Get Mystery Box with random crypto!

Wolaita Sodo University

የቴሌግራም ቻናል አርማ wolaitasuniversity — Wolaita Sodo University W
የቴሌግራም ቻናል አርማ wolaitasuniversity — Wolaita Sodo University
የሰርጥ አድራሻ: @wolaitasuniversity
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 18.46K
የሰርጥ መግለጫ

This is the official telegram channel of Wolaita Sodo University
Our Official Website :
http://www.wsu.edu.et/
Our Official Facebook page :
https://m.facebook.com/Wolaita-Sodo-University-246568056057804

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2023-04-26 17:42:24 የዕጩ ዶ/ር ከበደ ካሳ ጋዳቦ የፒ ኤች ዲ (PhD) መመረቂያ ጽሑፍ ተገመገመ!!
═════════════════════════════
በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ማሕበራዊ ሳይንስና ስነ ሰብ ኮሌጅ፤ በእንግሊዝኛ ቋንቋ እና ሥነጽሑፍ ትምህርት ክፍል “በእንግሊዝኛ ቋንቋ የማስተማር” የትምህርት ፕሮግራም/‹‹Teaching English Language (ELT)›› ላለፉት 6 ዓመታት የ3ኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩት ዕጩ ዶ/ር ከበደ ካሳ ጋዳቦ የጥናትና ምርምር ሥራቸው ሚያዚያ 18/ 2015 ዓ.ም የውስጥ እና የውጪ ገምጋሚዎች በተገኙበት ተገምግሟል፡፡

ዕጩ ዶ/ር ከበደ ካሳ የፒ ኤች ዲ (PhD) መመረቂያ ጽሑፋቸውን ‹‹Effects of Content-Based Language Teaching on Student's English Vocabulary Knowledge and Their Attitudes Towards The Lesson›› በሚል ርዕስ የውስጥ እና የውጪ ገምጋሚዎች በተገኙበት አቅርበዋል።

ዕጩ ዶ/ር ከበደ ካሳ ያቀረቡት የፒ ኤች ዲ (PhD) መመረቂያ ጥናታዊ የምርምር ጽሑፋቸው አስፈላጊውን መስፈርት ማሟላቱን፥ በግምገማው ሂደት በበጣም ጥሩ (Very Good) ውጤት በማግኘት በአማካሪ ቦርዱ ተቀባይነት ያገኘ መሆኑን በማህበራዊ ሳይንስና ስነሰብ ኮሌጅ የእንግሊዝኛ ቋንቋና ሥነጽሑፍ ትምህርት ክፍል ኃላፊ የሆኑት ረዳት ፕ/ር ተስፋዬ ቡቼ አሳውቀዋል።

የእንግሊዝኛ ቋንቋና ሥነጽሑፍ ትምህርት ክፍል የሶስተኛ ድግሪ የጥናትና ምርምር ሥራ በማቅረብ ሲያስገመግም ይህ ለሶስተኛ ጊዜ መሆኑን ኃላፊ ገልጸው፤ ከዚህ ቀደም ትምህርት ክፍሉ 6 ዶክተሮችን (PhD in ELT) ማስመረቁን ጠቁመዋል።

ዕጩ ዶ/ር ከበደ ካሳ ጋዳቦ የዶክትሬት ዲግሪያቸውን (PhD in ELT) በዩኒቨርሲቲው ሴኔት ከጸደቀ በኋላ የሚያገኙ መሆኑን ረዳት ፕ/ር ተስፋዬ ተናግረው፤ በግምገማ በመርሃ-ግብሩ ላይ የውስጥና የውጪ ገምጋሚዎችን ጨምሮ የዩኒቨርሲቲው ተመራማሪዎች፣ የኮሌጅ ዲኖች፣ የትምህርት ክፍል ኃላፊዎች፣ የዘርፉ መምህራን እና የድኅረ ምረቃ ተማሪዎች ተገኝተዋል ሲሉ አሳውቀዋል።

በ2010 ዓ/ም የ3ኛ ዲግሪ ትምህርት ዕድል በማግኘት ትምህርታቸውን በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የጀመሩት ዕጩ ዶ/ር ከበደ ካሳ ጋዳቦ የመጀመሪያ ድግሪያቸውን ከባህርዳር ዩኒቨርሲቲ፣ ሁለተኛ ድግሪያቸውን ከሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተቀበሉ ሲሆን፤ ከጥቅምት ወር 2005 ዓ.ም ጀምሮ በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ማሕበራዊ ሳይንስ እና ስነ ሰብ ኮሌጅ በእንግሊዘኛ ቋንቋ ትምህርት ክፍል መምህር ሆነው እያገለገሉ እንደሚገኙ ከግለ ማህደራቸው የተገኘ መረጃ ያመላክታል።

#Congratulations

➭ «ዕውቀትን በተግባር!!»

