Get Mystery Box with random crypto!

Wolaita Sodo University

የቴሌግራም ቻናል አርማ wolaitasuniversity — Wolaita Sodo University W
የቴሌግራም ቻናል አርማ wolaitasuniversity — Wolaita Sodo University
የሰርጥ አድራሻ: @wolaitasuniversity
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 18.46K
የሰርጥ መግለጫ

This is the official telegram channel of Wolaita Sodo University
Our Official Website :
http://www.wsu.edu.et/
Our Official Facebook page :
https://m.facebook.com/Wolaita-Sodo-University-246568056057804

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2023-04-12 20:49:47
1.1K views17:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-12 20:49:44 የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ፕ/ር ታከለ ታደሰ ከአስተዳደር ዘርፍ ሠራተኞች እና ከህክምና ባለሙያዎች ጋር ውይይት አደረጉ።
____________
በዩኒቨርሲቲው ሁለገብ መሰብሰቢያ አደራሽ በተካሄደው የውይይት መድረክ በ2015 አጋማሽ አመት የተከናወኑ ዋና ዋና የስራ አፈጻጸሞች እና ተያያዥነት ያላቸውን ተቋማዊ ጉዳዮች በተመለከተ ፕሬዝዳንቱ ለመድረኩ ተሳታፊዎች ማብራሪያ ሰጥተዋል።

የተቋሙን "የ2015 በጀት አመት የ6 ወር የስራ አፈጻጸም ሪፖርት" ፕ/ር ታከለ ታደሰ በመድረኩ ያቀረቡ ሲሆን፤ አመራርና አስተዳደርን ከማጠናከር እንዲሁም ተቋማዊ የማስፈፀም አቅምን ከማጎልበት ረገድ እየተሰሩ ያሉ ተግባራት የበለጠ ተጠንክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።

አዲሱ የሰው ሀይል አደረጃጀት መዋቅር ተሰርቶ እና በሲቭል ሰርቪስ ኮሚሽን ፀድቆ ለዩኒቨርሲቲው የተላከ መሆኑን ፕዝሬዳንቱ አሳውቀው፤ እንደ ተቋም በአፈጻጸም መመሪያው መሠረት የአደረጃጀት መዋቅሩን ስራ ላይ ለማዋል ተገቢው ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል ሲሉ ጠቁመዋል።

በ2013 በጀት ዓመት በኦዲት ውጤቶች ላይ የድርጊት መርሃ ግብር ተዘጋጅቶ ተገቢው የማስተካከያ እና የእርምት እርምጃ እየተወሰደ ይገኛል ያሉት ፕ/ር ታከለ፤ የኦዲትና የህግ የበላይነትን ከማስከበር ረገድ የተጀመሩ ተግባራት በቀጣይ ጊዜያት የበለጠ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።

ሰላማዊ መማር መስተማርን ከማስፈን እና ከማዝለቅ ረገድ ባለፉት 6 ወራት ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ዘርፈ ብዙ ተግባራት የተከናወነ መሆኑን ፕ/ር ታከለ ገልጸው፤ የውስጥ ተጋላጭነትን የመቀነስ፤ የህግ የበላይነትን የማስፈንና የማረጋገጥ እንዲሁም የተደራጀ ችግር ፈቺ የክትትል እና ድጋፍ ተግባራት በተቀናጀ አግባብ መሰራቱን ጠቁመዋል።

ፕሬዝዳንቱ፤ አደረጃጀቶችን በማጠናከር ሰላማዊ መማር ማስተማር መቀጠሉ፤ የውስጥ አቅምን በመጠቀም ከፍተኛ ወጪዎች መቀነሱ፤ ከሀገር አቀፍና ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር ትስስር በመፍጠር ሀብት ማመንጨት መቻሉ፤ የድጋፍ፥ ክትትልና ግምገማ ሥርዓትን በማጠናከር የመልካም አስተዳደር ችግሮች መፈታት መቻሉ በአፈጻጸም ደረጃ ባለፉት 6 ወራት በጥንካሬ የታየ መሆኑን ገልጸዋል።

“ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደትን ማረጋገጥ እና ማዝለቅ፤ የትምህርት ጥራትና ተገቢነትን ማረጋገጥ፤ የመውጫ ፈተና ዝግጅት እና ትግበራን የበለጠ ማጠናከር፤ የመሠረተ ልማትና ግንባታ ፕሮጄክቶችን አፈፃፀም ማሻሻል፤ የሃብት አስተዳደርና ተጠያቂነትን ማስፈን፤ የኦዲት ግኝቶችን በፍጥነት ማረም፤ ለመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በወቅቱ ፈጣን ምላሽ መስጠት፤ አዲሱን የሰው ሀይል አደረጃጀት መዋቅር ስራ ላይ ማዋል፤ ከምርምር ተቋማት እና ኢንዱስትሪዎች ጋር ያለውን ትስስር ማጠናከር እንዲሁም የተደራጀና ችግር ፈቺ የክትትልና ድጋፍ ሥራ በቀጣይ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት እንደሚተገበር ፕ/ር ታከለ አሳውቀዋል።

ዩኒቨርሲቲውን ወደሚፈለገው የዕድገት ደረጃ ለማሻገር በተቀናጀ አግባብ ምቹ ሁኔታዎችን ወደ መልካም ውጤት መቀየር ተገቢ ነው ያሉት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት፤ እንደ ተቋም ያለንን የሰለጠነ የሰው ኃይል፣ የተትረፈረፈ ሀብትና ሕጋዊ የአስተዳደር ስርዓት መጠቀም ግድ ይላል ሲሉም ተናግረዋል።

በመድረኩ በ2015 አጋማሽ አመት በተከናወኑ ዋና ዋና የስራ አፈጻጸሞች እንዲሁም ትኩረት በሚሹ ጉዳዮች ላይ በማተኮር ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶ የዕለቱ መርሃ ግብር ተጠናቋል።

ዕውቀትን በተግባር!!

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
1.1K views17:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 20:22:21 «ዩኒቨርሲቲውን ወደሚፈለገው የዕድገት ደረጃ ለማሻገር በተቀናጀ አግባብ ምቹ ሁኔታዎችን ወደ መልካም ውጤት መቀየር ተገቢ ነው።» ፕ/ር ታከለ ታደሰ-የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት

በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ አጠቃላይ ተቋማዊ የምክክር መድረክ በዛሬው ዕለት ተካሂዷል።
____
የዩኒቨርሲቲው ምክር ቤት አባላት፣ መምህራን እና የቴክኒክ ሰራተኞች፣ የመምህራን ማህበር አመራሮች እንዲሁም የተማሪዎች ሕብረት አመራሮች በምክክር መድርኩ ተሳትፈዋል።

በመድረኩ የዩኒቨርሲቲው የ2015 በጀት አመት የ6 ወር የስራ አፈጻጸም ሪፖርት እንዲሁም የመምህራን ማህበር የ2015 በጀት አመት የሥራ እቅድ ቀርቦ ከተሳታፊዎች ጋር ውይይት ተካሂዷል።

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ፕ/ር ታከለ ታደሰ የተቋሙን የ2015 በጀት አመት የ6 ወር የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን፤ አመራርና አስተዳደርን ከማጠናከር እንዲሁም ተቋማዊ የማስፈፀም አቅምን ከማጎልበት ረገድ ሠፊ ስራ መሰራቱን አብራርተዋል።

አዲሱ የሰው ሀይል አደረጃጀት መዋቅር ተሰርቶና በሲቭል ሰርቪስ ኮሚሽን ፀድቆ የተላከ መሆኑን ፕዝሬዳንቱ ገልጸው፤ ለትግበራ ተገቢው ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል ሲሉም አሳውቀዋል።

