Get Mystery Box with random crypto!

Wolaita Sodo University

የቴሌግራም ቻናል አርማ wolaitasuniversity — Wolaita Sodo University W
የቴሌግራም ቻናል አርማ wolaitasuniversity — Wolaita Sodo University
የሰርጥ አድራሻ: @wolaitasuniversity
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 18.46K
የሰርጥ መግለጫ

This is the official telegram channel of Wolaita Sodo University
Our Official Website :
http://www.wsu.edu.et/
Our Official Facebook page :
https://m.facebook.com/Wolaita-Sodo-University-246568056057804

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 8

2023-04-07 19:24:09 የዩኒቨርሲቲው ስራ አመራር ቦርድ በተለያዩ ተቋማዊ ጉዳዮች ላይ በመወያየት ውሳኔዎችን አስተላልፏል።
_______
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የሥራ አመራር ቦርድ አዲስ አበባ በሚገኘው ጁፒተር ኢንተርናሽናል ሆቴል በተለያዩ ተቋማዊ ጉዳዮች ላይ በመወያየት ውሳኔዎችን አስተላልፏል።

በመድረኩ የ2015 አጋማሽ ዓመት ሪፖርት በመገምገም ቀጣይ የሥራ አቅጣጫ መስጠት፣ የ2015 ዓ.ም ተጨማሪ በጀት ማጽደቅ እንዲሁም የመምህር ደረጃ ዕድገት ገምግሞ ማጽደቅ በአጀንዳነት ለውይይት ቀርቧል።

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ፕ/ር ታከለ ታደሰ የተቋሙን የ2015 አጋማሽ ዓመት አፈጻጸም ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን፤ በመማር ማስተማር፣ በምርምር፣ በማህበረሰብ አገልግሎት እና በቴክኖሎጂ ሽግግርና ስርጸት እንዲሁም በሌሎች ልማታዊ ዘርፎች የተሰሩ ተግባራትን በተመለከተ ገለጻ አድርገዋል።

በዩኒቨርሲቲው አደረጃጀቶችን በማጠናከር ሰላማዊ መማር ማስተማር ተጠናክሮ መቀጠሉ፤ የውስጥ አቅምን አሟጦ በመጠቀም ከፍተኛ ወጪዎችን መቀነስ መቻሉ፤ ከሀገር አቀፍና ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር ትስስር በመፍጠር ሀብት ማመንጨት መቻሉ፤ የድጋፍ፥ ክትትልና ግምገማ ሥርዓትን በማናጠከር የመልካም አስተዳደር ችግሮች እተየፈቱ መሆኑ በመልካም ተሞክሮነት ተገምግሟል።

ባለፉት 6 ወራት ከፍተኛ የሆነ የበጀት እጥረት እና የዋጋ ግሽበት መኖሩ፤ የግንባታ ፕሮጄክት ሥራዎች መዘግየት፤ የተማሪ ቀለብ እና የሆስፒታል በጀት ክፍያ ከዕቅድ በላይ መሆን፤ የተሽከርካር ዕጥረት እንዲሁም የቅሬታዎች ማዕከላዊነትን መጣስ እንደ ተቋም ያጋጠሙ ችግሮች መሆናቸው በመድረኩ ተጠቁሟል።

ሠላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት የበለጠ ተጠናክሮ እንዲቀጥልና እንዲዘልቅ፤ የመውጫ ፈተና ዝግጅት እና ትግበራን ማጠናከር፤ የኦዲት ግኝቶችን በፍጥነት ማረም፤ የዩኒቨርሲቲውን አዲስ መዋቅር ስራ ላይ ማዋል፤ ከምርምር ተቋማት እና ከኢንዱስትሪዎች ጋር ያለውን ትስስር የበለጠ ማጠናከር፤ የመሠረተ ልማት እና ግንባታ ፕሮጄክቶችን አፈፃፀም ማሻሻል፤ ለመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በወቅቱ ምላሽ መስጠት እንዲሁም የተደራጀና ችግር ፈቺ የክትትልና ድጋፍ ሥራ መስራት በቀጣይ ጊዜ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት እንዲሰራ ሥራ አመራር ቦርዱ የሥራ አቅጣጫ ተቀምጧል።

