Get Mystery Box with random crypto!

AddisWalta - AW

የቴሌግራም ቻናል አርማ waltatveth — AddisWalta - AW A
የቴሌግራም ቻናል አርማ waltatveth — AddisWalta - AW
የሰርጥ አድራሻ: @waltatveth
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 45.24K
የሰርጥ መግለጫ

This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.
For more updates please visit https://shorturl.at/ehosX https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 345

2022-05-14 09:36:01
የአውሮፓ ኅብረት የመንግሥትን መልካም ጥረቶች የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ ድጋፍ እንደሚያደርግ ገለጸ

ግንቦት 6/2014 (ዋልታ) የአውሮፓ ኅብረት የመንግሥትን ያልተገደበ ሰብአዊ እርዳታ እንዲዳረስ ያሳለፈው የተኩስ አቁም ውሳኔ እና ለችግሮች እልባት ለመስጠት እየተጓዘበት ያለው መንገድ አበረታች መሆኑን ገልጾ ጥረቶቹ የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ ድጋፍ እንደሚያደርግ ገለጸ፡፡

የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን የአውሮፓ ኅብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛን አኔት ዌበር (ዶ/ር)ን በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን እና በሰሜኑ ግጭት እና በድርቅ ምክንያት ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎች እየተደረገ ስላለው ሰብአዊ እርዳታ አቅርቦት ወቅታዊ ሁኔታ ዙሪያ እና በቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ለልዩ መልዕክተኛዋ ገለጻ አድርገዋል።

መንግሥት ያልተገደበ ሰብአዊ እርዳታ እንዲዳረስ የተናጥል የተኩስ አቁም ስምምነት አድርጎ እርዳታ እንዲደርስ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

በሰብአዊ እርዳታ ሥራ ላይ ከተሰማሩ ድርጅቶች መካከል አንዱ የሆነው የዓለም የምግብ ፕሮግራም ሰብአዊ እርዳታ እያሰራጨ መሆኑን ተናግረዋል። https://www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate/posts/5424201760993894
1.1K views06:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-14 08:18:29
"እኔ ለከተማዬ ፅዳትና ውበት ባለቤት ነኝ" በሚል የፅዳት ዘመቻ ተካሄደ

ግንቦት 6/2014 (ዋልታ) በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ "እኔ ለከተማዬ ፅዳትና ውበት ባለቤት ነኝ" በሚል መሪ ሀሳብ የፅዳት ዘመቻ ተካሂዷል፡፡

በፅዳት ዘመቻው የተገኙት የክፍለ ከተማው የፅዳት አስተዳደር ጽሕፈት ቤት ኃለፊ አሸናፊ ተፈሪ አካባቢን ማፅዳት ለሀገር ውበት እና የቤተሰብ ጤንነትን ለማስጠበቅ ወሳኝ በመሆኑ የዘወትር ተግባር ሊሆን ይገባል ብለዋል፡፡

ከተማዋን ውብና ማራኪ ለማድረግ ሀሉም ኅብረተሰብ ፅዳትን ከቤቱ እና ከአካባቢው መጀመር እንዳለበትም ገልጸዋል፡፡

በፅዳት ዘመቻው የክፍለ ከተማው ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጀማል ረዲን፣ ከፍተኛ አመራሮች፣ የሃይማኖት አባቶች እና በርካታ ቁጥር ያላቸው የክፍለ ከተማው ነዋሪዎች ተሳትፈዋል፡፡

በአመለወርቅ መኳንንት

ለፈጣን መረጃዎች፦
ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW
ቴሌግራም https://t.me/WALTATVEth
ዩቲዩብ https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured
ቲዊተር https://twitter.com/walta_info
አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን!
1.6K views05:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 20:33:17
“የጸጥታ ኃይሎች የተሻለ አቋምና ብቃት ላይ ይገኛሉ ፤ ጠላቶቻችን ይህንን ሊረዱ ይገባል” - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
2.0K views17:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 20:06:16
አልሸባብ የሽብር ተልዕኮ የሰጣቸው 6 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ

ግንቦት 5/2014 (ዋልታ) በሶማሊያ በሚንቀሳቀሰው አልሸባብ የሽብር ቡድን ሰልጥነው በኢትዮጵያ የጥፋት ተልዕኮ ተሰጥቷቸው ወደ ስምሪት ሊገቡ የነበሩ ስድስት ተጠርጣሪ ግለሰቦች በአዲስ አበባ ከተማ እና በኦሮሚያ ክልል በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አስታውቋል።

የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት እንዳስታወቀው፤ ጃፋር ያያ ረቢ፣ ሙሳ ቀና ቤኛ፣ አደም ቤካ ኬነሳ፣ አብዱራዛቅ ሻፊ አሊ፣ አብዱል ከሪም አህመድ ኩሽዬ እና ዘቢር ጂያድ ከድር የተባሉት ተጠርጣሪዎች በሶማሊያ በሚንቀሳቀሰው የአልሸባብ የሽብር ቡድን ተመልምለው በኢትዮጵያ በህቡዕ ድጋፍ በሚያደርጉ አካላት አማካኝነት ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል ተሰባስበው ከየካቲት 2 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ በተለያዩ ወቅቶች ወደ ሶማሌ እንዲገቡ ተደርጓል።

በዚያም የሽብር ጥቃት ለመፈጸም የሚረዱ የተለያዩ ስልቶችንና የቡድኑን አስተምህሮ የተመለከቱ ስልጠናዎች ለሶስት ወራት ወስደዋል።

በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች የሽብር ጥቃት እንዲፈጽሙ የተመለመሉትና ስልጠና የወሰዱት ስድስቱ ተጠርጣሪ ግለሰቦች ግንቦት 3 ቀን 2014 ዓ.ም ከሶማሊያ ተነስተው በሞያሌ በኩል ወደ ሀገር ውስጥ መግባታቸው የተመላከተ ሲሆን ፤ ሚያዚያ 4 እና 5 ቀን 2014 ዓ.ም በሁለት ቡድን ተከፍለው ወደ ጅማ ለመሄድ አቅደው እንደነበርም ጠቁሟል።
548 views17:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 19:36:01
150 ዜጎች ከየመን ወደ ሀገራቸው ተመለሱ

ግንቦት 5/2014 (ዋልታ) ከየመን በተደረገ የአንድ ጊዜ በረራ 150 ዜጎች ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።

ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና ከኢሚግሬሽን የተወክሉ ልዑካን ዜጎችን ወደ ሀገራቸው የመመለስ ሥራውን በኤደን የመን እየሰሩ መሆናቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽ/ቤት መረጃ አመላክቷል።

ለፈጣን መረጃዎች፦

ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW
ቴሌግራም https://t.me/WALTATVEth
ዩቲዩብ https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured
ቲዊተር https://twitter.com/walta_info
አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን!
913 viewsedited  16:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 19:27:30
ትሕነግ የጦርነት ነጋሪት እየጎሰመ በመሆኑ በየደረጃው ያለው የፀጥታ መዋቅር ዝግጁ እንዲሆን የአማራ ክልል መንግሥት አሳሰበ

ግንቦት 5/2014 (ዋልታ) ወራሪው የትሕነግ ቡድን በየቀኑ የጦርነት ነጋሪት እየጎሰመ እና የትግራይን ሕዝብ ለጦርነት እያነሳሳ መሆኑን የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የጸጥታ ምክር ቤት አስታውቋል፡፡

የክልሉ የፀጥታ ምክር ቤት ባደረገው ስብሰባ የክልሉን ሰላምና ፀጥታ ሁኔታ በዝርዝር የገመገመ ሲሆን የአሸባሪው ትሕነግን አደገኛ ቅዠት መመከትና መቀልበስ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ተወያይቷል፡፡
ምክር ቤቱ በየደረጃው ያለው የፀጥታ መዋቅር ዝግጁ መሆን እንዳለበትም አቅጣጫ ያስቀመጠም ሲሆን በጉዳዩ ላይ መግለጫ አውጥቷል፡፡

የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የፀጥታ ምክር ቤት የሰጠው መግለጫ ሙሉ ቃል አንደሚከተለው ቀርቧል፡-

የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የፀጥታው ምክር ቤት ባደረገው ስብሰባ የክልሉን ሰላምና ፀጥታ ሁኔታ በዝርዝር ገምግሟል፡፡ የወያኔ ወራሪ ቡድን በየቀኑ የጦርነት ነጋሪት እየጎሰመ የትግራይን ህዝብ ለጦርነት እያነሳሳ በአማራ ክልል ላይ ዳግም ጦርነት አውጇል፡፡

ይህን አደገኛ ቅዠቱን ለመመከትና ለመቀልበስ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ የክልሉ መንግስት የፀጥታ ምክርቤት በአንክሮ ተወያይቶበታል፡፡ ጸጥታ ምክርቤቱ በየደረጃው ያለው የፀጥታ መዋቅር ዝግጁ መሆን እንዳለበት አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡

በሌላ በኩል በየደረጃው በተደረጉ ህዝባዊ ውይይቶች ላይ ጎልተው ከወጡ ወሳኝ ጉዳዮች መካከል አንዱ የህግ ማስከበር ስራ መላላት ተጠቃሽ መሆኑን ጸጥታ ምክር ቤቱ በጥልቀት አንስቷል፡፡

https://www.facebook.com/489211707826282/posts/pfbid02NiuEwFUbqA7bcgUxfeupqKwzyKPmfRYUC9bzeGtcq3Mh3aZYaRNb2NjJ9hL4rd1Vl/
1.0K viewsedited  16:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 19:11:06
ኢትዮጵያ የደቡብ ሱዳን አገራዊ ምክክር ስኬታማ እንዳይሆን ካደረገው ችግር መማር አለባት ተባለ

ግንቦት 5/2014 (ዋልታ) ኢትዮጵያ የደቡብ ሱዳን አገራዊ ምክክር ስኬታማ እንዳይሆን ካደረገው የአካታችነት ችግር ትምህርት መውሰድ እንዳለባት በጁባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ፣ ሰላምና ጸጥታ ረዳት ፕሮፌሰር አብርሃም ኮኣ ንዮን መከሩ።

አገራዊ ምክክሩ ተዓማኒነትና ግልጸኝነት እንዲኖረው የመገናኛ ብዙኃን ለአጠቃላይ ሂደቱ ሽፋን ሊሰጡት እንደሚገባም ነው ያመላከቱት።

ደቡብ ሱዳን እ.አ.አ በ2011 ነጻነቷን ከተቀዳጀች በኋላ ከገባችበት የእርስ በእርስ ጦርነት ለመውጣት የተለያዩ የሰላም አማራጮችን ተከትላለች።

ከእነዚህም መካከል አ.አ.አ በ2017 ወደ ሥራ ያስገባችው አገራዊ ምክክር አንዱ ሲሆን ምክክሩም የተጠበቀውን ያህል ውጤት ማምጣት አልቻለም።

ለዚህም ደግሞ ምክክሩ የአካታችነት ችግር ያለበት መሆኑን ነው የተለያዩ መረጃዎች የሚያሳዩት።

ይህንን ሃሳብ የሚጋሩት የጁባ ዩኒቨርሲቲው አብርሃም ኮኣ ንዮን ኢትዮጵያም አካታችነት ላይ ጥንቃቄ ልታደርግ ይገባል ብለዋል።

የደቡብ ሱዳኑ ምክክር የተካሄደው የጸጥታ ችግር በነበረበት ወቅት እንደነበር አስታውሰው፤ በምክክሩ የተወሰኑ ሥፍራዎች ሳይካተቱ መቅረታቸውን ነው የገለጹት።

በተጨማሪም በአገራዊ ምክክሩ የተነሱትና በመጨረሻም ለውሳኔ የቀረቡት ምክረ-ሃሳቦች ሙሉ በሙሉ ገቢራዊ አለመሆናቸውም ሌላኛው ችግር እንደነበር መግለጻቸውን የዘገበው ኢዜአ ነው።

በመሆኑም የኢትዮጵያ መንግሥት ተመሳሳይ ስህተት እንዳይፈጽም የመከሩት ረዳት ፕሮፌሰሩ ኢትዮጵያ የደቡብ ሱዳንን ተሞክሮን በደንብ ማጤን አለባት ብለዋል።
1.0K views16:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 19:06:18
ዋልታ ምሽት በቀጥታ ግንቦት 5/2014

https://www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate/videos/554224312796376
975 views16:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 18:20:19
በሚቀጥሉት 10 ቀናት በምዕራብና የደቡብ ምዕራብ ተፋሰሶች ላይ የተሻለ ዝናብ ይኖራል

