Get Mystery Box with random crypto!

AddisWalta - AW

የቴሌግራም ቻናል አርማ waltatveth — AddisWalta - AW A
የቴሌግራም ቻናል አርማ waltatveth — AddisWalta - AW
የሰርጥ አድራሻ: @waltatveth
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 45.24K
የሰርጥ መግለጫ

This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.
For more updates please visit https://shorturl.at/ehosX https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 340

2022-05-16 20:23:01
አምባሳደር ዲና ኢትዮጵያ ለሶማሊያ ሰላም ከፍተኛ የሕይወት ዋጋ ከፍላለች አሉ

ግንቦት 8/2014 (ዋልታ) ኢትዮጵያ ለሶማሊያ ሰላም ከፍተኛ የሕይወት ዋጋ የከፈለች እና በቀጣይም ለሀገሪቷ ዘላቂ ሰላም ከአዲሱ መንግሥት ጎን የቆመች መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ተናገሩ።

አምባሳደር ዲና ፤ ኢትዮጵያ ከሶማሊያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ትብብር በማጠናከር ለአካባቢው ሰላም እና መረጋጋት የሚኖራትን ሚና አጠናክራ ትቀጥላለች ብለዋል፡፡

አገራቱ የቆየ ዲፕሎማሲያዊ እና የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ያላቸው አገሮች መሆናቸውን በማስታወስ የኢኮኖሚ እና ፖለቲካዊ ትብብር እንዲሁም የልማት ትስስራቸው ጠንካራ መሠረት ያለው መሆኑንም ጠቅሰዋል።

በጎረቤት አገር ሶማሊያ ዘላቂ ሰላም እንዲኖር የኢትዮጵያ ድጋፍ እና እገዛ እስካሁንም የዘለቀ መሆኑን ጠቅሰው ሶማሊያ ሰላማዊ ምርጫ እና በዴሞክራሲያዊ መንገድ ያካሄደችውን የስልጣን ሽግግር ኢትዮጵያ ታደንቃለች ብለዋል።

የሶማሊያ ሰላማዊ የምርጫ ሂደት እና የስልጣን ሽግግር ለሶማሊያውያን ኩራት ሲሆን ለሌሎች የአፍሪካ አገራትም በጥሩ ተሞክሮነት የሚወሰድ መሆኑን አምባሳደር ዲና ገልጸዋል።

በመሆኑም ኢትዮጵያ ከሶማሊያ ጋር ያላትን ሁለንተናዊ ትብብር ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ በአዲሱ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ ሞሐሙድ ከሚመራው መንግሥት ጋር በቅርበት እንደምትሰራም አረጋግጠዋል።

በተጨማሪ ድህነትን በመዋጋት እና ድርቅን በመከላከል እንዲሁም በቀጣናው የልማት ትስስርን በማጎልበት ሽብርተኝነት በጋራ እንዋጋለን ብለዋል።

በኢኮኖሚ ውህደት፣ በንግድ፣ በመሠረተ-ልማት ትስስር እና የሁለቱን አገራት ሕዝቦች በሚጠቅሙ ፕሮጀክቶች ላይ በጋራ መስራታችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል።
2.3K views17:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-16 20:08:38 የቤተ እምነቶች መልሶ ግንባታ በስልጤ ዞን



2.0K views17:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-16 19:52:20
የታሪክና የኦሮሞ ባህል ምሁሩ አቶ ስንታየሁ ቶላ አረፉ

ግንቦት 8/2014 (ዋልታ) ታላቁ የታሪክና የኦሮሞ ባህል ምሁር አቶ ስንታየሁ ቶላ ቀናዓ ባደረባቸው ድንገተኛ ህመም ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።

አቶ ስንታየሁ ቶላ በኦሮሚያ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ከባለሙያነት እስከ ምክትል ኃላፊነት በሀገር ደረጃ ብሎም በዓለም ዐቀፍ ደረጃ የኦሮሞን ሕዝብ ያስተዋወቀ በርካታ ሥራዎችን የሰሩ ታላቅ ምሁር ነበሩ።

ያደረባቸው ድንገተኛ ህመም እስኪያጋጥማቸውና ለህልፈት እስኪዳረጉ ድረስም የኦሮሞ ጥናትና ምርምር እኒስትቲዩት ምክትል ዳይሬክተር ሆነው ሲያገለግሉ ነበር።