ሥራ አመራር ቦርዱ በተጨማሪም የ2013 በጀት ዓመት የኦዲት አፈጻጸ ግብረ መልስ ሪፖርት እንዲሁም በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መዋቅራዊ አደረጃጀትና የሰው ኃይል ምደባ ላይ ጥልቅ ውይይት በማካሄድ የሥራ አቅጣጫ ሰጥቷል።

የመንግስት ፋይናንስ ህግጋትንና አሰራሮችን ተከትሎ በቁርጠኝነት መስራት እንዲሁም የአሰራር ክፍተቶችን በፍጥነት ማረም ተገቢ እንደሆነ ሥራ አመራር ቦርዱ በጥልቀት የተወያየ ሲሆን፤ ከኦዲት ግኝት ነጻ ለመሆን ተቀናጅቶና ተናቦ መስራት ተገቢ መሆኑን በማመላከት የውሳኔ አቅጣጫ አስተላልፏል።

ዩኒቨርሲቲው የ2013 በጀት ዓመት የኦዲት ግኝት ላይ ፈጣን የማስተካከያ እርምጃ በመውሰድ ያሳየው ቁርጥኝነት እና በቀጣይ ጊዜያትም ከኦዲት ግኝት መሉ በሙሉ ነጻ ለመሆን የያዘው አቋም ሥራ አመራር ቦርዱ በጥንካሬ ገምግሟል።

መንግስት የትምህርት ተደራሽነት፣ ፍትሀዊነት አግባብነትና ጥራት ለማረጋገጥ ተግባራዊ እያደረገ ካለው በርካታ የሪፎርም ስራዎች አንዱ በሆነው “የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መዋቅራዊ አደረጃጀትና የሰው ኃይል ምደባ” በተመለከተም ሥራ አመራር ቦርዱ በስፋት ተወያይቷል።

አሁን ላይ መዋቅራዊ አደረጃጀቱና የሰው ኃይል ጥናቱ ተጠናቅቆ ለትግበራ መላኩ በመድረኩ የተገለጸ ሲሆን፤ በአዲሱ መዋቅር መሠረት የአመራር ቦታዎች ምደባ የአፈጻጸም አቅጣጫ መመሪያው በሚፈቅደው አግባብ በፍጥነት ተግባራዊ እንዲደረግ ሥራ አመራር ቦርዱ ወስኗል።

በመጨረሻም የዩኒቨርሲቲው ሴኔት ገምግሞ ባቀረበው ጥያቄ መሰረት ሥራ አመራር ቦርዱ ለዶ/ር መስፍን ቢቢሶ በአፈር ምርምር ሳይንስ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ (Professor of Soil Science) ሰጥቷቸዋል፡፡

የዩኒቨርሲቲው ሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢና የኢፌድሪ ሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር የሆኑት አቶ ብናልፍ አንዷለም ተቋሙ በመማር ማስተማር፣ በምርምር፣ በማህበረሰብ አገልግሎት፣ ቴክኖሎጂ ሽግግርና ስርጸት እንዲሁም በሌሎች የሥራ መስኮች የጀመራቸውን ተግባራት አጠናክሮ እንዲቀጥል የሥራ መምሪያ አስተላልፈዋል።

ዕውቀትን በተግባር!!

