Get Mystery Box with random crypto!

Wolaita Sodo University

የቴሌግራም ቻናል አርማ wolaitasuniversity — Wolaita Sodo University W
የቴሌግራም ቻናል አርማ wolaitasuniversity — Wolaita Sodo University
የሰርጥ አድራሻ: @wolaitasuniversity
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 18.46K
የሰርጥ መግለጫ

This is the official telegram channel of Wolaita Sodo University
Our Official Website :
http://www.wsu.edu.et/
Our Official Facebook page :
https://m.facebook.com/Wolaita-Sodo-University-246568056057804

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2023-04-23 20:23:09 «ዩኒቨርሲቲያችንን እናጽዳ፤ በፍቅር እንሻገር» በሚል መሪ ቃል የጽዳት ዘመቻ ተካሄደ።
__

በዩኒቨርሲቲው
ተማሪዎች ሕብረት አስተባባሪነት «ዩኒቨርሲቲያችንን እናጽዳ፤ በፍቅር እንሻገር» በሚል መሪ ቃል በዛሬው ዕለት በዋናው ግቢ የጽዳት ዘመቻ ተካሂዷል።

በዩኒቨርሲቲው ገንዳባ ካምፓስ የተካሄደው የጽዳት ዘመቻ አረንጓዴ፣ ጽዱ፣ ውብ፣ ማራኪ እና ለመማር ማስተማር ተግባር ምቹ የሆነ ተቋም ለመፍጠር የሚደረገውን ሁለንተናዊ ጥረት ለመደገፍ የተካሄደ መሆኑን የተማሪዎች ሕብረት ፕሬዝዳንት የሆነው ተማሪ ፍሬው ተክሌ አሳውቋል።

በጽዳት ዘመቻው የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ሕብረት አመራሮች እና በርካታ ተማሪዎች የተሳተፉ መሆኑን የሕብረቱ ፕሬዝዳንት ገልጾ፤ ቆሻሻ የመጥረግና የማስወገድ ተግባር በስፋት መካሄዱንም አመላክቷል።

ለውጤታማ የመማር ማስተማር ሂደት መጎልበት የጽዳትና ውበት ስራ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ተማሪ ፍሬው ተክሌ ገልጾ ፤ «ዩኒቨርሲቲያችንን እናጽዳ፤ በፍቅር እንሻገር» በሚል መሪ ቃል የተካሄደው የጽዳት ዘመቻም፡ ቆሻሻን ከማጽዳት ባሻገር “አስተሳሰብን ከክፋት በማጽዳት በፍቅር እና በይቅርታ መሻገርን” ዓላማው ያደረገ መሆኑን አሳውቋል።

ተማሪዎች ሕብረ ብሔራዊ አንድነታቸውን አጠናክረው በመተሳስብና በፍቅር ትምህርታቸውን መከታተል እና ብሩህ ተስፋ አንግበው ወደፊት ብቻ መሻገር ይጠበቅባቸዋል ያለው የሕብረቱ ፕሬዝዳንት፤ ህሊናችንን ከክፉ አስተሳሰቦች እንዲሁም የምንኖርበትን አካባቢ ደግሞ ከቆሻሻ እናጽዳ በማለት መልዕክት አስተላልፏል።

የጽዳት ዘመቻው ዛሬ ተጀምሮ የሚቆም ሳይሆን ተማሪዎችን በማሳተፍ ቢያንስ በወር አንድ ጊዜ በቀጣይነት የሚከናወን መሆኑ ተመላክቷል።

ዕውቀትን በተግባር!!

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት!!

https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid02PDGigBxnkwLAGW9oB6XY1tfQnYCPdKJH28rPVSvURhUCaCfXzPBHjPDb7DC9DAqPl&id=100063820159424&mibextid=Nif5oz
950 viewsedited  17:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-23 17:50:41
1.3K views14:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-23 17:50:23 የዩኒቨርሲቲው “የሆስፒታሊቲ እና ቱሪዝም ማሰልጠኛ ማዕከል” ሕንጻ ግንባታ ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁ ተገለጸ።

ማዕከሉ በቅርቡ አስፈላጊ የሆኑ ቁሳቁሶችን በማሟላት አገልግሎት መስጠት የሚጀምር መሆኑም ተመላክቷል።
_______________

በወላይታ ሶዶ ከተማ ኮካቴ ማራ ጫሬ ቀበሌ የተገነባው ባለ አምስት ወለል (G+5) የሆስፒታሊቲና ቱሪዝም ማሰልጠኛ ማዕከል ሕንጻ ግንባታ ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁን የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር አሳውቋል።