የኦዲትና የህግ የበላይነትን ለማስከበር የተሰሩ ተግባራትን ፕሬዝዳንቱ ሲያብራሩ፡ “በ2013 በጀት ዓመት በኦዲት ውጤቶች ላይ የድርጊት መርሃ ግብር ተዘጋጅቶ የማስተካከያ እና የእርምት እርምጃ እየተወሰደ ይገኛል” ብለዋል።

ሰላማዊ መማር መስተማርን ለማረጋገጥና ለማዝለቅ ባለፉት 6 ወራት፡ የውስጥ ተጋላጭነትን የመቀነስ፥ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት የመስራት፥ የህግ የበላይነትን የማረጋገጥ እና የተደራጀ ችግር ፈቺ የክትትል እና ድጋፍ ሥራ የተሰራ መሆኑንም ፕ/ር ታከለ ጠቁመዋል።

የትምህርት ጥራት፣ አግባብነት፣ ፍትሐዊነት፣ ተደራሽነት እንዲሁም የመምህራንን ብቃትን ከማረጋገጥ ረገድ ዘርፈ ብዙ ተግባራት ተከናውኗል ያሉት ፕሬዝዳንቱ፤ ባለፉት 6 ወራት 24 ያህል የአካዳሚክ ፕሮግራሞችን  የማስፋፋት ስራ ተጀምሯል ብለዋል።

የመዉጫ ፈተና ዝግጅትን በተመለከተ፡ ግብረ-ኃይል በማቋቋምና የድርጊት መርሀ ግብር በማዘጋጀት መጠነ ሰፊ የቅድመ ዝግጅት ስራ መሰራቱን ፕ/ር ታከለ ገልጸው ፤ችግር ፈቺ የክትትልና ድጋፍ ሥራ በተቀናጀ አግባብ እየተሰራ እንደሆነም አመላክተዋል።

የምርምር፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርና የፈጠራ ስራዎች ተደራሽነት፣ ጥራት እና ፍትሀዊነትን ከማሳደግ ረገድ ውጤታማ ስራ መሰራቱን የገለጹት ፕሬዝዳንቱ፤ የምርምር፥ ማኅበረሰብ አገልግሎትና የቴክኖሎጂ ሽግግር ተግባራት የትኩረት መስክና የፕሮጄክቶቹን የወደፊት ተጠባቂ ውጤት መሰረት በማድረግ ተፈጻሚ መሆኑንም ጠቁመዋል።

በአረንጓዴ አሻራ ዙሪያ የተከናወኑ ተግባራት አፈጻጸምን ፕሬዝዳንቱ ሲያብራሩ፡ “አሻራችን ለትውልዳችን በሚል መሪ ቃል” 15 ሺህ አቮካዶ ችግኝ በአንድ ጀምበር መተከሉን ገልጸው፤ በቀጣይ የክረምት ወራት ለተከላ እንዲውል 330 ሺሕ የአቮካዶ ፍሬ እየፈላ ይገኛል ብለዋል።

በዩኒቨርሲቲው መሰረተ ልማት፣ ፋሲሊቲንና የዲጂታል ክህሎት ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ከማሻሻል ረገድ መጠነ ሰፊ ስራ የተከናወነ መሆኑን ፕ/ር ታከለ ገልጸው፤ በመሠረተ ልማት ዙሪያ የሚከናወኑ ተግባራት የበለጠ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቁመዋል።

አደረጃጀቶችን በማጠናከር ሰላማዊ መማር ማስተማር መቀጠሉ፤ የውስጥ አቅምን በመጠቀም ከፍተኛ ወጪዎችን መቀነሱ፤ ከሀገር አቀፍና ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር ትስስር በመፍጠር ሀብት ማመንጨት መቻሉ፤ የድጋፍ፥ ክትትልና ግምገማ ሥርዓትን በማጠናከር የመልካም አስተዳደር ችግሮች መፈታት መቻሉ በመልካም ተሞክሮነት ተገልጿል።