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት!!
1.5K viewsedited  16:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-07 19:24:02
1.5K views16:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-05 17:40:07 በዩኒቨርሲቲው “በከተማ መሬትና ፕላን ዘርፍ” በተለያዩ የሙያ ደረጃዎች ለ45 ቀናት ሲሰጥ የቆየው ሥልጠና ተጠናቆ የመዝግያ መርሀ ግብር ተካሂዷል።

ከደረጃ 2-5 ባሉ አራት የሙያ ደረጃዎች ስልጠናውን ላጠናቀቁ 200 ሰልጣኞች የሙያ ብቃት ምዘና (COC) ከነገ ጀምሮ የሚሰጥ መሆኑም ተመላክቷል።
______

ዩኒቨርሲቲው ከፌዴራል ከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር “በከተማ መሬትና ፕላን ዘርፍ” ያዘጋጀው የስልጠናና የሙያ ብቃት ምዘና (COC) ባለፉት 45 ቀናት  ሲካሄድ ቆይቷል። 

የስልጠናው መጠናቀቅን ተከትሎ በተካሄደ የመዝግያ መርሃ ግብር ላይ የተገኙት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ፕ/ር ታከለ ታደሰ፡ እንደ ሀገር የከተማ መሬት ይዞታ ምዝገባና መረጃ አስተዳደር ስርዓት ያልዘመነ እንዲሁም ለብልሹ አሰራር የተጋለጠ መሆኑን ገልጸዋል።

ዘርፉን ማዘመን እንዲቻል ተቋማት የጋራ ርብርብ ሊያደርጉ ይገባል ያሉት ፕሬዝዳንቱ፤ በከተሞች ከመሬት አስተዳደር ጋር ተያይዞ የሚታየውን የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መቅረፍ የቅድምያ ቅድምያ ሊሰጠው ይገባል ብለዋል።

ዩኒቨርሲቲው በዘርፉ ለሚስተዋለው የተወሳሰበ ችግር የተቀናጀ ምላሽ መስጠት እንዲያስችል ከከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር የከተሞች ገቢዎች ሪፎርም ፕሮጄክት ጽ/ቤት ጋር ስምምነት በመፈራረም "በሰለጠ የሰው ኃይል ልማት ዘርፍ" በአጋርነት እየሰራ መሆኑን ፕ/ር ታከለ ጠቁመዋል።

ዩኒቨርሲቲው “በከተማ መሬትና ፕላን ዘርፍ” ከደረጃ 2-5 ባሉ አራት የሙያ ደረጃዎች "ስልጠናና የሙያ ብቃት ምዘና (COC)" እንዲሰጥ ሕጋዊ ዕውቅና የተሰጠው ተቋም መሆኑንም ፕሬዝዳንቱ ገልጸዋል።

በተሰጠው ዕውቅና መሰረት በከተማ ፕላን እና መሬት አስተዳደር፣ በካዳስተር ቅየሳና ካርታ ዝግጅት፣ በመሬት መረጃ ምዝገባ እንዲሁም በቋሚ ንብረት ግመታና ግምገማ ዘርፍ ስልጠናና የሙያ ብቃት ምዘና (COC) እየሰጠ ይገኛል ሲሉ ፕ/ር ታከለ አሳውቀዋል።

ለሁለት ተከታታይ ዓመታት ከደረጃ 2-5 ባሉ አራት የሙያ ዘርፎች ተቋሙ ባካሄደው "ስልጠናና የሙያ ብቃት ምዘና (COC)" ብቁ እና ተወዳዳሪ ባለሙያዎችን ከማሰልጠን ረገድ ሀገራዊ ሀላፊነቱን በሚገባ እየተወጣ እንደሆነም አመላክተዋል።

በማህበራዊ ሳይንስና ስነ-ሰብ ኮሌጅ የጂኦግራፊና አካባቢ ጥናት ትምህርት ክፍል አመራሮችና አሰልጣኞች ስልጠናው በንድፈ ሀሳብ፣ በላቦራቶሪና በመስክ ቅየሳ ጥራቱን ጠብቆ እንዲሰጥ በማድረጋቸው ሊመሰገኑ ይገባል ሲሉ ፕሬዝዳንቱ  ተናግረዋል።