የሕንጻው ግንባታ አለም አቀፍ የጥራት ደረጃን በጠበቀ መልኩ የተገነባ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፤ ውስጣዊ አደረጃጀቱ 150 መኝታ ቤቶችን፤ በርካታ የተማሪዎች መማሪያ ክፍሎችን፣ መመገቢያ እና መሰብሰቢያ አዳራሾችን፣ የግብይት አገልግሎት የሚሰጡ ሱቆችን፣ ማሳጅ ቤቶችን፣ ክሊኒክ፣ ላውንደሪ፣ ፕሌይ ስቴሽን እና ልዩ ልዩ የመዝናኛ ስፍራዎችን ያካተተ መሆኑ ተጠቁሟል።

ማዕከሉ በሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍ ብቁ የሰው ኃይል አስተምሮና አሰልጥኖ ከማፍራት ባሻገር ለአካባቢው የቱሪዝም እድገት ጉልህ ሚና እንደሚኖረው የተገለጸ ሲሆን፤ በሆቴል ልማት ዘርፍ ኢትዮጵያ ውስጥ ካሉ ባለ አራት ኮከብ ሆቴሎች እኩል አገልግሎት የሚሰጥ እንደሆነም ተመላክቷል።

ማዕከሉ በተሟላ መልኩ ወደ ስራ ሲገባ ለበርካታ የአካባቢው ወጣቶች ምቹ የስራ እድል እንደሚፈጥር፤ ለከተማው ዕድገት የራሱ አዎንታዊ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው እንዲሁም የውስጥ ገቢን ከማሳደግ ረገድ ከፍተኛ ፋይዳ ይኖረዋል ነው የተባለው።

የሕንጻው ውስጣዊ ውቅር (ኢንቴርየር ዲዛይን) የወላይታን ብሔር ባሕላዊ ዕሴት በጠበቀ መልኩ የሚዋቀር መሆኑን እና ማዕከሉ ለሥራ አስፈላጊ የሆኑ ቁሳቁሶችን በማሟላት በቅርቡ የሆቴል እና የሆስፒታሊቲ አገልግሎት መስጠት የሚጀምር መሆኑንም የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር አሳውቋል።

ዕውቀትን በተግባር!!

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት!!
1.3K viewsedited  14:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-22 19:46:40
1.2K views16:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-22 19:45:04 ዩኒቨርሲቲው በክረምት ወራት ለሚካሄደው 5ኛ ዙር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከ 330 ሺሕ የሚበልጥ የአቮካዶ ችግኝ ዝርያ ለተከላ ማዘጋጀቱን አስታወቀ።

ዩኒቨርሲቲው ባለፉት አራት ዓመታት ባካሄደው የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ ዘመቻ ከ 1 ሚሊየን የሚበልጥ የደን እና የፍራፍሬ ችግኞችን አዘጋጅቶ መትከሉም ተጠቁሟል።
___

ታሪካዊው የአረንጓዴ አሻራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር በተካሄደበት ሐምሌ 22/2011 ዓ.ም የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) በዩኒቨርሲቲው ተገኝተው አሻራቸውን ማኖራቸውን ተከትሎ የአረንጓዴ አሻራ ልማት ተጠናክሮ የቀጠለ መሆኑን ነው የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ታከለ ታደሰ የገለጹት።

ዩኒቨርሲቲው ባለፉት አራት ዓመታት የደንና የተለያዩ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸውን የፍራፍሬ ዝርያዎች በማፍላት ለተከላ ማዘጋጀቱን፥ ሕብረተሰቡን በማሳተፍ በሶስቱም ካምፓሶቹ መትከሉን እና ለአካባቢው ማሕበረሰብም በመቶ ሺህዎች የሚቆጠሩ ችግኞችን ተደራሽ ማድረጉን ፕሬዝዳንቱ አሳውቀዋል።

ባለፉት አራት ተከታታይ ዓመታት በሶስቱም ካምፓሶች፣ ዩኒቨርሲቲው በሚገኝበት የተለያያዩ አካባቢዎች እንዲሁም በሶዶ ዙሪያ ወረዳ ቡጌ ዋንቼ ቀበሌ እየለማ ባለው የደን ይዞታ በመቶ ሺህዎች በሚቆጠር ሄ/ር መሬት በደን እና በፍራፍሬ የችግኝ ዝርያዎች የተሸፈነ መሆኑንም ፕሬዝዳንቱ ጠቁመዋል።