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት!!

➤ ሚያዝያ 18/2015 ዓ.ም

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት

ፌስቡክWolaita Sodo University4/

ቴሌግራም፡https://t.me/WolaitaSUniversity

ዩቲዩብ፡ https://www.youtube.com/channel/UC6VukdZbl5iVgZGXG8BkMdw/videos

ዌብሳይት፡ http://www.wsu.edu.et/

ትዊተር፡ https://twitter.com/WSodoUniversity?t=w_VzjrOWj3D3Mc8BKlQFXA&s=09

ሊንክዲን፡ https://www.linkedin.com/company/wolaita-sodo-university/

ኢንስታግራም፡ https://instagram.com/wolaita_sodo_university?igshid=YmMyMTA2M2Y=

አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን
2.6K viewsedited  14:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 17:42:23
2.1K views14:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 06:46:09 በቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ በ2015 የመውጫ ፈተና /Exit Exam/ ለሚፈተኑ ተመራቂ ተማሪዎች ለመጀመሪያ ጊዜ በበየነ መረብ /online/ የታገዘ ሞዴል የሙከራ ፈተና ተሰጠ።
________

በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ በ2015 የመውጫ ፈተና ለሚፈተኑ ተመራቂ ተማሪዎች ለመጀመሪያ ጊዜ በበይነ መረብ /online የታገዘ ሞዴል የሙከራ ፈተና መሰጠቱን የኮሌጁ ዲን ረዳት ፕ/ር ዘገየ ጳውሎስ አሳውቀዋል።

በበይነ መረብ የታገዘው ሞዴል የሙከራ ፈተና ከዩኒቨርሲቲው ኢንፎርማትክስ ትምህርት ቤት ጋር በመተባበር የተዘጋጀ መሆኑን የገለጹት ዲኑ፤ ፈተናው ተመራቂ ተማሪዎችን ለአገረ-አቀፍ የመውጫ ፈተና በሚያግዝ መልኩ የተዘጋጀ መሆኑንም አመላክተዋል።

ለመውጫ ፈተና ዝግጅት አጋዥ የሆነው ሞዴል የሙከራ ፈተና በኮሌጁ 6 የትምህርት ክፍሎች ተመራቂ ለሆኑ ተፈታኝ ተማሪዎች የተዘጋጀ መሆኑን ረዳት ፕ/ር ዘገየ ገልጸው፤ የፈተና ጥያቄዎቹ ለመጀመሪያ ጊዜ በበይነ መረብ ተዘጋጅቶ ትማሪዎቹ መፈተናቸውን ገልጸዋል።

ለመጀመሪያ ጊዜ በበይነ መረብ በመታገዝ የተዘጋጀው ሞዴል የሙከራ ፈተና በትምህርት ሚኒስትር የሚዘጋጀውን የመውጫ ፈተና /exit exam አሰጣጥ ሂደት እንዲለማመዱት የሚረዳ መሆኑንም የኮሌጁ ዲን አሳውቀዋል።

የኮሌጁን ተማሪዎች ለመውጫ ፈተና/exit exam ዝግጁ እንዲሆኑ ለማስቻል ዘርፈ ብዙ ተግባራት መከናወኑን የገለጹት ዲኑ፤ በቀጣይ ጊዜያት ይኸው ሂደት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተናግረዋል።

በመጪው ሀምሌ ወር በኦንላይን የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና 440 ያህል የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ ተማሪዎች የሚወስዱ መሆኑን ከኮሌጁ የተገኘ መረጃ ያመላክታል።

➭ «ዕውቀትን በተግባር!!»

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት!!