ሰላማዊ መማር ማስተማር ሂደት ማረጋገጥና ማዝለቅ፤ የትምህርት ጥራትና ተገቢነትን ማረጋገጥ (የመውጫ ፈተና)፤ የመሠረተ ልማትና ግንባታ ፕሮጄክቶች አፈፃፀም ማሻሻል፤ የሃብት አስተዳደርና ተጠያቂነት ማስፈን (የኦዲት ግኝቶችን በፍጥነት ማረም)፤ ለመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በወቅቱ ምላሽ መስጠት፤ አዲሱን የሰው ሀይል አደረጃጀት መዋቅር ስራ ላይ ማዋል፤ ከምርምር ተቋማትና ኢንዱስትሪዎች ጋር ትስስር ማጠናከር እንዲሁም የተደራጀና ችግር ፈቺ የክትትልና ድጋፍ ሥራ መስራት በቀጣይ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት ይተገበራል ሲሉም ፕ/ር ታከለ አሳውቀዋል።

ዩኒቨርሲቲው በርካታ የሰለጠነ የሰው ኃይል፣ የተትረፈረፈ ሀብት እንዲሁም ሕጋዊ የሆነ የአስተዳደር ስርዓት እንዳለው የገለጹት ፕሬዝዳንቱ፤እንደ ተቋም ዩኒቨርሲቲውን ወደሚፈለገው የዕድገት ደረጃ ለማሻገር በተቀናጀ አግባብ ምቹ ሁኔታዎችን ወደ መልካም ውጤት መቀየር ተገቢ ነው” ብለዋል።

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ መምህራን ማህበር ፕሬዝዳንት መምህር ደጉ መና የማህበሩን የ2015 በጀት አመት የሥራ እቅድ በመድረኩ አቅርበዋል።

የመርሃ ግብሩ ተሳታፊዎችም በቀረቡ ሰነዶች ላይ በጥልቀት በመወያየት ሀሳብ አስተያየት የሰጡ ሲሆን፤ በመድረኩ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ ተሰጥቶ መርሃ ግብሩ ተጠናቋል።

ዕውቀትን በተግባር!!

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
2.3K viewsedited  17:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 20:21:27
2.1K views17:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-08 18:13:43 ዩኒቨርሲቲው 1 ሺሕ 788 ብሄራዊ የበጎ ፍቃድ ማህበረሰብ አገልግሎት ሰልጣኞችን አስመረቀ።
________

ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ከኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሰላም ሚኒስቴር ጋር በመተበበር የ6ኛ ዙር ብሄራዊ የበጎ ፍቃድ ማህበረሰብ አገልግሎት ሰልጣኞችን የምረቃ ሥነ-ስርዓት አካሂዷል።

«በጎነት ለአብሮነት» በሚል መሪ ቃል በተከታታይ 5 ዙር በተካሄደ ብሔራዊ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ስልጠና ከ 6 ሺህ የሚበልጡ ሰልጣኞች መመረቃቸውን በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ፕ/ር ታከለ ታደሰ ገልጸዋል።

ዩኒቨርሲቲው በ 6ኛ ዙር የበጎ ፍቃድ አገልግሎት የሰልጠና መርሃ ግብር ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የተውጣጡ 1 ሺሕ 788 ሰልጣኞችን ተቀብሎ ባለፉት 33 ቀናት እያሰለጠነ መቆየቱን ፕሬዝዳንቱ ጠቁመዋል።

የወጣቶች በጎ ፍቃድ ማህበረሰብ አግልግሎት መርሃ ግብር “ኢትዮጵያዊ እሴቶችን እና መርሆችን ለወጣቱ ትውልድ በማስተላለፍ ረገድ ጉልህ ፋይዳ አለው” በማለት ፕ/ር ታከለ ተናግረዋል።

ስልጠናው “በብሄር፣ በጎሳ፣ በሃይማኖት እና በሌሎችም ማንነቶች ላይ መሠረት አድርጎ ያለውን መከፋፈልና ጥርጣሬ በማስወድ የወጣቶችን የሀገርና የሕዝብ ፍቅር ለማሳደግ ከፍተኛ አስተዋፆ ያበረክታል” ሲሉም ገልጸዋል።