ፕሬዝዳንቱ አክለውም፤ ዩኒቨርሲቲው የራሱን ችግኝ ጣቢያ በማቋቋም ባለፉት አራት ዓመታት 1,080,000 የደን እና የተለያዩ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸውን የአቮካዶ፣ ማንጎ እና ፓፓያ ምርጥ ዝርያዎችን በማፍላት ለተከላ ማብቃቱን ነው የተናገሩት።

ዩኒቨርሲቲው በ2014 ዓ.ም በተካሄደ 4ኛ ዙር የአረንጓዴ አሻራ ዘመቻ ብቻ 550,000 የደንና የፍራፍሬ ችግኞችን በማፍላት ለተከላ ማብቃቱን ፕ/ር ታከለ ተናግረው፤ በዓመቱ ከተተከሉት ውስጥ 300,000 የፍራፍሬ እንዲሁም 250,000 የደን እንደሆነም አሳውቀዋል።

«ዐሻራችን ለትውልዳችን» በሚል መሪ ቃል በዩኒቨርሲቲው በተካሄደ 4ኛ ዙር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በአንድ ጀምበር ከ15 ሺህ የሚበልጥ የአቮካዶ እና የማንጎ ችግኝ ዝርያ መተከሉን ፕሬዝዳንቱ ገልጸው፤ ይህም በሀገር ደረጃ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በፍራፍሬ ችግኝ ላይ የተመሰረተ የ 30-40-30 ፕሮጀክት ጅምር ተግባር መሆኑን አብራርተዋል።

የአረንጓዴ አሻራ ልማት የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ እና አረንጓዴ ኢኮኖሚን ከመግንባት ረገድ ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ፕ/ር ታከለ የተናገሩ ሲሆን፤ ዩኒቨርሲቲው የሚበሉ የፍራፍሬ ዝርያዎች ላይ በማተኮር በቀጣይ ክረምት ለሚካሄደው 5ኛ ዙር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር 330 ሺሕ የአቮካዶ ፍሬ እያፈላ ይገኛል ብለዋል።

በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲው የአረንጓዴ አሻራ ልማት የችግኝ የፅድቀት መጠን በ2011 ዓ.ም 85.98 በመቶ፣ በ2012 ዓ.ም 88.50 በመቶ፣ በ2013 ዓ.ም 88.24 በመቶ እና በ2014 ዓ.ም ደግሞ 90 በመቶ መሆኑን ከዩኒቨርሲቲው አረንጓዴ አሻራ ፕሮጀክት ዳይሬክቶሬት የተገኘ መረጃ ያመላክታል።

ዕውቀትን በተግባር!!

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
1.2K views16:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-21 17:54:21
1.8K views14:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-21 17:53:49 የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች 1444ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል በድምቀት አከበሩ። (መጋቢት 13/2015 ዓ.ም)

በዩኒቨርሲቲው የእስልምና ሐይማኖት ተከታይ ተማሪዎች 1444ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል በድምቀት አክብረዋል።
________

በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ የሚገኙ የእስልምና ሐይማኖት ተከታይ መደበኛ ተማሪዎች ከዩንቨርሲቲው ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን የኢድ አልፈጥር በዓል በድምቀት አክብረዋል።

ኢድ አልፈጥርን አስመልክቶ በተዘጋጀው ክብረ በዓል የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ታከለ ታደሰ፣ የአስተዳደርና ተማሪዎች አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር አብርሃም ቦሻ፣ የተማሪዎች አገልግሎት ዳይሬክተር መምህር ተመስገን ማርቆስ፣ የተማሪዎች አገልግሎት ምክትል ዘርፍ ኃላፊ አቶ ዘገየ ገብረመድህን፣ የተማሪዎች ሕብረት አመራሮች እንዲሁም ሌሎች የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

ፕ/ር ታከለ በዩኒቨርሲቲው የእስልምና ሐይማኖት ተከታይ የሆኑ ተማሪዎችን እንኳን ለ1444ኛዉ የኢድ አልፈጥር በዓል በሠላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን በማለት በዓሉ የሰላም፣ የደስታ፣ የፍቅር፣ የአብሮነት፣ የአንድነት እና የመተሳሰብ እንዲሆንላቸው መልካም ምኞታቸውንም ገልጸዋል፡፡

Eid Mubarak!

Wishing everybody celebrating a happy and blessed #EidUlFitr.

➭ «ዕውቀትን በተግባር!!»

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት!!

