Get Mystery Box with random crypto!

AddisWalta - AW

የቴሌግራም ቻናል አርማ waltatveth — AddisWalta - AW A
የቴሌግራም ቻናል አርማ waltatveth — AddisWalta - AW
የሰርጥ አድራሻ: @waltatveth
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 45.24K
የሰርጥ መግለጫ

This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.
For more updates please visit https://shorturl.at/ehosX https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 347

2022-05-13 14:14:46
#ተገልጋይ - በግብርና ግብአት አቅርቦት ዙሪያ እየተደረገ ያለ ውይይት - አሁን

https://www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate/videos/2210233229153094
1.4K views11:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 13:05:01
የዘ ኢክኖሚስት ጋዜጠኛ ቶም ጋርድነር የሥራ ፈቃድ ተሰረዘ

ግንቦት 5/ 2014 (ዋልታ) የዘ ኢኮኖሚስት መጽሔት ዘጋቢ ጋዜጠኛ ቶም ጋርድነር በኢትዮጵያ መስራት የሚያስችለውን የሥራ ፈቃድ መሰረዙን የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን አስታውቋል።

ጋዜጠኛው የጋዜጠኝነት ሥነ ምግባርና የአገሪቱን ህግ አክብሮ ለመስራት የገባውን ግዴታ ማክበር እንዳልቻለ ባለስልጣኑ ገልጿል።

ጋዜጠኛው ችግሩን እንዲያርም በተደጋጋሚ ውይይት ቢደረግም ከጥፋቱ ለመታረም እንዳልቻለ ባለስልጣኑ አመልክቷል።

ጋዜጠኛው ከአሁን በኋላ በኢትዮጵያ ውስጥ የመስራት ፈቃድ እንደሌለው በደብዳቤ የገለጸለት ሲሆን ጋዜጠኛ ቶም ጋርድነር የሚሰራበት ‘ዘ ኢኮኖሚስት ማጋዚን’ በምትኩ ነጻና ገለልተኛ የሆነ ጋዜጠኛ መመደብ እንደሚችል ተገልጾለታል።

ለፈጣን መረጃዎች፦
ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW
ቴሌግራም https://t.me/WALTATVEth
ዩቲዩብ https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured
ቲዊተር https://twitter.com/walta_info
አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን!
93 views10:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 12:52:23
ህጻን አግቶ ህይወቱ እንዲያልፍ ያደረገው ግለሰብ በ25 ዓመት ፅኑ እስራት ተቀጣ

ግንቦት 5/2014 (ዋልታ) በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ጭልጋ ወረዳ ታዳጊ ህጻንን በማገት ህይወቱ እንዲያልፍ በማድረግ ወንጀል የተከሰሰው ግለሰብ በ25 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ የተወሰነበት መሆኑን የዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አስታወቀ፡፡

የቅጣት ውሳኔው የተላለፈው በጭልጋ ወረዳ የቤዛሆ መቀነት ቀበሌ ነዋሪ በሆነው አበበ ዳኘው ላይ መሆኑን የፍርድ ቤቱ የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያ ማስተዋል ወርቁ ተናግረዋል።

ግለሰቡ ድርጊቱን የፈጸመው በወረዳው የአይከል ከተማ ነዋሪ የሆነውን የ15 ዓመት ታዳጊ ህጻን ጥር 2 ቀን 2013 ዓ.ም ከመኖሪያ ቤቱ አፍኖ በመውሰድ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

ለህጻኑ ወላጆች ስልክ በመደወል 100 ሺሕ ብር ከፍለው ልጃቸውን እንዲወስዱ፤ ብሩን ካልከፈሉ ግን ህጻኑን እንደሚገድለው ሲዝት እንደነበር ባለሙያዋ ገልጸዋል።

በዛተውም መሰረት ህጻኑን በወረዳው ፋይና ገብ ተብሎ በሚጠራው ገደል ውስጥ በመክተት ህይወቱ እንዲያልፍ ማድረጉ በሰውና በሕክምና ማስረጃ መረጋገጡንም አስረድተዋል፡፡