ፕሬዝዳንቱ አክለውም ስልጠናው “ወጣቶች ማህበረሰባዊ እሴቶችን እና የሞራል አቅም እንዲያጎለብቱ በመደገፍ በተለይም ብዝሃነት ባላት እንደ ኢትዮጵያ ያለ ሀገር ውስጥ እርስ በርስ መደማመጥና መረዳዳትን ያመጣል” ሲሉም ተናግረዋል።

ከጭፍን ጥላቻ ወጥቶ እርስ በርስ የተጋመደ ማህበረሰብ እንዲፈጠር በማድረግ ዘላቂ ሰላምና ሀገራዊ መግባባትን ማሳደግ ካለው ፋይዳ ረገድ ስልጠናው የበለጠ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል ፕ/ር ታከለ።

ፕሬዝዳንቱ ለተመራቂዎች ባስተላለፉት መልዕክት “በዘላቂ ሰላም እና ሀገራዊ መግባባት ስራ ውስጥ የራሳችሁን አሻራ እንድታሳርፉ ይጠበቅባችኋል” ብለዋል።

የዕለቱ ተመራቂ የሆኑ 1 ሺሕ 788 በጎ ፍቃደኛ ሠልጠኞች በስልጠና ቆይታቸው ያገኙትን ስነ-ምግባር፣ እውቀትና ክዕሎት ማህበረሰቡን ለማገልገል ዓላማ እንዲያውሉት አሳስበዋል።

በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የኢፌዲሪ ሠላም ሚኒስቴር ሚኒስትር አማካሪና የዕለቱ የክብር እንግዳ አቶ ካዳይኪ ገዛኸኝ በመርሃ ግብሩ የተገኙ ሲሆን፤ የአካል ብቃት፥ የስሜት ብስለት እና የስራ ዝግጁነት ላይ በማተኮር ከተሰጠው ስልጠና መልካም ቁም ነገር እንደጨበጣችሁ እምነቴ ጽኑ ነው ብለዋል።

የስልጠናው መርሃ ግብር “ኢትዮጵያዊ እሴቶቻችንን የሚያሳድጉ፣ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ልማትን የሚያመጡ፣ ብሔራዊ አንድነትን የሚያጠናክሩ ሥራዎች እንዲሰሩ ጉልህ ፋይዳ አለው” ብለዋል አቶ ካዳይኪ።

የ6ኛ ዙር ሰልጣኞችም ማህበረሰቡን በብቃት ከማገልገል ረገድ ድርሻችሁ ከፍተኛ መሆኑን አውቃችሁ በቀጣይ 10 ወራት ማህበረሰቡን ለማገልገል ከወዲሁ ራሳችሁን እንድታዘጋጁ ሀደራ ሲሉም የክብር እንግዳው ተናግረዋል።

የብሄራዊ በጎ ፍቃድ ማህበረሰብ አገልግሎት ስራ ላይ መሳተፍ ከዕድለኝነት ባሻገር የህሊናና የመንፈስ እርካታ የሚሰጥ ተግባር መሆኑን አቶ ካዳይኪ ለሰልጣኞች ገልጸዋል።

በቀጣይ ጊዜያት “የዘላቂ ሰላምና ሀገራዊ መግባባት ስራ ውስጥ የራሳችሁን አዎንታዊ አሻራ በማሳረፍ የዜግነት ግዴታችሁን መወጣት ይጠበቅባችኋል ሲሉ የክብር እንግዳው አሳስበዋል።

በመርህ ግብሩ ማጠቃለያ ስልጠናውን ላስተባበሩ አካላት የምስጋና ምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል።

ዕውቀትን በተግባር!!

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
1.3K views15:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-08 18:13:38
1.2K views15:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-07 19:35:17 በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ህግ ትምህርት ቤት አዘጋጅነት በተማሪዎች መካከል «የክርክር ውድድር» መድረክ ተካሄደ!!