በፌዴራል የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር የከተሞች ገቢዎች የሪፎርም ፕሮጄክት ጽ/ቤት ተወካይ የሆኑት አቶ ሰለሞን ጴጥሮስ፡ የስልጠናና የብቃት ማረጋገጫ ምዘናው  በከተሞች ከመሬት አስተዳደር ጋር ተያይዞ የሚታየውን የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን እንዲቀረፉ ማስቻል ነው ብለዋል።

የከተማ መሬት ይዞታ ምዝገባና መረጃ ስርዓት በማዘመን ዘላቂ መፍትሄን ለማበጀት ሙያዊ ስልጠናና ምዘናው ጉልህ ጠቀሜታ እንዳለው የተናገሩት ተወካዩ፤ ሰልጣኞች በንድፈ ሀሳብና በተግባር ያገኙትን እውቀትና ክዕሎት በመጠቀም ሙያዊ ግዴታቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል።

የደቡብ ክልል የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ ተወካይ የሆኑት አቶ ዳዊት ኃይሉ በበኩላቸው ከተሞች በፕላን እንዲመሩና ከመሬት ጋር ተያይዞ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ችግሮች እንዲቀረፉ ስልጠናው ካለው ጠቀሜታ ረገድ ይበልጥ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል።

መንግስት በሀገር ደረጃ ከተሞች ያላቸውን የመሬት ሀብት በአግባቡ እንዲያውቁት እና እንዲያስተዳሩ ባስቀመጠው አቅጣጫ ዘርፉን የሚመጥን ባለሙያ ከማፍራት ረገድ ዩኒቨርሲቲው ላበረከተው አስተዋጽኦ ሊመሰገን ይገባል ብለዋል።

በማህበራዊ ሳይስና ስነ-ሰብ ኮሌጅ የጂኦግራፊና አከባቢ ጥናት ት/ክፍል መምህርና የፕሮጀክቱ አስተባባሪ የሆኑት ረዳት ፕ/ር መለሰ ማንዳዶ፡ በስልጠናውና የምዘና ሂደት የፕላን፣ የመሬት ልማት እና የከተማ መሬት ይዞታ ምዝገባና መረጃ ዘርፍ ባለሙያዎች የተሳተፉ መሆኑን ጠቁመዋል።

ዩኒቨርሲቲው በ 16 የሙያ ደረጃዎች ስልጠና መስጠትና በደረጃ 5 የብቃት ማረጋጋገጫ ምዘና ማካሄድ እንዲችል እውቅና የተሰጠው ተቋም መሆኑን የፕሮጀክቱ አስተባባሪ ተናግረዋል።

በ2ኛ ዙር በተካሄደ ስልጠናና ምዘና መርሀ ግብር ከደቡብ፣ ከሲዳማ እና ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ የተወጣጡ 200 የዘርፉ ባለሙያዎች የተሳተፉ መሆኑንም ገልጸዋል።

ሰልጣኞች ስልጠናውን ማጠናቀቃቸው የሚገልጽ ደረጃዉን የጠበቀ የምስክር ወረቀት እንደተበረከተላቸው ረዳት ፕ/ር መለሰ አሳውቀው፤ ከነገ ጀምሮ የሙያ ብቃት ምዘና(COC) እንደሚሰጣቸውም ጠቁመዋል።
1.4K views14:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-05 17:40:01
1.4K views14:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-05 05:22:35
1.6K views02:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-16 20:23:43
2.8K views17:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-16 20:23:31
2.8K views17:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-16 19:54:26 የገንዘብ ድጋፍ ያስገኙ መምህራን እና የምርምር ውጤት ስራዎችን በታዋቂ ጆርናል በብዛት ያሳተሙ ኮሌጆች እውቅና ተሰጣቸው።
_______

ለዩኒቨርሲቲው የገንዘብ ድጋፍ (fund) ላስገኙ መምህራን እንዲሁም የምርምር ውጤት ስራዎችን እውቅና ባለው ጆርናል (Acredited Journal) በብዛት ላሳተሙ ኮሌጆች ነው የዕውቅና መርሃ ግብሩ የተዘጋጀው።