➤ ሚያዝያ 17/2015 ዓ.ም

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት

ፌስቡክWolaita Sodo University4/

ቴሌግራም፡https://t.me/WolaitaSUniversity

ዩቲዩብ፡ https://www.youtube.com/channel/UC6VukdZbl5iVgZGXG8BkMdw/videos

ዌብሳይት፡ http://www.wsu.edu.et/

ትዊተር፡ https://twitter.com/WSodoUniversity?t=w_VzjrOWj3D3Mc8BKlQFXA&s=09

ሊንክዲን፡ https://www.linkedin.com/company/wolaita-sodo-university/

ኢንስታግራም፡ https://instagram.com/wolaita_sodo_university?igshid=YmMyMTA2M2Y=

አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን
1.2K viewsedited  03:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 06:46:08
1.1K views03:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-25 23:21:19 በዩኒቨርሲቲው “በሆቴል እና ቱሪዝም” ዘርፍ ላይ ትኩረት ያደረገ የአቅም ግንባታ ስልጠና ሊሰጥ መሆኑ ተገለጸ።

ስልጠናው "ፓም ኔዘርላንድስ ሲኒየር ኤክስፐርትስ"/PሀM Netherlands Senior Experts/ ከተሰኘ ተቋም ጋር በመተባበር የተዘጋጀ መሆኑም ተመላክቷል።
_______
በሁለትዮሽ የአጋርነት እና ትብብር ማዕቀፍ ከወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ጋር እየሰሩ ካሉ ዓለም አቀፍ አጋር ተቋማት መካከል "ፓም ኔዘርላንድስ ሲኒየር ኤክስፐርትስ"/PሀM Netherlands Senior Experts/ የተሰኘው ተቋም አንዱ ነው።

ፓም ኔዘርላንድስ በአውሮፓዊቷ አገር ኔዘርላንድስ-ዘሔግ መቀመጫውን ያደረገ ነጻ የሙያ፣ የልምድና የዕውቀት ሽግግር አገልግሎት ድጋፍ የሚያደርግ ተቋም መሆኑ ከተቋሙ ለመጡ ልዑካን በዩኒቨርሲቲው በተደረገ አቀባበል ተገልጿል።

ለልዑካኑ በተደረገ የአቀባበል ስነ ሥርዓት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ተወካይ እና የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሙላቱ ዴአ እንዲሁም የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ መምህራን ተገኝተዋል።

ፓም ኔዘርላንድስ ለዘላቂና አካታች ልማት አዎንታዊ ጠቀሜታ ያለውን ሙያዊ ድጋፍ መስጠትን ዓላማው በማድረግ የሚንቀሳቀስ መንግሥታዊ ያልሆነ ተቋም መሆኑ ከልዑካኑ ጋር በተካሄደ ውይይት ተጠቁሟል።

ከዩኒቨርሲቲው ጋር በተፈጠረ ጉድኝት በሆቴል እና ቱሪዝም ዘርፍ ልዩ ትኩረት በማድረግ ለዘርፉ ተዋንያን ተከታታይነት ያለውን የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት እንዲቻል የውል ስምምነት የተፈረመ መሆኑም በመድረኩ ተገልጿል።

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ተወካይ ዶ/ር ሙላቱ ዴአ በሆቴል እና ቱሪዝም የሥራ መስክ ላይ ለተሰማሩ የዘርፉ ባለሙያዎች ከድርጅቱ በመጡ ኤክስፐርቶች የሚሰጠው ስልጠና ጉልህ ጠቀሜታ ይኖረዋል ሲሉ ተናግረዋል።

በሆቴል፣ መስተንግዶና ቱሪዝም ዘርፍ የተሰማሩ ተቋማት የአገልግሎት አሰጣጥ ዘዴ፣ ጥራት እና ትርፋማነት በማሻሻል ረገድ ውጤታማ በመሆን የበለጠ የሥራ ዕድል በመፍጠር ለድህነት ቅነሳ አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ስልጠናው ከፍተኛ ተቀሜታ እንደሚኖረው ነው ዶ/ር ሙላቱ ያሳወቁት።

ኤክስፔርቶቹ በሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍ የተሰማሩ ተቋማት የምርትና አገልግሎት ደረጃቸውን እንዲያሻሽሉ ልምድና ዕውቀታቸውን በተለመደው ሁኔታ ለማጋራት ዝግጁ መሆናቸውውን በመድረኩ ገልጸዋል።

በሆቴል አስተዳደር፣ መስተንግዶ እና ቱሪዝም ዘርፍ ላይ በማተኮር በሚሰጠው ስልጠና በዩኒቨርሲቲው የዘርፉ መምህራን፣ ተማሪዎች እንዲሁም ከወላይታ ሶዶ ከተማ ደረጃቸውን ከጠበቁ ሆቴሎች የተወጣጡ ባለሙያዎች የሚሳተፉ መሆኑ ተመላክቷል።

ዩኒቨርሲቲው ለሆቴል፣ ቱሪዝምና ሆስፒታሊቲ ዘርፍ ልዩ ትኩረት በመስጠት ብቁ እና የሰለጠነ የሰው ኃይል ማፍራት በሚቻልበት አግባብ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል።

➭ «ዕውቀትን በተግባር!!»

