Get Mystery Box with random crypto!

Wolaita Sodo University

የቴሌግራም ቻናል አርማ wolaitasuniversity — Wolaita Sodo University W
የቴሌግራም ቻናል አርማ wolaitasuniversity — Wolaita Sodo University
የሰርጥ አድራሻ: @wolaitasuniversity
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 18.46K
የሰርጥ መግለጫ

This is the official telegram channel of Wolaita Sodo University
Our Official Website :
http://www.wsu.edu.et/
Our Official Facebook page :
https://m.facebook.com/Wolaita-Sodo-University-246568056057804

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2023-07-05 16:36:50
1.7K views13:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-05 10:34:27
ትምህርት ሚኒስቴር ከሬሜዲያል ፕሮግራም ፈተናዎች ጋር በተያያዘ የተለያዩ ውሳኔዎች አሳለፈ
******************************

ትምህርት ሚኒስቴር ከሬሜዲያል ፕሮግራም ፈተናዎች ጋር በተያያዘ የተለያዩ ውሳኔዎች አሳልፏል።

ትናንት የተሰጡት የሬሜዲያል ፕሮግራም ፈተናዎች መሰረዛቸውን የትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።

የ2014 ዓ.ም 12ኛ ክፍል ረሜዲያል ተጠቃሚ ተማሪዎች ፈተና ትናንት ሰኔ 26/2015 ዓ.ም በዩኒቨርስቲዎች መሰጠት መጀመሩ ይታወቃል።

ይሁን እንጂ በፈተና ሂደት በተፈጠሩ ችግሮች ምክንያት የትምህርት ሚኒስቴር የሚከተሉትን ውሳኔዎች አሳልፏል።

1) ሰኔ 26/2015 የተሰጡት የሬሜዲያል ፕሮግራም ፈተናዎች ተሰርዘው ተማሪዎች በቀሩት የትምህርት ዓይነቶች ብቻ እንዲመዘኑ

2) ቀደም ብሎ በሁሉም ሬሜዲያል ፕሮግራም ተጠቃሚ ተማሪዎች ባላቸው ተቋማት ፈተናውን በአንድ ጊዜ ለመስጠት የታቀደው ተሻሽሎ በተለይም ከ150 በላይ የሆኑና ከ200 በላይ ካምፓስ ያላቸውን የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፈተና ቀርቶ ወደ ፊት በሚወሰን አግባብ ፈተናው በመስከረም ወር 2016 ዓ.ም እንዲሰጥ

3) በመንግስት ተቋማት የሬሜዲያል ፕሮግራም ተጠቃሚ የሆኑትን ተማሪዎች በተያዘው ፕሮግራም መሰረት የሚሰጥ መሆኑን የትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።
2.3K views07:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-04 20:22:07
# 2nd_Day National Mock Exit Exam Successfully Completed!!

Knowledge in Action!

Wolaita Sodo University
_

#
የ2ኛ_ቀን ሀገር አቀፍ የመልቀቂያ ሙከራ ፈተና በተሳካ ሁኔታ ተጠናቀቀ!!

እውቀትን በተግባር!

ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ
3.0K views17:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-06 19:42:41 #ጉብኝት-3( የአረንጓዴ አሻራ ልማት ሥራዎች)

ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ከኢ.ፌ.ዴ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር «ውጤታማ ተግባቦት ለኢትዮጵያ ልዕልና» በሚል ርዕሰ ጉዳይ ያዘጋጀውን ስልጠና ለመሳተፍ ከ 47 የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች እና ተጠሪ ተቋማት የመጡ የህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዘርፍ የሥራ ኃላፊዎች በዩኒቨርሲቲው እስካሁን የተከናወኑ እና ቀጣይ ለሚካሄደው ሁለተኛው ምዕራፍ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሀ ግብር የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን ጎብኝተዋል።

እንደ ተቋም ባለፉት አራት ዓመታት በተካሄደው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸውን የደን እና የሚበሉ የፍራፍሬ ችግኞችን በራሱ «ችግኝ ጣቢያ» አፍልቶ የመትከል እንዲሁም ለተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች እና ተቋማት ተደራሽ ሲያደርግ መቆየቱን በዩኒቨርሲቲው የአረንጓዴ አሻራ ልማት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት መ/ር ገለታው ከበደ ለጎብኝቱ ተሳታፊዎች አሳውቀዋል።