በመድረኩ የተገኙት የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር መስፍን ቢቢሶ እንደገለጹት፡ ዕውቅናው ዩኒቨርሲቲው «የአፕላይድ ሳይንስ ዩኒቨርሲቲ» ከሆነበት ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ የተሰሩ ተግባራትን አፈጻጸም መሠረት ያደረገ ነው ብለዋል።

እውቅናው በግል ተነሳሽነት ከተለያዩ ዓለም አቀፍና ሀገራዊ ተቋማት ጋር በመጻጻፍ ለፕሮጀክቶች ማፈፀሚያ የሚውል የገንዘብ ድጋፍ (Fund) ላመጡ 26 መምህራን እንዲሁም የጥናትና ምርምር ውጤት ስራዎችን እውቅና ባለው ጆርናል (Acredited Journal) ላሳተሙና ከ1ኛ-3ኛ ደረጃ ለወጡ ኮሌጆች የተዘጋጀ መሆኑን ምክትል ፕሬዝዳንቱ ገልጸዋል።

ሀብት በማፈላለግ ረገድ ውጤታማ በመሆን ዕውቅና ከሚሰጣቸው 26 ፕሮጀክቶች 19 የምርምር ፕሮጀክቶች እንዲሁም 7 ያህሉ ደግሞ የማህበረሰብ አገልግሎት ፕሮጀክቶች መሆናቸውንም ጠቁመዋል።

ዓለም አቀፍ የጥናት ሰነዶችን ዋቢ በማድረግ ዶ/ር መስፍን ሲናገሩ፡ “ባደጉ ሀገራት እና ባላደጉ ሀገራት የሚሰሩ የጥናት እና ምርምር ስራዎች ከፍተኛ የሆነ የጥራት ልዩነት እንዲሁም ከችግር ፈቺነት ረገድ ብዙ እንደሚቀራቸው ተናግረዋል።

የጥናትና ምርምር ሥራዎችን ዕውቅና ባላቸው ጆርናሎች ከማሳተም ባለፈ፤ በምሁራን የሚሰሩ የምርምር ስራዎች ለፖሊሲ ግብዓት የሚሆኑ እንዲሁም የሕብረተሰቡን ችግር በተጨባጭ የሚፈቱ ሊሆኑ ይገባል ሲሉም ገልጸዋል።

በዩኒቨርሲቲው ምሁራን የሚሰሩ የጥናትና ምርምር ስራዎች የተቋም ተልዕኮን እና የትኩረት መስክን መሰረት በማድረግ እየተተገበረ መሆኑን የገለጹት ምክትል ፕሬዝዳንቱ፤ በቀጣይ ጊዜያት በተመራማሪዎች የሚሰሩ የምርምር ሥራዎች የሕብረተሰቡን ችግርን በተጨባጭ ሊፈቱ የሚችሉ ሊሆን ይገባል ብለዋል።

የዕውቅና መድረኩ የተዘጋጀውም በሀብት አፈላለግ ረገድ ውጤታማ የሆኑ አንጋፋ መምህራንንና ተመራማሪዎችን ለማበረታታት እና ልምዳቸውን ለሌሎች እንዲያጋሩ መሆኑን ዶ/ር መስፍን አሳውቀዋል።

በመድረኩ የተገኙት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ተወካይና የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሙላቱ ዴአ በበኩላቸው፡ “እንደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ከፍ ብለን እንድንታይ ከሚያደርጉ ተግባራት አንዱ እና ዋንኛው ጥራት ያለውን የምርምር ውጤት በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ባለው ጆርናል ማሳተም ነው” ብለዋል።