ከፍተኛ ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኙን ክርክር ያዳመጠ ሲሆን፤ ተከሳሹ በእምነት ክህደት ቃሉ ወንጀሉን አልፈጸምኩም ሲል ክዶ ተከራክሯል፡፡

ይሁን እንጂ ተከሳሹ በአቃቢ ሕግ የቀረበበትን ማስረጃ ማስተባበል ባለመቻሉ በወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ህግ ቁጥር 149/1/ መሰረት ጥፋተኛ ሆኖ መገኘቱን ገልጸዋል ሲል የዘገበው ኢዜአ ነው፡፡

ግለሰቡ የቤተሰብ አስተዳዳሪና ከዚህ ቀደም የወንጀል ሪከርድ የሌለበት መሆኑን በቅጣት ማቅለያነት የተመለከተው ፍርድ ቤቱ የ25 ዓመት ጽኑ እስራት ውሳኔ እንዳስተላለፈበት የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያዋ ገልጸዋል።
356 views09:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 12:44:28
ወደ ውጪ መላክ የነበረበት ከ235 ሺሕ ሜትሪክ ቶን በላይ እህል በክምችት መኖሩ ተረጋገጠ

ግንቦት 5/2014 (ዋልታ) ወደ ውጪ መላክ የነበረበት ከ235 ሺሕ ሜትሪክ ቶን በላይ የጥራጥሬ እና የቅባት እህል በክምችት መኖሩ መረጋገጡን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ገለጸ፡፡

ሚኒስቴሩ ከጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት ጋር በመተባበር በአራት ከተሞች በክምችት ተይዘው የሚገኙ የቅባትና ጥራጥሬ ሰብሎች በአይነትና በመጠን ለማጣራት ዳሰሳዊ ጥናት አካሂዷል።
በተደረገው የዳሰሳ ጥናትም፦

- በአዳማ ከተማ 6 ሺሕ 610 ነጥብ 18 ሜትሪክ ቶን የቅባት እህል እንዲሁም 55 ሺሕ 485 ነጥብ 75 ሜትሪክ ቶን የጥራጥሬ ሰብል

- በአቃቂ ቃሊቲ 3 ሺሕ 325 ነጥብ 95 ሜትሪክ ቶን የቅባት እህል እንዲሁም 2 ሺሕ 400 ነጥብ 22 የጥራጥሬ ሰብል

- በቡራዩ ከተማ 43 ሺሕ 569 ነጥብ 25 ሜትሪክ ቶን የቅባት እህል እንዲሁም 116 ሺሕ 844 ነጥብ 99 ሜትሪክቶን የጥራጥሬ እህል

- በገላን 57 ሺሕ 274 ነጥብ 13 ሜትሪክ ቶን የቅባት፣ 177 ሺሕ 514 ነጥብ 82 ሜትሪክ ቶን የጥራጥሬ እህል እንዲሁም 502 ነጥብ 06 ሜትሪክቶን ሌሎች ምርቶች በድምሩ 235 ሺሕ 291 ነጥብ 2 ቶን በክምችት መገኘቱ ተገልጿል።

በሚኒስቴሩ የግብርና ምርቶች መሠረተ ልማት ቡድን መሪ ታረቀኝ ሽበሺ ወደፊት የምርቶቹ ዋጋ ይጨምራል በማለት ምርትን በወቅቱ ወደ ውጪ ገበያ ከመላክ ይልቅ በክምችት ይዞ ማቆየት የሀገሪቱን ብሔራዊ ጥቅም የሚጎዳ መሆኑን መግለጻቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ አመላክቷል።
422 views09:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 12:03:32
የቀን 6፡00 ዜና በቀጥታ ከዋልታ ቴቪ ግንቦት 5/2014

https://www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate/videos/721730309020148
769 views09:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 11:55:32
ኢትዮጵያ ሙዓለ ነዋይ ለማፍሰስ የሚፈልጉ ቁርጠኛ ባለሃብቶችን ለመቀበል ዝግጁ ናት - ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ

ግንቦት 5/2014 (ዋልታ) ኢትዮጵያ መጠነ ሰፊ ሙዓለ ነዋይ ለማፍሰስ የሚፈልጉ ቁርጠኛ ባለሃብቶችን ለመቀበል እና አስቻይ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ዝግጁ መሆኗን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

በቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ በ60 ሚሊየን ዩሮ ወጪ የተገነባው ሱፍሌት ማልት ብቅል አምራች ፋብሪካ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በተገኙበት በዛሬው ዕለት ተመርቋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፋብሪካው ከ50 ሺሕ ከሚበልጡ አርሶ አደሮች ጋር ትስስር በመፍጠር በዓመት 60 ሺሕ ቶን ብቅል ለማምረት የሚያስችል መሆኑ በዋናነት የውጭ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርቶች ለመተካት የሚደረገውን ጥረት ለመደገፍ ያስችላል ብለዋል።

ኢትዮጵያ እንዲህ ባለ መጠነ ሰፊ መንገድ ሙዓለ ነዋይ ለማፍሰስ የሚፈልጉ ቁርጠኛ ባለሃብቶችን ለመቀበል እና አስቻይ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ዝግጁ መሆኗንም በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል።

ለፈጣን መረጃዎች፦
ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW
ቴሌግራም https://t.me/WALTATVEth
ዩቲዩብ https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured
ቲዊተር https://twitter.com/walta_info
አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን!
888 views08:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 11:48:40
የሕዳሴ ግድቡን 3ኛ ዙር የውሃ ሙሌት ለማከናወን የምንጣሮ ሥራ መጀመሩ ተገለጸ

ግንቦት 4/2014 (ዋልታ) የታላቁን የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ 3ኛ ዙር የውሃ ሙሌት ለማከናወን በ21 ሺሕ ሄክታር መሬት ላይ የምንጣሮ ሥራ እየተሰራ መሆኑን የመተከል ዞን የተቀናጀ ኮማንድ ፖስት ዋና አስተባባሪ ሌ/ጀኔራል ደስታ አብቼ ገለጹ።

የሕዳሴ ግድቡ ግንባታ ያለምንም የፀጥታ ችግር እንዲከናወን በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡

ሠራዊቱ የተሠጠውን ተልዕኮ ሌት ተቀን በቁርጠኝነት መፈፀም በመቻሉ ለሕዳሴ ግድብ ግንባታ የሚውሉ ግብአቶች በሰላም ተጓጉዘው እንዲደርሱ እና ሰራተኞችም ደኅንነታቸው ተጠብቆ እንዲሰሩ ማድረግ መቻሉ ተገልጿል፡፡

የግድቡ ግንባታ ሰራተኞች ያለምንም የፀጥታ ስጋት ሥራቸውን እንዲያከናውኑ የተቀናጀ የፀጥታ ኃይሉ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ማረጋገጣቸውን የመከላከያ ሰራዊት መረጃ አመላክቷል።

የተቀናጀ የፀጥታ ኃይሉ ዕድገታችንን ለማደናቀፍ ከሱዳን ሰርገው የሚገቡ ኃይሎችን እየተከታተለ ሴራቸውን እያከሽፈው እንደሚገኝ እና በቀጣይም ከአካባቢው ማኅበረሰብ እና ሲቪል አመራሮች ጋር ተቀናጅቶ ግዳጁን በአስተማማኝ ለመወጣት ዝግጁነቱ የላቀ መሆኑን የኮማንድ ፖስቱ ዋና አስተባባሪው ጠቁመዋል፡፡

ለፈጣን መረጃዎች፦
ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW
795 views08:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 11:31:26
ሀገር ዐቀፍ የምርምር አውደ ጥናትና ኮንፍረንስ በሁለት ዩኒቨርሲቲዎች ተጀመረ

