Get Mystery Box with random crypto!

Wolaita Sodo University

የቴሌግራም ቻናል አርማ wolaitasuniversity — Wolaita Sodo University W
የቴሌግራም ቻናል አርማ wolaitasuniversity — Wolaita Sodo University
የሰርጥ አድራሻ: @wolaitasuniversity
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 18.46K
የሰርጥ መግለጫ

This is the official telegram channel of Wolaita Sodo University
Our Official Website :
http://www.wsu.edu.et/
Our Official Facebook page :
https://m.facebook.com/Wolaita-Sodo-University-246568056057804

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2023-03-05 18:21:39 ለመውጫ ፈተና (Exit Exam) እየተካሄደ ያለው የቅድመ ዝግጅት ተግባር አፈጻጸም ከትምህርት ሚኒስትር በመጡ ግብረ-ኃይል አባላት ተገምግሟል።

የዩኒቨርሲቲው አስተዳደርም «አንድም ተማሪ በመውጫ ፈተና (Exit Exam) ምክንያት መውደቅ የለበትም» በሚል አቋም እየሰራ መሆኑን አሳወቋል።
___
ለመው
ጫ ፈተናው እየተካሄደ ያለው የቅድመ ዝግጅት ተግባር ያለበትን ደረጃ አስመልክቶ በተካሄደ የግምገማ መድረክ የዩኒቨርሲቲው ማኔጅማንት አባላት፣ የኮሌጅ እና የትምህርት ቤት ዲኖች ተሳትፈዋል።

በመድረኩ ትምህርት ሚኒስቴር ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት የቅድመ ዝግጅት ሥራው በታቀደው አግባብ እና በተቀናጀ መልኩ ተግባራዊ እየሆነ መምጣቱ ተብራርቷል።

ዩኒቨርሲቲው “አንድም ተማሪ በመውጫ ፈተና ምክንያት መውደቅ የለበትም” የሚል አቋም ይዞ የቅድመ ዝግጅት ስራውን በተቀመጠው ስታንዳርድ መሰራት እየሰራ መሆኑን አሳውቋል።

መውጫ ፈተናው በኦንላይን እንደሚሰጥ የትምህርት ሚኒስቴር ባሳወቀው መሰረት በዩኒቨርሲቲው የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች አዲስ የለማ መተግበሪያ ሶፍትዌር በፈተናው ወቅት ጥቅም ላይ እንዲውል መዘጋጀቱም ተጠቁሟል።

መውጫ ፈተናው የሚወስዱ ተማሪዎች በየጊዜው የመውጫ ፈተናን በተመለከተ የግንዛቤ ማስጨበጫ እንዲሰጣቸው በማድረግ ተገቢው የሥነ ልቦና እና የዕውቀት ዝግጅት እንዲኖራቸው መደረጉም ተመላክቷል።

የአይሲቲ መሠረተ ልማት ዝርጋታ፣የሞጁል
እና የሞዴል ፈተና አደረጃጀት እንዲሁም ተማሪዎችን በአእምሮና በስነ ልቦና ከማዘጋጀት አንፃር የተከናወኑት ስራዎች አበረታች በመሆን በግብረ ኃይሉ በጥንካሬ ተገምግሟል።

ለተመራቂ ተማሪዎች ግንዛቤ በመፍጠር በእውቀት፥ በክህሎት፣ በአመለካከት እና በስነ ልቦና ዝግጁ እንዲሆኑ እየተሰራ ያለው ተግባር የበለጠ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም ግብረ ኃይሉ አቅጣጫ አስቀምጧል።

የዩኒቨርሲቲው የመውጫ ፈተና ቅድመ ዝግጅት ዕቅድ አፈጻጸም አሁን ያለበት ደረጃ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የበለጠ ቅንጅት እና ትብብር አስፈላጊ መሆኑን ግብረ ኃይል አባላቱ አመላክተዋል።