➤ ሚያዝያ 8/2015 ዓ.ም

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት

ፌስቡክWolaita Sodo University4/

ቴሌግራም፡https://t.me/WolaitaSUniversity

ዩቲዩብ፡ https://www.youtube.com/channel/UC6VukdZbl5iVgZGXG8BkMdw/videos

ዌብሳይት፡ http://www.wsu.edu.et/

ትዊተር፡ https://twitter.com/WSodoUniversity?t=w_VzjrOWj3D3Mc8BKlQFXA&s=09

ሊንክዲን፡ https://www.linkedin.com/company/wolaita-sodo-university/

ኢንስታግራም፡ https://instagram.com/wolaita_sodo_university?igshid=YmMyMTA2M2Y=

አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን
1.8K views14:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 19:23:06 ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1444 ኛዉ የዒድ አልፈጥር በአል በሰላም አደረሳችሁ!! አደረሰን!!


የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ፕ/ር ታከለ ታደሰ 1444 ኛዉን የኢድ አልፈጥር በዓል በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

ፕሬዝዳንቱ በኢትዮጵያ እና በመላው ዓለም ለሚገኙ የእስልምና ሐይማኖት ተከታዮች በሙሉ በተለይ በዩኒቨርሲቲው የእምነቱ ተከታይ ለሆኑ ሠራተኞች እና ተማሪዎች ለ1444ኛው ዓመተ ሒጅራ የኢድ አል ፈጥር በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የረመዳን ወር በእምነቱ ተከታዮች ዘንድ ከሌሎች ወሮች በተለየ መልኩ የሚወደድ የቁርአን፣ የሶላት፣ የአዝካር፣ የሰደቃ፣ የዱዓ እና መልካም ተግባራት የሚፈፀሙበት ወር መሆኑን ፕ/ር ታከለ ጠቁመው፤ የዚህ ቅዱስ ወር ፍፃሜ ማብሰሪያ የሆነው የኢድ አልፈጥር ወይም ረመዳን ጾም ፍቺ በዓል ለሕዝበ ሙስሊሙ የሰላም፣ የጤና፣ የደስታ፣ የፍቅር እና የመረዳዳት እንዲሆን ልባዊ ምኞታቸውን ገልጸዋል።

የረመዳን ጾም መስዕዋትነትን፣ በትዕግስት መሻገርን፣ ለመልካም ነገሮች ሁሉ መነሳሳትን፣ ፈተናን በትህትና ማለፍን፣ ሐይማኖታዊ ሥነ ምግባርን በመጠበቅ በፍጹም መታዘዝ የሚፆምበት ወቅት መሆኑን የገለጹት ፕ/ር ታከለ፤ ህዝበ ሙስሊሙ በዓሉን ሲያከብር አብሮነትን በተግባር በማሳየት፣ እርስ በእርስ በመተጋገዝ፣ በመተዛዘንና በመደጋገፍ፣ ወንድማማችነትን በማጠናከር፣ በህዝቦች መካከል አብሮ የኖረውን የመቻቻል፣ የመፈቃቀድ እንዲሁም የአንድነት እሴትን በማጎልበት መልካም ስራዎችን በመስራት ተምሳሌታዊ በሆነ አግባብ ማክበር ተገቢ ነው ብለዋል።

የኢድ አልፈጥር/ ረመዳን በዓል የፆም ፍቺ እና ለዐቅመ ደካሞች የሚደረግ እዝነትን አስተሳስሮ የያዘ ልዩ በዓል መሆኑን ፕሬዝዳንቱ ተናግረው፤ ህዝበ ሙስሊሙ በዓሉን ሲያከብር የተቸገሩ ወገኖችን በማሰብ፣ በመርዳት እና በመተዛዘን መሆን እንዳለበትም ፕሬዝዳንቱ አሳስበዋል።

በመጨረሻም፤ ፕ/ር ታከለ መላዉን የእስልምና ሐይማኖት ተከታዮች በድጋሚ እንኳን ለ1444ኛዉ የኢድ አልፈጥር በዓል በሠላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን በማለት በዓሉ የሰላም፣ የደስታ፣ የፍቅር፣ የአብሮነት፣ የአንድነት እና የመተሳሰብ እንዲሆንላቸው መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡

#ዒድ_ሙባረክ!!

መልካም በዓል!