ዩኒቨርሲቲው ለሚበሉ የፍራፍሬ ዝርያዎች ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል በማለት ለጎብኝዎች ገላጻ ያደረጉት ዳይሬክተሩ፤ ተቋሙ ባቋቋመው ችግኝ ጣቢያ ከሚፈሉ ችግኞች አብዛኞቹ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ጠቀሜታ ያላቸው የፍራፍሬ ዝርያዎች እንዲሆኑ ጠቁመዋል።

በ2014 ዓም በዩኒቨርሲቲው በተካሄደ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በአንድ ጀምበር የደቡብ ክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት 10 ሺሕ የተዳቀለ ምርጥ የአቦካዶ ችግኝ ዝርያ መተከሉንም ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል። ይህን ተሞክሮ በመቀመር ለሁለተኛው ምዕራፍ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ ተገቢው ዝግጅት መደረጉን በመጠቆም

በሁለተኛው ምዕራፍ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሀ ግብር ሙሉ በሙሉ የሚበላ የፍራፍሬ ችችግኞችን ማዕከል ያደረገ እንዲሆን አቅጣጫ መቀመጡን የገለጹት መምህር ገለታው፤ ከመጀመሪያው ምዕራፍ የአረንጓዴ አሻራ ትግበራ በተሻለ መልኩ በሁለተኛው ምዕራፍ በጥራት፣ በእውቀትና በቴክኖሎጂ የታገዘ ትግበራ እንዲኖር ሰፊ ዝግጅት መደረጉንም ለጎብኝዎች አብራርተዋል።

በዘንድሮው ዓመት ለሚጀመረው የሁለተኛው ምዕራፍ 5ኛ ዙር የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ዩኒቨርስቲው ከፍተኛ የኢኮኖሚ ጠቀሜታ ያላቸውን 330 ሺሕ ምርጥ የአቦካዶ ችግኝ ዝርያዎችን በማፍላት ዩኒቨርሲቲው ሙሉ ዝግጅቱን እንዳጠናቀቀም ዳይሬክተሩ አሳውቀዋል።

ለተከላ ከተዘጋጁ የአቦካዶ ችግኝ ዝርያዎች 40,000 ያህሉን ሙሉ በሙሉ የማዳቀል (graft) የማድረግ ስራ የተከናወነ መሆኑን ለጎብኝዎቹ አሳውቀዋል።

የጉብኝቱ ተሳታፊዎች በገንደባ ካምፓስ የሚገኘውን የክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ(ዶ/ር) ፓርክ ጨምሮ ከዚህ ቀደም ተተክለው የጸደቁ ችግኞችን እና ለሁለተኛው ምዕራፍ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ የተዘጋጁ ችግኞችን ተዟዙረው ምልከታ አካሂደዋል።

የየዓመቱ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ዕቅድ እና አፈጻጸም መረጃ

➧ በ2011 ለመትከል የታቀደው 80 ሺህ ችግኝ ሲሆን፣ በድምሩ 100 ሺህ የደን ችግኝ ተተክሏል፣

➧ በ2012 ለመትከል የታቀደው 120 ሺህ ችግኝ ሲሆን ከዚህም ውስጥ፦
የፍራፍሬ ችግኝ 20,000
የደን ችግኝ 130,000
በድምሩ 150,000 ችግኝ ተተክሏል፣

➧ በ2013 ለመትከል የታቀደው 500,000 ችግኝ ሲሆን፣
የፍራፍሬ ችግኝ 200,000፣
የደን ችግኝ 100,000፣
በድምሩ 300,000 ችግኝ ተተክሏል፣

➧ በ2014 ለመትከል የታቀደው ዕቅድ 550,000 ችግኝ ሲሆን፣
የፍራፍሬ ችግኝ 300,000፣
የደን ችግኝ 250,000፣
በድምሩ 550,000 ችግኝ በዩኒቨርሲቲው ካምፓሶች እና በአካባቢው ተተክሏል።( ለተለያዩ መንግስታዊና መንግስታዊ ላልሆኑ ተቋማት ተደራሽ ሆኗል)