“ከፍ ብለን ለመታየት ደግሞ የጥናትና ምርምር ውጤቶችን ጽፎ በማሳተም ሼልፍ ላይ መደርደር ሳይሆን፤ ዘርፈ ብዙ ችግሮቻችንን መፍታት በሚያስችል መልኩ መሬት ላይ ማውረድ እና መተግበሩ ነው” ሲሉም የፕሬዝዳንቱ ተወካይ ገልጸዋል።

መምህራን የጥናትና ምርምር ስራ ላይ በስፋት እንዳይሳተፉ የበጀት ውስንነት እንዳለ የገለጹት ዶ/ር ሙላቱ፤ ከውስጥ ገቢም ቢሆን በቀጣይ ተመራማሪዎችን የምንደግፍ ይሆናል ሲሉ ተናግረዋል።

ሀብት በማፈላለግ ረገድ ብዙ ውጣ ውረድ በማለፍ ውጤታማ ስራ ለሰሩ ተመራማሪዎች ዕውቅና መስጠት ተገቢ ነው ያሉት ምክትል ፕሬዝዳንቱ፤ ተመራማሪዎችን ማበረታታት የበለጠ የሞራል ስንቅ በመሆን ለላቀ ስራ ያነሳሳቸዋል ሲሉ አውስተዋል።

ከ2013 ዓ.ም ወዲህ ለምርምር እንዲሁም ለማኅበረሰብ አገልግሎት ፕሮጀክቶች የገንዘብ ድጋፍ ከተለያዩ ተቋማት ያመጡ መምህራንና ተመራማሪዎች ስለ ፕሮጀክቱ ልምድና ተሞክሯቸውን ያጋሩበትን ቁልፍ ንግግር አድርገዋል።

በመድረኩ ሀብት በማፈላለግ ረገድ ውጤታማ ለሆኑ 26 መምህራን እና ተመራማሪዎች የዕውቅና ምስጋና ምስክር ወረቀት የተበረከተ ሲሆን፤ ዕውቅናው 19 በምርምር፥ 7ቱ ደግሞ በማህበረሰብ አገልግሎት ዘርፍ መሆኑ ተመላክቷል።

በዩኒቨርሲቲ ደረጃ በርካታ የጥናት እና ምርምር ስራዎችን ታዋቂ በሆኑ ጆርናሎች (Acredited Journal) በማሳተም ከ1ኛ-3ኛ ደረጃ የወጡ ኮሌጆችም በመድረኩ እውቅና ተሰጥቷቸዋል።

በመርሀ ግብሩ ሕክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ 1ኛ፣ ተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ 2ኛ እንዲሁም ግብርና ኮሌጅ 3ኛ በመሆን በደረጃ ሰንጠረዥ ዕውቅና አግኝተዋል።

የእውቅና ሥነ-ስርዓት ተሳታፊዎች ውይይት በማድረግ እና ለቀጣይ ስራ ግብዓት የሚሆን ገንቢ አስተያየት በመስጠት መርሃ ግብሩ ተጠናቋል።

➭ «ዕውቀትን በተግባር!!»

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት!!

➤ መጋቢት 07/2015 ዓ.ም

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት

ፌስWolaita Sodo Universityty4/

ቴሌግራም፡https://t.me/WolaitaSUniversity

ዩቲዩብ፡ https://www.youtube.com/channel/UC6VukdZbl5iVgZGXG8BkMdw/videos

ዌብሳይት፡ http://www.wsu.edu.et/

ትዊተር፡ https://twitter.com/WSodoUniversity?t=w_VzjrOWj3D3Mc8BKlQFXA&s=09

ሊንክዲን፡ https://www.linkedin.com/company/wolaita-sodo-university/

ኢንስታግራም፡ https://instagram.com/wolaita_sodo_university?igshid=YmMyMTA2M2Y=

አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን
2.6K views16:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-16 19:54:25 በዩኒቨርሲቲው የወላይትኛ ቋንቋ ሰዋሰው መጽሐፍ ተመረቀ። (ወሶዩ፤ መጋቢት 07/2015 ዓ.ም)

