋዊ የሥራ ኃላፊዎች በማስረከብ የቤተ ክርስቲያኒቱ የእለት ከእለት ተግባርና ሐዋርያዊ አገልግሎት ያለምንም የጸጥታ ሥጋት እንዲከናወን እንዲሁም በተደረሰው ስምምነት መሠረት እስከአሁን መፈታት ሲገባቸው በእስር ላይ የሚገኙ የቤተ ክርስቲያኒቱ የሥራ ኃላፊዎችና ምእመናን እንዲፈቱ ቤተ ክርስቲያኗ ጥሪዋን አስተላልፋለች።

5. ሃያ አምስቱን ግለሰቦች በሚመለከት ከኦሮምያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ርእሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ ጋር በተደረገው ውይይት ርእሰ መስተዳድሩ በተደረሰው 10ሩ ስምምነት ነጥቦች መሠረት " ሃያ አምስቱንም ግለሰቦች አጠቃልዬ ወደ አዲስ አበባ አመጣቸዋለሁ " በማለት በገቡት ቃል መሠረት በአሁኑ ሰዓት ግለሰቦቹ በክልሉ መንግሥት አማካኝነት ወደ አዲስ አበባ መግባታቸውን ስለተሰማ የክልሉ መንግሥት በገባው ቃል መሠረት ለፈጸመው አድራጐት ቤተ ክርስቲያኗ ያመሰገናች ሲሆን ያልገቡትን ግለሰቦች በአጭር ጊዜ ውስጥ በተገባው ቃል መሠረት እንዲገቡ እንዲደረግ ቤተክርስቲያኗ ጥሪ አስተላልፋለች።

6. ውግዘቱን በሚመለከት ውግዘቱን የማንሳት ሥልጣን የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ እንደመሆኑ መጠን ሁሉም የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ለመጋቢት 21 ቀን 2015 ዓ.ም. ተጠቃለው ወደ መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት እንዲመጡ ጥሪ ተላልፏል።
(EOCTV)
617 views05:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-18 09:23:28 ዘ-ሐበሻ የዕለቱ ዜና - Zehabesha News pinned «ስለ ስምምነቱ… የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከቀናት በፊት ስምምነት ላይ የደረሱት አባቶች ስምምነቱን እንዲሁም ቀኖናውን ደግመው መጣሳቸውን አሳወቀች። ይህንን በተመለከተ ዛሬ የቅዱስ ሲኖዶስ ፅህፈት ቤት መግለጫ ሰጥቶ ነበር። በመግለጫው ብፁዕ አቡነ አብርሃም ተከታዩን ብለዋል ፦ " ከሁለት ቀናት በፊት ሰላም መፈጠሩን ማወጃችን ይታወሳል። በዚህ ሁለት ቀን ውስጥ የምንሰማቸው ነገሮች…»
06:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-18 09:23:22 ስለ ስምምነቱ…

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከቀናት በፊት ስምምነት ላይ የደረሱት አባቶች ስምምነቱን እንዲሁም ቀኖናውን ደግመው መጣሳቸውን አሳወቀች።

ይህንን በተመለከተ ዛሬ የቅዱስ ሲኖዶስ ፅህፈት ቤት መግለጫ ሰጥቶ ነበር።

በመግለጫው ብፁዕ አቡነ አብርሃም ተከታዩን ብለዋል ፦

" ከሁለት ቀናት በፊት ሰላም መፈጠሩን ማወጃችን ይታወሳል።

በዚህ ሁለት ቀን ውስጥ የምንሰማቸው ነገሮች ሁሉ እንደገና ጆሮን ጭው የሚያደርጉ ቤተ ክርስቲያንን የሚከፋፍል አባቶችን ከልጆች ልጆችን ከአባቶች የሚያሻክሩ ነገሮችን እየሰማን ነው።