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት!!

➤ ሚያዝያ 17/2015 ዓ.ም

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት

ፌስቡክWolaita Sodo University4/

ቴሌግራም፡https://t.me/WolaitaSUniversity

ዩቲዩብ፡ https://www.youtube.com/channel/UC6VukdZbl5iVgZGXG8BkMdw/videos

ዌብሳይት፡ http://www.wsu.edu.et/

ትዊተር፡ https://twitter.com/WSodoUniversity?t=w_VzjrOWj3D3Mc8BKlQFXA&s=09

ሊንክዲን፡ https://www.linkedin.com/company/wolaita-sodo-university/

ኢንስታግራም፡ https://instagram.com/wolaita_sodo_university?igshid=YmMyMTA2M2Y=

አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን
1.4K viewsedited  20:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-25 23:21:01
1.2K views20:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-25 14:17:06 የአረንጓዴ አሻራ ልማት በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ

https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid0BkcyGSpmoynaHmUU4dyNzRkdUnm3ysfPyqUgEFMmzkfb4HUAXzTciGfwEbn3sVnnl&id=100063820159424&mibextid=Nif5oz
1.8K views11:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-24 20:27:25 ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በሁለትዮሽ የአጋርነትና ትብብር ማዕቀፍ ስምምነት በመፍጠር ከፍተኛ ሀብት ላስገኙ ከፍተኛ ተመራማሪዎችና መምህራን ዕውቅና ተሰጣቸው።
_______
በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ከመደበኛ የመማር ማስተማር ሥራ ጎን ለጎን ከአለም አቀፍ ተቋማት ጋር በሁለትዮሽ የአጋርነት ትብብር ማዕቀፍ ስምምነት በመፍጠር ሀብት አፈላልገው ላገኙና በዘርፉ የድርሻቸውን ተቋማዊ ሚና ለተወጡ ተመራማሪዎች እና መምህራን ዕውቅና ተሰጥቷቸዋል።

የዩኒቨርሲቲው አለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት መምህር ፍሰሀ ሰለሞን፡ ከአለም አቀፍ ተቋማት ጋር አጋርነትና ትብብር በመመስረት ሀብት በማፈላለግ የድርሻቸውን ተቋማዊ ሚና የተወጡና እየተወጡ ያሉ ከፍተኛ ተመራማሪዎችንና ባለሙያዎችን እንደ ተቋም ላበረከቱት ጉልህ አስተዋጽኦ የላቀ ምስጋና ይገባቸዋል ሲሉ ተናግረዋል።

ለዚህም ዳይሬክቶሬቱ ለ2ኛ ጊዜ ባካሄደው የዕውቅና ሥነ ስርዓት ከተለያዩ ዓለም አቀፍ ዩኒቨርሲቲዎች እና ተቋማት ጋር ሳይሰላቹ በመጻጻፍ ሀብት በማፈላለግ ረገድ ህጋዊ አካሄድን ተከትለው የሁለትዮሽ የመግባቢያ ሰነድ እንዲፈረ ያደረጉ እንዲሁም ወደ ሥራ በመግባት ዓለም አቀፍ ልምዶችን እና ተጨማሪ ሀብት ወደ ዩኒቨርሲቲው እንዲመጣ ላደረጉ አካላት ዕውቅናው የተሰጠ መሆኑንም ዳይሬክተሩ አሳውቀዋል።

ዕውቅናው የተሰጣቸው ከፍተኛ ተመራማሪዎች ባለሙያዎች ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በጋራ የምርምር እና ፕሮጀክቶች በመስራት፤ በአጫጭር እና የረዥም ጊዜ ስልጠናዎችን በማመቻቸት፤ የድህረ ምረቃ የትምህርት ዕድል በማመቻቸት፤ የተማሪና የሠራተኞችን ተቋማዊ ልውውጥ በማሳደግ እንዲሁም የተለያዩ የቁሳቁስ ድጋፍ እንዲገኝ ያደረጉና የድርሻቸውን ሚና የተወጡ ናቸው ሲሉም መምህር ፍሰሀ ጠቁመዋል።