መውጫ ፈተናው ተማሪዎች በተማሩበት የትምህርት መስክ የሚፈለግባቸውን ክህሎት ማግኘታቸውን የሚለካ በመሆኑ ተፈታኞች ከወዲሁ ዝግጅት ማድረግ ይኖርባቸዋል በማለት አስተያየት ሰጥተዋል።

የዩኒቨርሲቲው ማናጅመንት፣ የኮሌጅ እና የትምህርት ቤት ዲኖች ከግብረ-ኃይል አባላት ጋር በመሆን የአይ.ሲ.ቲ ላብራቶሪዎችን፣ የኤሌክትሮኒክስ ቤተ-መጻሕፍቶችን፣ የማንበቢያ ክፍሎችን እንዲሁም ሌሎች የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ጎብኝተዋል።
══════════════════
The implementation of the preparatory work for the Exit Exam was evaluated by the task force members from the Ministry of Education.

The administration of the university announced that "no student should fail due to the exit exam".
___
Members of the university management, college and school deans participated in an evaluation forum on the status of the preparation for the exit exam.

According to the direction set by the Ministry of Education, it was explained that the preparatory work is being implemented in the planned and in a coordinated manner.

The university has stated that "no student should fail due to the exit exam" and is doing the preparatory work according to the standards.

According to the Ministry of Education's announcement that the exit exam will be offered online, a new application software to be used during the exam has been developed by the university's technologists.

It was also pointed out that the students taking the exit exam should be regularly informed about the exit exam so that they have the appropriate psychological and knowledge preparation.

ICT infrastructure development;the organization of the module and model test as well as the motivational work done in terms of preparing students intellectually and psychologically was strongly evaluated by the task force.

The task force has set a direction that the work being done to create awareness for graduate students in terms of knowledge, skills, attitudes and psychology should be strengthened.

The members of the task force pointed out that more coordination and cooperation is necessary to strengthen the implementation of the university's exit exam preparation plan.

The task force finally said that the exit exam measures whether students have acquired the required skills in the field of study, so the examinees should prepare themselves properly.

The university management, college and school deans along with the task force members visited the ICT laboratories, electronic libraries, reading rooms and other preparatory works.
1.4K viewsedited  15:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-04 19:01:12
ስለ ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ «ሆስፒታሊቲ እና ቱሪዝም ማሰልጠኛ ማዕከል» በጥቂቱ
═════════❁✿❁═════════
➧ በወላይታ ሶዶ ከተማ ኮካቴ ማራ ጫሬ ቀበሌ እየተገነባ ያለ ባለ አምስት ወለል (G+5) የሆስፒታሊቲና ቱሪዝም ማሰልጠኛ ማዕከል ሕንጻ ነው፤

➧ የማዕከሉ ግንባታ አለም አቀፍ የጥራት ደረጃን በጠበቀ መልኩ እየተገነባ ያለ ዘመናዊ ሕንጻ ሲሆን፤ 150 የመኝታ ክፍሎች አሉት፤

➧ ማዕከሉ የተማሪዎች መማሪያ ክፍሎችን፣ መመገቢያ እና መሰብሰቢያ አዳራሾችን፣ የተሟላ የግብይት አገልግሎት የሚሰጡ ሱቆችን፣ ማሳጅ ቤቶችን፣ ክሊኒክ፣ ላውንደሪ ቤት፣ ፕሌይ ስቴሽን እና ልዩ ልዩ የመዝናኛ ስፍራዎችን ያካትታል፤

➧ ማዕከሉ በሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍ ብቁ የሰው ኃይል አስተምሮ እና አሰልጥኖ ከማፍራት ባሻገር፤ ለአካባቢው የቱሪዝም እድገት ጉልህ ሚና ይጫወታል፤