3.8K views16:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 19:21:32
3.3K views16:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 19:20:29 “መውጫ ፈተናን በተመለከተ በየትምህርት ክፍሉ የተገኙ ምርጥ የተባሉ ልምዶችንና ተሞክሮዎችን በመቀመር ማስፋትና ጥቅም ላይ ማዋል ተገቢ ነው።”– ፕ/ር ታከለ ታደሰ (የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት)

በዩኒቨርሲቲው «የመውጫ ፈተና ቅድመ ዝግጅት ተሞክሮዎች፣ ያጋጠሙ ችግሮች እና ቀጣይ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች» በሚል ርዕሰ ጉዳይ ላይ ትኩረቱን ያደረገ ውይይት ተካሄዷል።
____

በዩኒቨርሲቲው በ2015 ዓ.ም ለሚሰጠው የመውጫ ፈተና ትግበራ የሚደረገው ዝግጅት ተጠናክሮ እንዲቀጥልና ተገቢው ድጋፋዊ ክትትል እንዲደረግ ሥራ አመራር ቦርድ አቅጣጫ አስቀምጧል።

በዚሁ መሰረት የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር የትምህርት ዘርፍ የሥራ ኃላፊዎችን በማሳተፍ «የመውጫ ፈተና ቅድመ ዝግጅት ተሞክሮዎች፣ ያጋጠሙ ችግሮች እና ቀጣይ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች» በሚል ርዕስ ጉዳይ ላይ ትኩረቱን ያደረገ የምክክር መድረክ አካሂዷል።

በመድረኩ የኮሌጅ እና ትምህርት ቤት ዲኖች፣ የአካዳሚክ ዘርፍ ምክትል ዲኖች እንዲሁም የሁሉም ትምህርት ክፍል የሥራ ኃላፊዎች የተሳተፉ ሲሆን፤ የየትምህርት ክፍል እስካሁን በተከናወኑ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ላይ ያላቸውን ተሞክሮዎችን እና ያጋጠማቸውን ተግዳሮቶችን በመድረኩ አሳውቀዋል።

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ፕ/ር ታከለ ታደሰ በመድረኩ እንደገለጹት፡ መውጫ ፈተናን በተመለከተ በየትምህርት ክፍሉ የተገኙ ምርጥ የተባሉ ልምዶችንና ተሞክሮዎችን በመቀመር ማስፋትና ጥቅም ላይ ማዋል ተገቢ መሆኑን አመላክተዋል።

በቅድመ ዝግጅት ምዕራፍ በተከናወኑ ሥራዎች ያጋጠሙ ውስንነቶችን ሁሉ በመለየት ተገቢውን ድጋፋዊ ክትትል ማድረግ፥ ችግሮችን ማረምና ፈጣን ምላሽ መስጠት እንዲሁም ቀሪ ስራዎች ላይ ትኩረት በማድረግ ለመውጫ ፈተናው ተገቢውን ዝግጅት ማድረግ ከሁሉም የዘርፉ የሥራ ኃላፊዎች ይጠበቃል ሲሉ ፕሬዝዳንቱ አሳስበዋል።

በመድረኩ ለ62 የትምህርት ክፍሎች የሚሆን ከ300 የሚበልጡ የስልጠና ማኑዋሎች መዘጋጀቱ፤ ማኑዋሎች በዩኒቨርሲቲው ዌብ ሳይት እና በቴሌግራም ቻናሎች ላይ ተጭኖ ተደራሽ መደረጉ፤ በተዘጋጁት ማኑዋሎች ላይ ስልጠና መሰጠቱ፤ ሞዴል ፈተናዎችን አዘጋጅቶ ለተማሪዎች በመስጠት የስነ ልቦና ዝግጅት ማድረጋቸው እንዲሁም የክትትል፥ ድጋፍና አመራር የመስጠት ተግባር ተጠናክሮ መቀጠሉ በጥንካሬ ተገምግሟል።

በሁሉም የትምህርት መስኮች እንዲሁም መርሀ ግብሮች ለሚሰጠው የመውጫ ፈተና ዩኒቨርሲቲው ተገቢውን ቅድመ ዝግጅት እያደረገ መሆኑ በመድረኩ በጥልቀት የተፈተሸ ሲሆን፤ በሂደቱ ላጋጠሙ አበይት ችግሮች እና ትኩረት ለሚሹ ጉዳዮች የመፍትሄ አቅጣጫ ተቀምጦ የምክክር መድረኩ ተጠናቋል።

በመጪው ሀምሌ ወር የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና ከሚወስዱ 3 ሺህ 623 የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች መካከል 2 ሺሕ 221 ወንዶች ሲሆኑ ቀሪ 1 ሺሕ 410 ሴቶች ናቸው።

ከአጠቃላይ ተፈታኞች መካከል 2 ሺሕ 56 የመደበኛ እንዲሁም 1 ሺሕ 567 ያህሉ ደግሞ የተከታታይ ትምህርት መርሃ ግብር ተማሪዎች እንደሆኑም ተመላክቷል።

እውቀትን በተግባር!!

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
1.4K viewsedited  16:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