ውድድሩ “ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብትና በኢንተርኔት ላይ የሚደርግ ገደብ” በሚል ርዕሰ ጉዳይ የተካሄድ መሆኑ ተመላክቷል።
________

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ ህግ ትምህርት ቤት ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ማዕከል #EHRDC ጋር በጋራ በመሆን የክርክር ውድድር መድረክ አዘጋጅቷል።

ክርክሩ በዋናነት ተማሪዎች በተለያዩ የሰብዓዊ መብትና ሌሎች ጉዳዮችንም በምክንያት በመሞገት የተሻለ ሀሳብ ለማፍለቅ እንዲረዳቸዉ ታስቦ የተዘጋጀ መድረክ መሆኑ የመርሃ ግብሩ አዘጋጆች አሳውቀዋል።

በክርክር መድረኩ የተገኙት የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ተወካይ መምህር የደሳለኝ ዳርጋሶ ዩኒቨርሲቲው አፕላይድ ሳይንስ ዩኒቨርሲቲ በመሆኑ በህግ ትምህርት ቤት እየተተገበረ ያለው ተግባር ተኮር ትምህርትና ልምምድ የዩኒቨርሲቲውን ራዕይ የሚያሳካ ነው ብለዋል፡፡

የህግ ተማሪዎች በተለያዩ የክርክር መድረክ እና ምስለ ችሎት ዉድድሮች የንድፈ ሀሳብ እዉቀታቸዉን በተግባር በመለማመድ ማዳበር ወደ ሥራ ዓለም ሲቀላቀሉ በሚገባ ይጠቅማቸዋል ሲሉም ተወካይ ተናግረዋል።

ውድድሩ ተማሪዎች የርስ በርስ የህግ ክርክር በማድረግ «የዕውቀት ሽግግር» እንዲያደርጉ የሚጠቅም መሆኑን የጠቆሙት ተወካዩ፤ ዩኒቨርሲቲው ይህን መሰል ተግባር ተኮር ትምህርት የሚደግፍ መሆኑን መምህር ደሰለኝ ገልፀዋል፡፡

የህግ ትምህርት ቤት ዲን የሆኑት ረዳት ፕሮፈሰር ታመነ ኤና የተግባር ትምህርት "እዉቀትን በተግባር" ከሚለዉ የዩኒቨርስቲው መርህ ጋር የሚጣጣም መሆኑን ጭምር አውስተዋል።

ተማሪዎች ተመርቀው ሲወጡ በእውነተኛ የችሎት ሥራ ላይ ውጤታማ እንዲሆኑ የተግባር ትምህርት እና ልምምዶች በትምህርት ቤቱ በስፋት ሲሰጥ መቆየቱንም ገለፀዋል፡፡

በተለይም የክርክሩ ርዕሰ ጉዳይ የሆነዉ “ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብትና በኢንተርኔት ላይ የሚደርግ ገደብ” ተማሪዎች መብታቸዉን እና የመብቱን ገደብ ለይተዉ እንዲያዉቁ እድል እንደሚፈጥር ዲኑ ተናግረዋል።

ዲኑ አክለውም፤ ወደፊትም የህግ ተማሪዎች ውጤታማ የሚሆኑበትን መንገድ በመከተል ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በጋራ ተቀናጅቶ ለመስራት ትምህርት ቤቱ ዝግጁ መሆኑን አሳውቀዋል፡፡

ፕሮግራሙ እዉን እንዲሆን የጎላ ሚና የተጫወቱ ተቋማትን እና ግለሰቦችን ረዳት ፕሮፈሰር ታመነ አመስግነዋል።

የክርክሩ አዘጋጅ የሆኑት የህግ ትምህርት ቤት ምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ዘርፍ ምክትል ዲን መምህር ነብዩ ማርቆስ በበኩላቸው ክርክሩ ሁሉንም የዩኒቨርሲቲውን ተማሪዎች በማሳተፍ የተዘጋጀ እንደሆነ ተናግረዋል።