➧ በ2015 ሁለተኛው ምዕራፍ 5ኛ ዙር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርር 330,000 የአቦካዶ ችግኝ ለመትከል እንዲሁም ለተለያዩ መንግስታዊና መንግስታዊ ላልሆኑ ተቋማት ተደራሽ ለማድረግ መታቀዱን ከዩኒቨርሲቲው አረንጓዴ አሻራ ልማት ዳይሬክቶሬት የተገኘ መረጃ ያመላክታል።

➭ «ዕውቀትን በተግባር!!»

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት!!

➤ ግንቦት 29/2015 ዓ.ም

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት

ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/profile.php?id=100063820159424

ቴሌግራም፡ https://t.me/WolaitaSUniversity

ዩቲዩብ፡ https://www.youtube.com/channel/UC6VukdZbl5iVgZGXG8BkMdw/videos

ዌብሳይት፡ http://www.wsu.edu.et/

ትዊተር፡ https://twitter.com/WSodoUniversity?t=w_VzjrOWj3D3Mc8BKlQFXA&s=09

ሊንክዲን፡ https://www.linkedin.com/company/wolaita-sodo-university/

ኢንስታግራም፡ https://instagram.com/wolaita_sodo_university?igshid=YmMyMTA2M2Y=

አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን
129 viewsedited  16:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-06 19:42:36
126 views16:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-06 17:46:52 #ጉብኝት-2(የሆስፒታሊቲ እና ቱሪዝም ማሰልጠኛ ማዕከል)

ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ከኢ.ፌ.ዴ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር «ውጤታማ ተግባቦት ለኢትዮጵያ ልዕልና» በሚል ርዕሰ ጉዳይ ያዘጋጀውን ስልጠና ለመሳተፍ ከ 47 የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች እና ተጠሪ ተቋማት የመጡ የህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዘርፍ የሥራ ኃላፊዎች ግንባታው የተጠናቀቀውን «የሆስፒታሊቲ እና ቱሪዝም ማሰልጠኛ ማዕከል»ጎብኝተዋል።

ባለ ሰባት ሰንሰለታማ ተራራ በሆነው እና በአስደማሚው ዳሞታ ተራራ ግርጌ የሚገኘው የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታሊቲ እና ቱሪዝም ማሰልጠኛ ማዕከል ግንባታው አለም አቀፍ የጥራት መመዘኛ መስፈርትን በጠበቀ መልኩ የተገነባ መሆኑ ለጎብኚዎች ተብራርቷል።

ባለ አራት ኮከብ ሆቴሎች የሚሰጡትን የተሟላና ብቁ አገልግሎት ለመስጠት እንዲሁም በሆቴልና ቱሪዝም መስክ ትምህርት እና ስልጠና በመስጠት ብቁ የሰው ኃይል ለማፍራት ራዕይ በመሰነቅ የተመሰረተ ማዕከል መሆኑ ጭምር በጉብኝቱ ወቅት ተመላክቷል።

ለጎብኝዎች በተደረገ ገለጻ፦ ማዕከሉ 150 መኝታ ቤቶች፥ የተለያየ መጠን ያላቸውን በርካታ የተማሪዎች መማሪያ ክፍሎች፣ መመገቢያና መሰብሰቢያ አዳራሾች፣ ግብይት የሚሰጡ ሱቆችን፣ ማሳጅ ቤቶችን፣ ክሊኒክ፣ ላውንደሪ፣ ፕሌይ ስቴሽን እና ልዩ ልዩ የመዝናኛ ስፍራዎችን ያካተተ መሆኑም ተጠቁሟል።

በሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍ ብቁ የሰው ኃይል አስተምሮና አሰልጥኖ ከማፍራት ባሻገር የማዕከሉ መቋቋም ለአካባቢው የቱሪዝም እድገት አዎንታዊ ፋይዳ እንደሚኖረው ጭምር ለጎብኚዎቹ ተብራርቷል።