➧ ማዕከሉ በሆቴል መስክ ኢትዮጵያ ውስጥ ካሉ ባለ አራት ኮከብ ሆቴሎች በማይተናነስ መልኩ አገልግሎት የሚሰጥ ይሆናል፤

➧ ማዕከሉ ግንባታው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር ለከተማው ዕድገት የራሱ አዎንታዊ አበርክቶ ይኖረዋል፤

➧ ማዕከሉ በታቀደው አግባብ በተሟላ መልኩ ወደ ስራ ሲገባ ለበርካታ የአካባቢው ወጣቶች ምቹ የስራ እድል ይፈጥራል፤

➧ ማዕከሉ የውስጥ ገቢን ከማሳደግ ረገድ ጉልህ ፋይዳ እንደሚኖረው ይጠበቃል፤

➧ የሕንጻው ውስጣዊ ውቅር (ኢንቴርየር ዲዛይን) የወላይታን ብሔር ባሕላዊ ዕሴት በጠበቀ መልኩ ይዋቀራል፤

➧ የማዕከሉ የግንባታ ሂደት 95 ከመቶ በላይ የደረሰ ሲሆን፤ በቅርቡ ግንባታው መሉ በሙሉ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት የሚጀምር መሆኑን የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር አሳውቋል፤

ዕውቀትን በተግባር!!

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት!!
480 views16:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-04 18:46:58
#ማስታወቂያ

➧በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ለሬሜዲያል (Remedial) ፕሮግራም የተመደባችሁ ተማሪዎች በሙሉ
═════════❁✿❁═════════
በ2014 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ለሬሜዲያል (Remedial) ፕሮግራም የተመደባችሁ ተማሪዎች እንኳን ደስ አላችሁ እያልን፤ የመግቢያ ጊዜ ከመጋቢት 1-2/2015 ዓ.ም ድረስ የሚከናወን መሆኑን እንገለጽን፤ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲው ስትመጡ፦

1ኛ/ መሰናዶ ያለፋችሁበትን(የ12ኛ ክፍል) ሰርተፍኬት፣

2ኛ/ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት

3ኛ/የ8ኛ ክፍል ሰርትፍኬት ዋና እና ፎቶ ኮፒ፤

4ኛ/ ጉርድ ፎቶ ግራፍ (3x4) ብዛት 4፤

5ኛ/የሌሊት ልብስ አልባሳት–ብርድ ልብስ፣ አንሶላ፣ ትራስ ልብስ እንዲሁም የስፖርት ትጥቅ ይዛችሁ መምጣት ይጠበቅባችኋል።

ማሳሰቢያ፦

➤ ከተጠቀሰው ቀን ቀድሞም ሆነ ዘግይቶ መምጣት አይፈቀድም።

➣ የመጀመሪያው ቀን የሬሜዲያል (Remedial) ትምህርት ፕሮግራም የሚጀመረው መጋቢት 4/2015 ዓ.ም መሆኑን አውቃችሁ በተጠቀሰው የመግቢያ/ምዝገባ ቀን ለመገኘት ከወዲሁ ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳስባለን።

እንኳን ተወዳዳሪ፣ አረንጓዴ፣ ጽዱ፣ ሠላማዊ እና ሕብረ- ብሔራዊ ወደሆነው ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በሠላም መጣችሁ!!

እውቀትን በተግባር

ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ

https://t.me/WolaitaSUniversity/1585
624 views15:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-04 09:05:46
#ማስታወቂያ

➧በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ለሬሜዲያል (Remedial) ፕሮግራም የተመደባችሁ ተማሪዎች በሙሉ
═════════❁✿❁═════════
በ2014 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ለሬሜዲያል (Remedial) ፕሮግራም የተመደባችሁ ተማሪዎች እንኳን ደስ አላችሁ እያልን፤ የመግቢያ ጊዜ ከመጋቢት 1-2/2015 ዓ.ም ድረስ የሚከናወን መሆኑን እንገልጻለን፡፡

ማሳሰቢያ፤

ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲው ስትመጡ የሚከተሉትን ይዛችሁ መምጣት ይጠበቅባችኋል፡፡