አቶ ስንታየሁ ለኦሮሞ ሕዝብ ብሎም ለኢትዮጵያ ከፈፀሟቸው ተግባራት መሀከል የገዳ ስርዓት ከማይዳሰሱ የሰው ልጅ ሀብቶች መሀከል እንዲሰፍርና በዩኔስኮ እንዲመዘገብ የአንበሳውን ድርሻ የተወጡ ሰው ናቸው።

የኦሮሞ ሕዝብ በአደዋ ድል፣ በሳምቤና በሌሎች የጣሊያን የድል አውድማዎች በጥናት በማሳየት የኦሮሞ ሕዝብ ለኢትዮጵያዊያን ጋሻ መሆናቸውን አንፀባርቀው ማሳየትም ችለዋል።

ከገዳ ስርዓት በተጨማሪም በኦሮሚያ ክልል የሚገኙ ቅርሶች የሶፍ-ዑመር ዋሻ፣ ድሬ ሼክ ሁሴን፣ የባሌ ተራሮች ፓርክና ሌሎችም በዩኔስኮ እንዲመዘገቡ በእጩነት እንዲቀርቡም ጠንካራ ሥራ ሲሰሩ ቆይተዋል።

የታሪክና የኦሮሞ ባህል ምሁሩ አቶ ስንታየሁ ቶላ የሁለት ልጆች አባት ሲሆኑ ባደረባቸው ድንገተኛ ህመም በዛሬው ዕለት ግንቦት 8/2014 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
2.1K views16:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-16 19:21:59
ህጋዊ የነዳጅ አቅርቦትና ስርጭትን በሚያስተጓጉሉ አካላት ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ ተገለጸ

ግንቦት 8/2014 (ዋልታ) ህጋዊ የነዳጅ አቅርቦትና ስርጭትን በማስተጓጎል ነዳጅ ለኅብረተሰቡ በወቅቱ እንዳይደርስ በሚያደርጉ አካላት ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

በነዳጅ አቅርቦትና ስርጭት ዙሪያ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ የሚያስችል ምክክር በሚኒስቴሩ ተካሂዷል፡፡

በምክክሩ ላይ አምባሳደር ግርማ ብሩን ጨምሮ ከብሔራዊ መረጃና ደኅንነት፣ ከንግድ ቢሮዎች፣ ከኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት፣ ከኢትዮጵያ ነዳጅና ኢነርጅ ባለስልጣን እንዲሁም ከነዳጅ አቅራቢ ድርጅቶች የተውጣጡ የሥራ ኃላፊዎች የተገኙ ሲሆን በነዳጅ አቅርቦትና ስርጭት ዙሪያ የተስተዋሉ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ላይ ውይይት ተካሂዷል፡፡

ያለፈው ሚያዚያ ወር የትንሳኤ በዓል እና 1443ኛው የኢድ በዓል የተከበሩበት ወቅት በመሆኑ በበዓላቱ ምክንያት ነዳጅ ከጂቡቲ ወደብ ወደ አዲስ አበባ ባለመጫኑ በተፈጠረ ክፍተት ጊዜያዊ የነዳጅ እጥረት በመከሰቱ በየማደያዎቹ የተሽከርካሪዎች ሰልፍ መስተዋሉ በውይይቱ ወቅት ተገልጿል፡፡

በውይይቱ የአቅርቦት ውስንነት፣ የቁጥጥር ስርዓቱ ድክመት፣ ከጅቡቲ አዲስ አበባ ባለው የነዳጅ ማጓጓዝ ሂደት የነዳጅ ቅሸባና የአሽከርካሪዎች በየቦታው ለረጅም ሰዓታት መቆም እንዲሁም መንግሥት ከፈቀደው የግብይት ቦታና ዋጋ ውጪ የዋጋ ጭማሪ አድርጎ የመሸጥ ፍላጎት የነዳጅ አቅርቦትና ሥርጭቱን እየፈተኑት ያሉ ችግሮች መሆናቸው ተብራርቷል፡፡