ዩኒቨርሲቲው ከያዘው የትኩረት መስኮች አንዱ የቱሪዝምና ሆስፒታሊቲ ልማት በመሆኑ የማዕከሉ መቋቋም በዘርፉ ከአጭር ጊዜ ስልጠና እስከ ፒ.ኤች.ዲ ደረጃ ትምህርትና ስልጠና የሚሰጥ መሆኑም ተገልጿል።

በሆቴል ልማት ዘርፍ ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ ባለ አራት ኮከብ ሆቴሎች እኩል አገልግሎት የሚሰጥ ከመሆኑ ባሻገር ማዕከሉ ያለበት አካባቢ ልዩ የመስዕብ ሥፍራ በመሆኑ ዘርፈ ብዙ የመዝናኛ አገልግሎት መስጠት የሚችል መሆኑም ተጠቁሟል።

ማዕከሉ ወደ ስራ ሲገባ ለበርካታ የአካባቢው ወጣቶች ምቹ የስራ እድል እንደሚፈጥር፤ ለከተማው ዕድገት የራሱ አዎንታዊ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው እንዲሁም የውስጥ ገቢ አቅምን በማሳደግ ዩኒቨርሲቲው "ራስ ገዝ" ለመሆን የሚያደርገውን ጉዞ የበለጠ የሚያጠናክር መሆኑም ለጉብኝቱ ተሳታፊዎች ተመላክቷል።

በወላይታ ሶዶ ከተማ ኮካቴ ማራ ጫሬ ቀበሌ የተገነባው ባለ አምስት ወለል (G+5) የሆስፒታሊቲ እና ቱሪዝም ማሰልጠኛ ማዕከል ውስጣዊ የሕንጻ ውቅር (ኢንቴርየር ዲዛይን) የወላይታ ብሔርን ባሕላዊ ዕሴት በጠበቀ አግባብ የሚዋቀር መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፤ ማዕከሉ ለስራ አስፈላጊ የሆኑ ቁሳቁሶችን በማሟላት አገልግሎት መስጠት የሚጀምር መሆኑ ለጎብኚዎች ተብራርቷል።

➭ «ዕውቀትን በተግባር!!»

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት!!

➤ ግንቦት 29/2015 ዓ.ም

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት

ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/profile.php?id=100063820159424

ቴሌግራም፡ https://t.me/WolaitaSUniversity

ዩቲዩብ፡ https://www.youtube.com/channel/UC6VukdZbl5iVgZGXG8BkMdw/videos

ዌብሳይት፡ http://www.wsu.edu.et/

ትዊተር፡ https://twitter.com/WSodoUniversity?t=w_VzjrOWj3D3Mc8BKlQFXA&s=09

ሊንክዲን፡ https://www.linkedin.com/company/wolaita-sodo-university/

ኢንስታግራም፡ https://instagram.com/wolaita_sodo_university?igshid=YmMyMTA2M2Y=

አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን
482 views14:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-06 17:46:48
428 views14:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-06 17:38:59 #ጉብኝት-1(የወላይታ ባሕል ሙዚየም)

ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ከኢ.ፌ.ዴ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር «ውጤታማ ተግባቦት ለኢትዮጵያ ልዕልና» በሚል ርዕሰ ጉዳይ ያዘጋጀውን ስልጠና ለመሳተፍ ከ 47 የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች እና ተጠሪ ተቋማት የመጡ የህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዘርፍ የሥራ ኃላፊዎች የወላይታ ባሕል ሙዚየም ጎብኝተዋል።

የወላይታን ብሔር ባሕላዊና ታሪካዊ ቅርሶችን በተደራጀ አግባብ አካቶ የያዘው ሙዚየሙ በባህል ልማት መስክ ትልቅ ሀብት መሆኑን በመግለጽ በጉብኝቱ ደስተኛ መሆናቸውን አሳውቀዋል። ሌሎች አካላትም በትውልድ ቅብብሎሽ ተጠብቆ የቆየውን ይህን የትውልድ አሻራ ቅርስ አሰባስቦ የያዘውን ሙዚየም እንዲጎበኙ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ስለ ሙዚየሙ እውነታዎች በጥቂቱ