1ኛ/ መሰናዶ ያለፋችሁበት ሰርተፍኬት፣ ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል : ትራንስክሪፕት እና የ8ኛ ክፍል ካርድ፤

2ኛ/ የሌሊት አልባሳት፥ የስፖርት ትጥቅ እና 3x4 ጉርድ ፎቶ ግራፍ ብዛት 4 ይዛችሁ መምጣት እንዳለባችሁ እያሳሰብን፤ ከተጠቀሰው ቀን በፊትም ሆነ በኋላ የሚመጣ ተማሪ የማናስተናግድ መሆኑን በጥብቅ እናሳውቃለን።

ውድ ተማሪዎች መጋቢት 4/2015 ዓ.ም የመጀመሪያው ቀን የሬሜዲያል (Remedial) ፕሮግራም የሚጀመርበት ዕለት መሆኑን አውቃችሁ፤ በተጠቀሱት የመግቢያ/ምዝገባ ቀናት ለመገኘት ከወዲሁ ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳስባለን።

እንኳን ተወዳዳሪ፣ አረንጓዴ፣ ጽዱ፣ ሠላማዊ እና ሕብረ- ብሔራዊ ወደሆነው ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በሠላም መጣችሁ!!

እውቀትን በተግባር

ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ
2.6K views06:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-02 15:19:44
እንኳን ለ127ኛው የአድዋ ድል በዓል አደረሰን፤ አደረሳችሁ!!

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደር ለመላው ኢትዮጵያውያን በሙሉ እንኳን ለ127ኛው የአድዋ ድል በዓል ቀን በሠላም አደረሳችሁ በማለት መልዕክት ሲያስተላልፍ ላቅ ያለ ደስታ ይሰማዋል።

ቀደምት አባቶቻችን በድንቅ ህብረት ዓለምን ጉድ ላሰኙበት፤ ኢትዮጵያዊያን ብቻ ሳይሆኑ መላው ጥቁር ሕዝቦች ከነጭ የበላይነት፥ የመንፈስ ጭቆናና ብዝበዛ ነጸ ለወጡበት እንዲሁም የአለምን የታሪክ ቅርፅ ለቀየረው ለታላቁ የድል ብስራት በዓል ለሆነው «አድዋ» በሰላም አደረሰን፤ አደረሳችሁ

“የአድዋን የድል ቀን ስናከብር ሁላችንም የአያት ቅድመ አያቶቻችንን ጀግንነት በማሰብ ብቻ ሳይሆን ከእነርሱ ታሪክ አንድነት፣ ጽናትና ፍትሃዊ ተጋድሎ ምን ያህል ኃያል እንደሆነ ትምህርት ወስደን እኛም ዛሬ ላይ ሆነን ለመጪው ትውልድ የምናስረክባትን ጠናካራ እና የበለጸገች ኢትዮጵያን በጋራ ለመስራት በልባችን ቃል ኪዳን በመግባት መሆን አለበት፡፡”

የአድዋ ድል አንድነት፣ ጀግንነትና ጽናት

ክብር ለኢትዮጵያ ጀግኖች

[የካቲት 23/2015 ዓ.ም]

መልካም የድል በዓል!

ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ
1.1K views12:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-11 01:05:58
544 views22:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-11 01:05:45 በ2022 ዓ.ም «ቴክኖሎጂ መር የግብርና እና የጤና ልዕቀት ማዕከል» ለመሆን ራዕይ የሰነቀውን ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ የሚተገብራቸው አበይት ተግባራት

1. ፍትሃዊ፣ አካታችና ተደራሽ ትምህርትን ማረጋገጥ፤

2. በሥራ ገበያ ላይ ብቁና ተፈላጊ የሆነ የሰው ሀይል ማፍራት፤

3. ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና የሥራ ፈጠራ ማስፋፋት፤

4. በምርምር ላይ የተመረኮዘ የማህበረሰብ እና የአካባቢ ልማት ማስፋፋት፤

5. ጠንካራ የትምህርት ሥርዓት እና የማስፈጸም አቅም መፍጠር፤

➭ «ዕውቀትን በተግባር!!»