ወደ ዘጠኝ ሰዓት አካባቢ ' አዲሱ ሲኖዶስ ' በሚል አዲስ ስም እስካሁን ድረስ ከሚጠቀሙበት ለየት ባለ ስም የተሰጠ መግለጫ በሚል በሰጡት ባስተላለፉት ሁሉም በአንድነት ጵጵስናው የሚመለከታቸውም የማይመለከታቸውም የኤጲስ ቆጶስነቱ ደረጃም በስምምነቱም በጋራ የጠፋ ወይም የተሻረ የተደመሰሰ መሆኑን እያወቁም የቅድስናውን ልብስ በመልበስ እና ሌሎችም የስምምነቱ አካል ሆነው ስምምነቱን ያነበቡት ሳይቀሩ በአንድ ላይ ስምምነቱን ጥሰውታል ቀኖናውን እንደገና ደግመው ጥሰውታል።

ሀይማኖቱን ሕጉንም መልሰው መላልሰው ጥሰውታል።

ሹመታቸው ሕጋዊ እንደሆነና በምንም ይሁን በምን የማይሻር መሆኑንም መልእክት አስተላልፈዋል።

ይህ ከዕለት ወደ ዕለት የሚታይ የሚሰማ ከንቱ ክስ ሆኗል።

ከሃይማኖታዊ ይልቅ ፖለቲካዊ ይዘትን ተጎናጽፏል።

በሃይማኖታዊ መንገድ በሰላምና በፍቅር በክርስቶስ ደም የተመሠረተችውን ቤተ ክርስቲያን ከመጠበቅ በክርስቶስ ደም የተዋጁትን ምእመናን ከማስተማር ይልቅ በኃይልና በጉልበት ሁሉንም በነገረ ሰሪነት ግጭት በመፍጠር ሁሉንም ለመቆጣጠር ከዕለት ወደ ዕለት ደፋ ቀና ሲሉ ይታያሉ።

አስተሳሰባቸው አነጋገራቸው ሁሉ በእኩል ደረጃ እንደሆኑም ተናግረዋል።

25 የተባሉትም የትናንትና ካህናት አገልጋዮች አሁንም ኤጲስ ቆጶሳት እንደሆኑ ተደርጎ ተንጸባርቋል።

ዘጠኝ ሰዓት ላይ ይህንን አድርገው ቀኑን ሙሉ አንመጣም ሲሉ ዉለው 10 ሰዓት ላይ ግን ለማንም ለማን መጣን ሳይሉ ቤታቸው ውስጥ [ቤተ ክህነት] ገብተዋል።

... ቤተ ክርስቲያንም እስቲ ሁሉንም ነገር በትዕግሥት እንየው በማለት ዝም ብለን እየተመለከትን ነው።

ስለዚህ ሕግን የጣሰ ሰው ስምምነትን ያፈረሰ ሰው ዛሬም ደግመው ደጋግመው እውነት ለማስመሰል ሐሰትን በሚለፍፉ ሰዎች እንዲህ ዓይነት ድፍረት የሚመለከተው አካል ሊመለከተውና አሁንም በቃ ሊለው ይገባል ብለን መልእክታችንን እናስተላልፋለን።

(ምንጭ:—ኢኦተቤ - ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል)
342 views06:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-15 14:39:06
ፈረንሳይ ጉራራ በርካታ የፌደራል ፖሊስና በሦስት ፓትሮል የተጫኑ የመከላከያ ሰራዊት ኮማንዶዎች በቦታው ላይ ደርሰዋል።
1.2K views11:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-10 19:34:32 #Update

ቅዱስ ሲኖዶስ በሰጠው መግለጫ ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ጋር በነበረው ውይይት የቤተክርስቲያኗ ብዙ ጥያቄዎቿ እንደተመለሰላትና ነገ ጥዋት 3 ሰዓት ላይ ዝርዝር እና ሰፊ መግለጫ እንደሚሰጥ አሳውቋል።
1.5K views16:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-10 19:30:38 እግድ

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የእግድ አቤቱታ መሠረት ቤተ ክርስቲያኗ በአወገዘቻቸው ተጠሪዎች ላይ ከደቂቃዎች በፊት የእግድ ትእዛዝ መስጠቱ ተሰምቷል።።
1.5K views16:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