ዩኒቨርሲቲው በሁለትዮሽ አጋርነት ለሚተገበሩ የአለም ዓቀፋዊነት ሥራዎች ልዩ ትኩረት ሰጥቶ በተቀናጀ መልኩ እየተንቀሳቀሰ እንደሚገኝ ዳይሬክተሩ ገልጸው፤ እንደ ተቋም በዓለም አቀፋዊነት የትብብርና የአጋርነት ማዕቀፍ ከ 47 በላይ የመግባቢያ ሰነድ መፈረሙን እና ይህም ለተቋም የዕድገት ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ተናግረዋል።

መምህር ፍሰሃ አክለውም፤ ዩኒቨርሲቲው በተለያዩ የስራ መስኮች ከተቋማቱ ጋር በትብብርና አጋርነት ለመስራት ከተፈራረማቸው አጠቃላይ የመግባቢያ ሰነዶች መካከል 24 ያህሉ ሙሉ በሙሉ ወደ ሥራ የገቡ እንደሆኑና 23 ያህሉ ደግሞ የትግበራ ሂደት ላይ እንደሚገኙ ጠቁመዋል።

ከተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በመጻጻፍ አጋርነትን መስርተው ሀብት በማፈላለግ ረገድ የድርሻቸውን ሚና የተወጡ እንዲሁም በትጋት እየሰሩ ያሉ የዩኒቨርሲቲው ተመራማሪዎችና መምህራን ምስጋና ይገባቸዋል ያሉት ዳይሬክተሩ፤ ግራንት በማፈላለግ ተጨማሪ ሀብት እንዲገኝ ያደረጉ አካላትን በማመስገን እውቅና መስጠቱ የላቀ ተነሳሽነትን የሚፈጥር መሆኑንም ገልጸዋል።

ዕውቅናው የተሰጣቸው ከፍተኛ ተመራማሪዎች እና ባለሙያዎች ያላሰለሰ ጥረት በማድረግ ለተቋሙ እድገት ላበረከቱት አስተዋፅዖ ሁሌም ሊመሰገኑ ይገባል ያሉት መምህር ፍሰሃ፤ የዩኒቨርሲቲውን አመራር በመወከል ለዘርፉ ቁልፍ ተዋናዮች፣ ለተመራማሪዎች እና ባለሙያዎች «የምስጋና ወረቀት» በታላቅ ክብር የተሰጠ መሆኑን ገልጸዋል።

ሌሎች የዩኒቨርሲቲው ተመራማሪዎችና ባለሙያዎች ይህንን አርሃያነት በመከተል የተቋሙን ተልዕኮ እና የትኩረት መስክ ታሳቢ ባደረገ መልኩ ከአለም አቀፍ ተቋማት ጋር አጋርነት በመመስረት ሀብት የማፈላለግ ስራ ላይ ትኩረት ሰጥተው የድርሻቸውን ሚና እንዲወጡ ዳይሬክተሩ ጥሪ አቅርበዋል።

ዕውቅና የተበረከተላቸው ከፍተኛ ተመራማሪዎች እና ኤክስፐርቶች እንደ ተቋም የተሰጣቸው እውቅና ለበለጠ ስራ እንደሚያነሳሳቸው በመግለጽ የተቋሙን አመራሮች አመስግነዋል።

➭ «ዕውቀትን በተግባር!!»

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት!!

➤ ሚያዝያ 16/2015 ዓ.ም

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት

ፌስቡክWolaita Sodo University4/

ቴሌግራም፡https://t.me/WolaitaSUniversity

ዩቲዩብ፡ https://www.youtube.com/channel/UC6VukdZbl5iVgZGXG8BkMdw/videos

ዌብሳይት፡ http://www.wsu.edu.et/

ትዊተር፡ https://twitter.com/WSodoUniversity?t=w_VzjrOWj3D3Mc8BKlQFXA&s=09

ሊንክዲን፡ https://www.linkedin.com/company/wolaita-sodo-university/

ኢንስታግራም፡ https://instagram.com/wolaita_sodo_university?igshid=YmMyMTA2M2Y=

አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን
2.2K views17:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-24 20:27:22
1.6K views17:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-23 20:24:42
942 views17:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