በታሪክ የመጀመሪያው የሆነና ደረጃውን የጠበቀ የወላይትኛ ቋንቋ ሰዋሰው መጽሐፍ ተመረቀ።
_______
በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ምርምርና ማኅበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት፤ በማህበረሰብ አገልግሎት ፕሮጀክት የገንዘብ ድጋፍ የታተመ መሆኑ በምረቃው ሥነ ስርዓት ተገልጿል።።

በመጽሐፉ ዝግጅት ከዩኒቨርሲቲው ማህበራዊ ሳይንስና ሥነ-ሰብ ኮሌጅ ከወላይትኛ ቋንቋ ትምህርት ክፍል 4 መምህራን እንዲሁም ከወላይታ ዞን የተውጣጡ ሁለት የቋንቋ ባለሙያዎች ተሳትፈውበታል።

ከወላይትኛ ቋንቋ ትምህርት ክፍል አባል በመሆን መጽሀፉን በማዘጋጀት የተሳተፉት ወ/ሮ አየለች በመድረኩ እንደገለጹት፡ "ይህ የሰዋሰው መጽሐፍ በዓይነቱ የመጀመሪያ እና ደረጃውን ጠብቆ ለየት ባለ መልኩ የታተመ ነው" ብለዋል።

የመጽሐፉ ዝግጅት 3 ዓመታትን ያስቆጠረ መሆኑን የገለጹት መምህርት አየለች፤ ከ2012–2015 ዓ.ም ደረስ ባሉት ሶስት ተከታታይ ዓመታት መጽሀፉን ለማዘጋጀት የጥናትና ምርምር ስራ ተሰርቷል ሲሉም ገልጸዋል።

ሥነ ቃላቱ በአጠቀላይ ከሕብረተሰቡ የተሰበሰቡ መሆኑን በመግለጽም፤ የሥራው ባለቤት የወላይታ ሕዝብ መሆኑን ተናግረዋል።

መጽሐፉ ሕዝብን በመጠየቅ እና በማወያየት መልሶ ሕዝብን እንዲያገለግል መዘጋጀቱን የገለጹት መምህርት አየለች፤ መጽሐፉ ለተማሪዎች፥ ለመምህራን እንዲሁም ለመላው ሕዝብ ጥቅም ይውላል ሲሉ አሳውቀዋል።

የወላይትኛ ቋንቋ ራሱን የቻለ የአጻጻፍ ይትብሃል አለው ያሉት መምህርቷ፤ በቋንቋው በዘፈቀደ አይጻፍም በማለትም ቋንቋው "ደረጃውን የጠበቀ" እንዲሆን በቀጣይ ሰፊ ስራ ለመስራት እቅድ ተይዟል ብለዋል።

በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የቋንቋ መምህር እና ተመራማሪ እንዲሁም የመጽሐፉ አርታኢ የሆኑት ዶክተር ፍሬው ደጀኔ በበኩላቸው፡ ቋንቋውን የበለጠ በማሳደግ ረገድ ከሁላችን የጋራ ርብርብ ይጠበቃል በማለት ተናግረዋል።

በዩኒቨርሲቲው ምሁራን ለመጀመሪያ ጊዜ የተዘጋጀው ይህ የወላይትኛ ቋንቋ ሰዋሰው መጽሐፍም በታሪክ የመጀመሪው በመሆን ደረጃውን በጠበቀ መልኩ የታተመ መጽሐፍ መሆኑን ጠቁመዋል።

ወላይትኛ "የጽሑፍ ቋንቋ" የሆነው በ1916 ዓ.ም መሆኑን የገለጹት ዶ/ር ፍሬው፤ ቋንቋው በሚፈለገው ልክ አላደገም፥ እስከአሁን የሥራ ቋንቋም አልሆነም ብለዋል። የመጽሐፉ መዘጋጀት ከማጣቀሻነት ባለፈ ለጥናትና ምርምር እንዲሁም በሂደት ዘርፈ ብዙ አገልግሎት እንደሚኖረው በመጠቆም።