ግንቦት 5/2014 (ዋልታ) ሀገር ዐቀፍ የምርምር አውደ ጥናትና ኮንፍረንስ በአርባ ምንጭና ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲዎች ዛሬ ተጀምሯል።

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተጀመረው አውደ ጥናት “ምርምር ለዘላቂ ልማት” በሚል መሪ ሀሳብ የሚካሄድ ስምንተኛው ዙር ሲሆን ለሁለት ቀናት የሚቆይ ነው ተብሏል።

በግብርናና ባህል ልማት እንዲሁም የቴክኖሎጂ ውጤቶችና ፋይዳቸው ላይ የሚያጠነጥኑ የተለያዩ የጥናትና ምርምር ሥራዎች ቀርበው በአውደ ጥናቱ ውይይት እንደሚደረግባቸው ይጠበቃል፡፡

በአውደ ጥናቱ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፤ ከ45 ዩኒቨርሲቲዎች የተወጣጡ ምሁራንና አመራሮች እየተሳተፉ ነው፡፡

በተያያዘም በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ 10ኛው ሀገር ዐቀፍ የምርምር ኮንፍረንስ መጀመሩ ተገልጿል፡፡

“በተግባር ተኮር ምርምርና ፈጠራ ሥራ የኅብረተሰቡን አቅም መገንባት” በሚል ርዕስ በተዘጋጀው ኮንፍረንስ የግብርና፣ የጤና እንዲሁም የቴክኖሎጂ ውጤቶችን ጨምሮ የተለያዩ የምርምር ውጤቶችና ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበው ውይይት እንደሚደረግባቸው ተመላክቷል።

የምርምር ውጤቶቹ እንደ ሀገር የተጀመሩ የለውጥና የዕድገት ጉዞዎችን ዘላቂ በማድረግ ለተሻለ የማኅበረሰብ አቅም ግንባታ ሚናቸው የላቀ እንደሆነ መገለጹን የዘገበው ኢዜአ ነው።

ለሁለት ተከታታይ ቀናት በሚቆየው ኮንፍረንስ የፌዴራል፣ የክልልና የዞን ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የዩኒቨርሲቲዎች ፕሬዝዳንቶች፣ ተመራማሪዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በመሳተፍ ላይ ናቸው።

ለፈጣን መረጃዎች፦
ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW
928 views08:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 11:16:14
የአፋር ክልል ለሶማሌ ክልል የ10 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ

ግንቦት 5/2014 (ዋልታ) የአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት በሶማሌ ክልል በድርቅ ምክንያት ለተጎዱ ወገኖች የ10 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አድርጓል።

ድጋፉን ለማስከከብ ማለዳ ጅግጅጋ ከተማ የገቡት የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ለሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ አስረክበዋል።

የአፋር እና የሶማሌ ወንድማማች ሕዝቦች በተለያዩ ጊዜያት እርስ በእርስ ሲደጋገፉ የመጡ መሆኑ ይታወቃል።

የአፋር ክልል በአሁኑ ወቅት አሸባሪው ሕወሓት በከፈተው ወረራ ከፍተኛ የሆነ ችግር ውስጥ ቢሆንም ለወንድም ሶማሌ ሕዝብ በድርቅ ምክንያት ለደረሰበት ጉዳት የክልሉ መንግሥት ድጋፉን አድርጓል።

ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሀመድ የአፋር ክልል በሶማሌ ክልል በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች ላደረገው ድጋፍ ምስጋና ማቅረባቸውን የአፋር ክልል ኮሙዩኒኬሽን መረጃ ያመለክታል።

ለፈጣን መረጃዎች፦
ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW
1.0K views08:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 11:07:31
#እንነጋገር፤ ታሪክ ለሀገራዊ ምክክሩ ፈተና ወይስ መደላድል?

https://www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate/videos/352165433645918
1.1K views08:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