➧ «ቅርስ ያለው ታሪክ አለው» በሚል መርህ በ2012 ዓ.ም በዩኒቨርሲቲው አስተዳደር ተመሠረተ።

➧ በዩኒቨርሲቲው ዋናው ግቢ–ገንዳባ ካምፓስ የሚገኝ ሲሆን፤ በሀገር በቀል ዕውቀት ተቋም ዳይሬክቶሬት ይተዳደራል።

➧ ውጫዊ እና ውስጣዊ አወቃቀሩ በወላይታ ብሔር ባህላዊ የጎጆ ቤት ቅርጽ የተሰራ ሲሆን፤ የብሔሩን ታሪክና ባህል እንዲገልጽ ተደርጎ የተደራጀ ነው።

➧ ከ300 የሚበልጡ የተለያዩ ባህላዊ እና ታሪካዊ ይዘት ያላቸው ቅርሶችን አደራጅቶ ይዟል።

➧ ቅርሶቹ ለተግባራዊ መማር ማስተማር፥ ለጥናትና ምርምር፣ ለቴክኖሎጂ ሽግግርና ስርጸት፣ ለስልጠና እንዲሁም ቀጣይነት ላለው የቱሪዝም ዕድገት ጉልህ ፋይዳ አላቸው።

➧ የወላይታን ቋንቋ፣ ባህል፣ ታሪክና ቅርስ መጠበቅ፣ ማሳደግና ለቀጣዩ ትውልድ ማስተላለፍ የሙዚየሙ ተቀዳሚ ዓላማ ነው።

➧ በቋንቋው፣ በባህሉ፣ በታሪኩ እና በቅርሱ የሚኮራ እና ማንነቱን የሚገልጽ ትውልድ ለመቅረጽ ሙዚየሙ የላቀ ፋይዳ አለው።

➧ የአካባቢውን ማህበረሰብ ጨምሮ ሙዚየሙን ከ40 ሺህ የሚበልጡ የአገር ውስጥ እና የውጭ ሀገር ዜጎች ጎብኝተውታል።

➧ ሙዚየሙ በሚገኝበት ስፍራ የተለያዩ የወላይታ ባህላዊ የቅመማ ቅመም ዝርያዎችን (ናቲራ፣ ጣሎቲያ፣ አጉፒያ፣ ሞርዳሊያ፣ ደቡዋ፣ ከፑዋ፣ ጉጨቻ...) አካቶ ይዟል።

➧ ሙዚየሙን በተለያዩ ቅርሶች የበለጠ ለማበልፀግ ተጨማሪ ባሕላዊ እና ታሪካዊ ቅርሶችን የማሰባሰብና የማደራጀት ተግባር አፅንዖት ተሰጥቶት እየተሰራ ነው።

➧ ሙዚየሙ ዘወትር ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ከጧቱ 2:00 እስከ ምሽቱ 1:00 ድረስ እንዲሁም ዕለተ እሁድ ከቀኑ 8:00 እስከ 12:00 ለጉብኝት ክፍት ነው።

➧ ይምጡ ይጎብኙ–ብዙ አትርፈው፤ ተደስተው ይመለሳሉ!!

➭ «ዕውቀትን በተግባር!!»

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት!!

➤ ግንቦት 29/2015 ዓ.ም

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት

ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/profile.php?id=100063820159424

ቴሌግራም፡ https://t.me/WolaitaSUniversity

ዩቲዩብ፡ https://www.youtube.com/channel/UC6VukdZbl5iVgZGXG8BkMdw/videos

ዌብሳይት፡ http://www.wsu.edu.et/

ትዊተር፡ https://twitter.com/WSodoUniversity?t=w_VzjrOWj3D3Mc8BKlQFXA&s=09

ሊንክዲን፡ https://www.linkedin.com/company/wolaita-sodo-university/

ኢንስታግራም፡ https://instagram.com/wolaita_sodo_university?igshid=YmMyMTA2M2Y=

አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን
437 views14:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-06 17:38:24
410 views14:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-18 18:09:35
5.9K views15:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