ተማሪዎች በሰብዓዊ መብት እና ሌሎች ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ሀሳባቸውን በነፃነት ማንሸራሸር የተሻለ የተግባር እዉቀት ለመጨበጥ እንዲሁም በምክንያት የመሞገት ባህል እንዲያዳብሩና በሀሳብ ልዕልና እንዲያምኑ ያግዛቸዋል ብለዋል ምክትል ዲኑ።

ከኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ተከላካዮች ማዕከል #EHRDC ተወክለው የመጡት ወ/ሪት ሀና ላሌ በበኩላቸው ተማሪ በነበሩበት ወቅት በተለያዩ ክበባት በመሳተፍ ያገኙት እዉቀትና ክህሎት በሥራ ዓለም የበለጠ እንደጠቀማቸው ተናግረዋል።

ተማሪዎች ከመደበኛ ትምህርት ጎን ለጎን በክበባት እና ማህበራት በመሳተፍ ክህሎታቸውን ማዳበር እንደሚገባም አሳስበዋል።

በክርክር መድረኩ አሸናፊ ለሆኑ ተወዳዳሪ ተማሪዎች ሰርተፊኬት እና የተለያዩ የግል እና የቡድን ማበረታቻ ሽልማቶች ተበርክቶላቸዋል።
1.7K viewsedited  16:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-07 19:35:09
1.5K views16:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-07 19:29:46 የዩኒቨርሲቲው ሥራ አመራር ቦርድ የዶክተር መስፍን ቢቢሶ ዶዳን የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ አፀደቀ!!
________

የዩኒቨርሲቲው ሴኔት ገምግሞ ባቀረበው ጥያቄ መሰረት ሥራ አመራር ቦርዱ በዛሬው ዕለት ባካሄደው ስብሰባ ለዶ/ር መስፍን ቢቢሶ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ በመስጠት አጽድቋል።

ዶ/ር መስፍን ቢቢሶ በአፈር ምርምር ሳይንስ (Professor of Soil Science)የሙሉ ፕፌሰርነት ማዕረግ ዕድገቱ በቦርዱ የጸደቀላቸው ሲሆን፤ በዲላ ዩኒቨርሲቲ ከ2009 ዓ.ም ጀምሮ እንዲሁም በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ከምስረታ ጀምረው በተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ፤ ኬሚስትሪ ትምህርት ክፍል በመምህርነት ያገለገሉና ይህን ማዕረግ ያገኙ የኮሌጁ የመጀመሪያው መምህርና ተመራማሪ ሆነዋል፡፡

ዶ/ር መስፍን የሥራ ልምድ ማዕደር እንደሚያመላክተው ከ2009 ዓ.ም ጀምሮ ጀምሮ እስካሁን ድረስ በዩኒቨርሲቲ መምህርነት እና ተመራማሪነት በቅንንትና በታታሪነት በማገልገል ላይ ይገኛሉ፡፡

ዶ/ር መስፍን በሙያቸው ካበረከቱት ጉልህ የመማር ማስተማርና ምርምር ስራዎች አስተዋፅዖ በተጨማሪ በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የተለያዩ የአመራርነት ሚናዎችን በብቃት ተወጥተዋል፡፡ እ.አ.አ ከ2015 ጀምሮ በዩኒቨርሲቲ የኬሚስትሪ ትምህርት ክፍል ኃላፊ፣ የተቋማዊ ጥራት ዳይሬክተር፣ የቢዝነስና ልማት ምክትል ፕሬዝዳንት (በውክልና) እንዲሁም ከመስከረም 1/2011 ዓ.ም ጀምሮ እስካሁን ድረስ የምርምር፣ ማህበረሰብ አገልግሎትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት በመሆን በአመራርነት እያገለገሉ ይገኛሉ።

ዶ/ር መስፍን ቢቢሶ 45 የምርምር ፅሁፎችን በሀገር ዉስጥ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ታዋቂ በሆኑ ጆርናሎች በዋነኝነት እና በተባባሪነት ለህትመት አብቅተዋል፡፡ የመማር ማስተማር ስራን የሚያግዙ ፅሁፎችን፣ የማስተማሪያ ጥራዞችን፣ መመሪያዎችን እና የመፅሀፍ ምዕራፎችን ፅፈዋል፡፡