ግንቦት 5/2014 (ዋልታ) በሚቀጥሉት አሥር ቀናት በአገሪቱ ምዕራብና የደቡብ ምዕራብ ተፋሰሶች ላይ የተሻለ የዝናብ ሁኔታ እንደሚኖራቸው የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ።

ኢንስቲትዩቱ በሚቀጥሉት አሥር ቀናት የበልግ ዝናብ በአገሪቱ የምዕራብ አጋማሽ አካባቢዎች እየተስፋፋ ይሄዳል ብሏል።

እነዚሁ አካባቢዎች ከመደበኛ በላይ የሆነ ዝናብ እንደሚያገኙም የሚቲዎሮሎጂ ትንበያዎች ያመለክታሉ ነው ያለው።

የዝናቡ ሁኔታ በደቡብ ኢትዮጵያ አካባቢዎች ደግሞ ከሞላ ጎደል ቀጣይነት እንደሚኖረውም አመልክቷል።

በእነዚሁ ቀናት ለዝናብ መፈጠር አስተዋጽኦ ሊያደርጉ የሚችሉ የሚቲዎሮሎጂ ክስተቶች ቀጣይነት እንደሚኖራቸውም ተጠቁሟል።

ይህም በተለያየ የዕድገት ደረጃዎች ላይ ለሚገኙ የበልግ ሰብሎችና ለቋሚ ተክሎች የውሃ ፍላጎትን ለማሟላት ይረዳልም ተብሏል።

በአርብቶ አደርና ከፊል አርብቶ አደር አካባቢዎች ለግጦሽና ለመጠጥ ውሃ አቅርቦት መሻሻል የጎላ ጠቀሜታ እንደሚኖረውም ነው የገለጸው።

በተጨማሪም ለመኸር ግብርና ዝግጅት መልካም አጋጣሚን እንደሚፈጥርም ኢንስቲትዩቱ አመላክቷል::
1.4K views15:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 17:15:01
በሀገር አቋራጭ የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የታሪፍ ማሻሻያ ተደረገ

ግንቦት 5/2014 (ዋልታ) በነዳጅ ዋጋ ጭማሪ ምክንያት በአገር አቋራጭ የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ለሚሰጡ ተሽከርካሪዎች የትራንስፖርት ታሪፍ ማሻሻያ መደረጉን የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

ሚኒስቴሩ የአገር አቋራጭ የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ለሚሰጡ ተሽከርካሪዎች የትራንስፖርት ታሪፍ ማሻሻያ ያደረገው ከሚያዝያ 30 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ የነዳጅ መሸጫ ዋጋ ላይ ማስተካከያ መደረጉን ተከትሎ ነው፡፡

በዚህም መሠረት ነባር ታሪፍ በደረጃ አንድ ተሽርካሪ በአስፋልት መንገድ በሰው በኪሎ ሜትር 0 ነጥብ 493 የነበረው በአዲሱ ታሪፍ በኪሎ ሜትር 0 ነጥብ 039 ጭማሪ በማድረግ በሰው በኪሎ ሜትር ብር 0 ነጥብ 532 ሆኗል ተብሏል፡፡

ደረጃ አንድ በጠጠር መንገድ በሰው በኪሎ ሜትር ታሪፍ 0 ነጥብ 548 የነበረው ወደ 0 ነጥብ 596 ከፍ ብሏል፡፡ በዚህም በኪሎ ሜትር የ 0 ነጥብ 049 ጭማሪ አድርጓል፡፡

በሌላ በኩል በደረጃ ሁለት በአስፋልት መንገድ ነባር ታሪፍ በሰው በኪሎ ሜትር 0 ነጥብ 457 የነበረው በአዲሱ ታሪፍ በኪሎ ሜትር የ0 ነጥብ 039 ጭማሪ በማድረግ በሰው በኪሎ ሜትር 0 ነጥብ 496 ሆኗል፡፡
1.7K views14:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