መጽሐፉ ደረጃውን ጠብቆ በጥራት የተዘጋጀ የመጀመሪያው «የወላይትኛ ቋንቋ ሰዋሰው መጽሐፍ» መሆኑን አርታኢው ተናግረው፤ መጽሐፉ በሚገባ ተገምግሞ ተገቢው እውቅና የተሰጠውና ለህዝብ አገልግሎት ጥቅም ላይ እንዲውል ይሁኝታ ማግኘቱን ገልጸዋል።

በመድረኩ የተገኙት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ተወካይና የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሙላቱ ዴአ፡ መጽሐፉ በቋንቋ ባለሙያዎች መዘጋጀቱ ለቋንቋውን ዕድገት እና ለቋንቋው ባለቤት ህዝብ እጅግ ከፍተኛ ፋይዳ አለው፥ የዘርፉን የቋንቋ ዕድገትም አንድ እርምጃ ከፍ ያደርገዋል ብለዋል።

መጽሐፉ በዛሬው ዕለት መመረቁን እና ለንባብ መብቃቱን በተቋሙ እና በራሴ ስም አበስራለሁ ያሉት ዶ/ር ሙላቱ፤ ከዚህ በኋላም ለመሰል የህትመት ስራዎች እናበረታታለን ሲሉም አሳውቀዋል።

የዩኒቨርሲቲው ምርምርና ማሕበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር መስፍን ቢቢሶ በበኩላቸው፡ ለባህል፣ ቋንቋ፣ ታሪክ እና ቅርስ ዕድገት በምርምር እና ማህበረሰብ አገልግሎት ዘርፍ ሰፊ ስራዎች የተሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።

ከቋንቋ እድገት አንጻር የወላይትኛ ቋንቋ ሰዋሰው መጽሐፍ ድጋፍ የተደረገለት የመጀመሪያው የመጽሐፍ ህትመት አለመሆኑን ምክትል ፕሬዝዳንቱ ጠቁመው፤ ከዚህ ቀደም ለተለያዩ የመጽሐፍ ሕትመቶች መሰል ድጋፍ መደረጉንም አሳውቀዋል።

መሰል ሕዝብን የሚጠቅሙ፥ ዘላቂ ለውጥ የሚያመጡና ፋይዳ ያላቸውን ፕሮጀክቶች በቀጣይ ጊዜያትም በገንዘብ እና በቁስ እና በሀሳብ እንደግፋለን በማለት ዶ/ር መስፍን ተናግረዋል።

ለመጽሐፉ አዘጋጆች እና ለቋንቋው አርታኢያን ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋጽኦ የምስጋና ምስክር ወረቀት በመድረኩ ተበርክቶላቸዋል።

በዛሬው ዕለት የተመረቀው ባለ 192 ገጽ «የወላይትኛ ቋንቋ ሰዋሰው መጽሐፍ» ለንባብ መብቃቱ በመጽሐፉ የምረቃ ሥነ-ስርዓት ተመላክቷል።

➭ «ዕውቀትን በተግባር!!»

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት!!

➤ መጋቢት 07/2015 ዓ.ም

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት

ፌስWolaita Sodo Universityty4/

ቴሌግራም፡https://t.me/WolaitaSUniversity

ዩቲዩብ፡ https://www.youtube.com/channel/UC6VukdZbl5iVgZGXG8BkMdw/videos

ዌብሳይት፡ http://www.wsu.edu.et/

ትዊተር፡ https://twitter.com/WSodoUniversity?t=w_VzjrOWj3D3Mc8BKlQFXA&s=09

ሊንክዲን፡ https://www.linkedin.com/company/wolaita-sodo-university/

ኢንስታግራም፡ https://instagram.com/wolaita_sodo_university?igshid=YmMyMTA2M2Y=

አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን
2.6K views16:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-05 18:22:53
1.4K views15:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