ዶ/ር መስፍን ቢቢሶ ሙያዊ እና የማህበረሰብ ተሳትፎ ተግባራትን በተመለከተ ከ25 በላይ ሙያዊና የማህበረሰብ ተሳትፎ ላይ በንቃት ተሳትፈዋል። ከ20 በሚበልጡ የዩኒቨርሲቲው ጉዳዮች ላይም ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ተሰማርተዋል።

ዶ/ር መስፍን በሙያቸው በተለይም በአፈር ኬሚስትሪ፣ አግሮኖሚ፣ የአፈር ሳይንስ፣ የትንታኔ ኬሚስትሪና የአካባቢ ሳይንስ መስክ ያሉ ከ 40 የሚበልጡ የማስተርስ ተማሪዎችን በዋና እና በረዳት አማካሪነት አገልግለዋል። እንዲሁም ከ50 የሚበልጡ የማስተርስ ተማሪዎችን ፈትነዋል። በተጨማሪም በአፈር ሳይንስ መስክ የ 1 ፒ.ኤች.ዲ ተማሪ የምርምር ድርሳን በማማከር ፈትነዋል፡፡

ዶ/ር መስፍን ቢቢሶ እውቅና ባለው የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ጆርናል (ጆርናል ኦፍ ሳይንስ እና አካታች ልማት) ላይ አሁን ድረስ የአለም አቀፍ አማካሪ ቦርድ አባል በመሆን እያገለገሉ ሲሆን፤ በብሔራዊ እና ዓለም አቀፍ የምርምር ኮንፈረንሶች ላይ ሳይንሳዊ ወረቀት በማቅረብ ጉልህ ሚና ከመወጣታቸውም ባሻገር የኢትዮጵያ ኬሚካላዊ ማህበር አባል ናቸው።

ዶ/ር መስፍን ቢቢሶ ከተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት ሀብት በማፈላለግ ረገድ በተለይም ከውጭ ተቋማት በ 6 ያህል ፕሮጀክቶች እንዲሁም በሀገር ውስጥ በ 10 ፕሮጀክቶች ጉልህ ተሳትፎ ያላቸው ሲሆን፤ ከአሜሪካ ኬሚካል ሶሳይቲ (ኤ.ሲ.ኤስ) እና ከአፍሪካ ኬሚካል ሶሳይቲ ፌዴሬሽን (ኤፍ.ኤሲ.ኤስ) የገንዘብ ድጋፍ እንዲገኝ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርገዋል።

ዶ/ር መስፍን ቢቢሶ ሀብት በማፈላልግ ረገድ ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ ሀብት እንዲያገኝ በማድረግ፣ በሙያቸው መስክ ብቃት ያላቸውን ተማሪዎች በማፍራት፣ ቅድምያ በሚሰጣቸው የማህበረሰቡ ችግሮች ላይ ምርምሮችን በማከናወን መፍትሔ እንዲያገኙ በማድረግ እንዲሁም የማህበረሰብ አገልግሎቶችን በመስጠታቸው ያስገኙትን ጥቅም ከመመሪያው አንፃር ገምግሞ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ እንዲሰጣቸው የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ሴኔት ያቀረበውን ጥያቄ ተቀብሎ የገመገመው የዩኒቨርሲቲው ሥራ አመራር ቦርድ መጋቢት 28/2015 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ ለዶ/ር መስፍን ቢቢሶ በአፈር ምርምር ሳይንስ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ (Professor of Soil Science) ሰጥቷቸዋል፡፡

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደርም ለፕሮፌሰር መስፍን ቢቢሶ እንኳን ደስ አለዎት እያለ መልካም የስራ ጊዜ እንዲሆንላቸው ይመኛል፡፡

ዕውቀትን በተግባር!!

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

መጋቢት 28/2015 ዓ.ም
1.5K views16:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-07 19:29:35
1.1K views16:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