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት!!

➤ የካቲት 03/2015 ዓ.ም

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት

ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/Wolaita-Sodo-University-246568056057804/

ቴሌግራም፡https://t.me/WolaitaSUniversity

ዩቲዩብ፡ https://www.youtube.com/channel/UC6VukdZbl5iVgZGXG8BkMdw/videos

ዌብሳይት፡ http://www.wsu.edu.et/

ትዊተር፡ https://twitter.com/WSodoUniversity?t=w_VzjrOWj3D3Mc8BKlQFXA&s=09

ሊንክዲን፡ https://www.linkedin.com/company/wolaita-sodo-university/

ኢንስታግራም፡ https://instagram.com/wolaita_sodo_university?igshid=YmMyMTA2M2Y=

አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን
555 views22:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-10 14:53:28
827 views11:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-10 14:53:27 Congratulations

According to the 'Webometrics Ranking of World Universities' Wolaita Sodo University has been ranked 10th from Ethiopian universities, 252nd in Africa and 5063rd in the world.

#NB፡ 'Ranking of World Universities website' is not the ranking of universities' websites, but 'ranking of universities'; The website uses both webometric (all institutional missions) and bibliometric (research missions) indicators for ranking.

Knowledge in Action

For details see the link below፡
https://www.webometrics.info/en/Africa/Ethiopia
__

እንኳን ደስ አላችሁ

"የአለም ዩኒቨርሲቲዎች ዌቦሜትሪክስ ደረጃ" እንደገለጸው ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች 10ኛ፣ ከአፍሪካ 252ኛ እና ከአለም 5063ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።

#ማስታወሻ፡ «የአለም ዩኒቨርሲቲዎች ድህረ ገጽ ደረጃ» የዩኒቨርሲቲዎች ድረ-ገጾች ደረጃ ሳይሆን "የዩኒቨርሲቲዎች ደረጃ" ነው። ድር ጣቢያው ሁለቱንም ዌቦሜትሪክ (ሁሉንም ተቋማዊ ተልእኮዎች) እና ቢቢዮሜትሪክ (የምርምር ተልዕኮዎች) አመላካቾችን ለደረጃ ፍረጃ ይጠቀማል።

ዕውቀት በተግባር

ለዝርዝሩ ከዚህ በታች ያለውን ሊንክ ይመልከቱ

https://www.webometrics.info/en/Africa/Ethiopia
818 views11:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-09 19:53:40
ዩኒቨርሲቲው በጀርመን ሀገር ከሚገኘው ከሳሃይ ሶላር (Sahay Solar) ኢንስቲትዩት ጋር በአጋርነት ሊሰራ መሆኑ ተገለጸ።

ዩኒቨርሲቲው በጀርመን ሀገር ከሚገኘው ከሳሃይ ሶላር (Sahay Solar) ኢንስቲትዩት ጋር በአጋርነት ሊሰራ መሆኑ ተገለጸ።

ኢንስቲትዩቱ የፀሐይን ሀይል በመጠቀም በፀሃይ እና በታዳሽ ሃይል ልማት ላይ በስፋት የሚሰራ መሆኑ ተመላክቷል።
___________________________________
ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በጀርመን ሀገር ከሚገኘው ከሳሃይ ሶላር ኢንስቲትዩት (Sahay Solar) ጋር በፀሃይ እና በታዳሽ ሃይል ልማት ዘርፍ በአጋርነት የትብብር ማዕቀፍ ለመስራት እእንቅስቃሴ መጀመሩን የዩኒቨርሲቲው ዓለም…

http://www.wsu.edu.et/ዩኒቨርሲቲው-በጀርመን-ሀገር-ከሚገኘው-ከ/
486 views16:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