ችግሮቹን በመፍታት ምርቱን ለተጠቃሚው ለማድረስ አሰራርን ከማስተካከል ጀምሮ መንግሥት ከዘረጋው የነዳጅ አቅርቦትና ስርጭት ሂደት ውጭ በሚፈጽሙ አካላት ላይ አስተዳደራዊና ህጋዊ እርምጃ ይወሰዳልም ተብሏል፡፡
2.1K views16:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-16 19:02:31
ዋልታ ምሽት በቀጥታ ግንቦት 8/2014

https://www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate/videos/703431497663493
1.9K views16:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-16 18:24:30
ከ300 በላይ የህንድ ኢንቨስተሮች በኢትዮጵያ ሥራ መጀመራቸው ተገለጸ

ግንቦት 8/2014 (ዋልታ) በኢትዮጵያ ከሚገኙ ከ650 በላይ የህንድ ኢንቨስተሮች መካከል ከ300 በላይ የሚሆኑት ሥራ መጀመራቸውን በኢትዮጵያ የህንድ አምባሳደር ሽሪን ሮበርት ተናገሩ።

አምባሳደሩ ከሠመራ ዪኒቨርሲቲ አመራርና ማኅበረሰብ አባላት እንዲሁም ከህንዳውያና መምህራኖች ጋር ተወያይተዋል።

በውይይቱ ላይ እንደገለጹት፤ ረጅም ጊዜ የቆየውን የኢትዮጵያንና የህንድ ሁለንተናዊ ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር እየተሰራ ይገኛል።

በኢትዮጵያ በኢንቨስትመንት መስክ የተሰማሩ የህንድ ባለሃብቶች ከ75 ሺሕ በላይ ለሚሆኑ ሰዎች የሥራ ዕድል መፍጠራቸውን የገለጹት አምባሳደሩ፤ አገራቸው በኢትዮጵያ በተለየያዩ ማኅበራዊ፣ ባህላዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት መስክ ንቁ ተሳትፎ እያደረገች እንደምትገኝ ገልጸዋል።

የትምህርት ልማት ዘርፉ ሌላኛው የኢትዮ-ህንድ ወሳኝ የግንኙነት መስክ መሆኑን ገልጸው፤ የከፍተኛ ትምህርታቸውን በህንድ እየተከታተሉ ከሚገኙ በርካታ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች በተጓዳኝ ህንድ በየአመቱ ለ50 ተማሪዎች ነጻ-የትምህርት ዕድል ትሰጣለች ብለዋል።

በሠመራ ዩኒቨርሲቲ የሚያስተምሩ 80 ህንዳውያንን ጨምሮ በርካታ ህንዳውያን መምህራን በኢትዮጵያ ውስጥ ባሉ የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች እያገለገሉ እንደሚገኙ ጠቅሰዋል።

የሠመራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት መሀመድ ኡስማን (ዶ/ር) በበኩላቸው ህንድ የኢትዮጵያን የትምህርት መስክ በመደገፍ የእውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግር በማድረግ ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
2.2K views15:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-16 18:13:50
አዋሽ ባንክ የሥራ ፈጠራ ውድድር አስጀመረ

ግንቦት 8/2014 (ዋልታ) አዋሽ ባንክ "ታታሪዎቹ" የተሰኘ የሥራ ፈጠራ ውድድር አስጀምሯል፡፡

ባንኩ የሥራ ፈጠራ ሃሳብ ይዘው ለሚመጡ ሥራ ፈጣሪዎች የፋይናንስ ድጋፍ እንደሚያደርግ አስታውቋል፡፡

በሁሉም ክልሎች ለሚገኙ የጥቃቅን፣ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የሙያ ክህሎት ስልጠና ላይ ዋነኛ ትኩረቱ አድርጎ ይሰራልም ተብሏል፡፡

"ታታሪዎቹ" የሥራ ፈጠራ ውድድርም የሥራ ፈጠራ ሃሳብ ኖሯቸው በፋይናንስ እጥረት ተግባራዊ ማድረግ ላልቻሉ የሥራ ፈጣሪዎች ዕድል የሚሰጥ መሆኑን የባንኩ ፕሬዝዳንት ጸሐይ ሽፈራው ገልጸዋል፡፡

ውድድሩ በዋናነት የክህሎት ስልጠና፣ መነሻ ካፒታልና ዘላቂ ብድር የሚመቻችበት መሆኑንም ነው የጠቀሱት፡፡

በውድድሩ የመጀመሪያ ዙር 1 ሺሕ እጩዎችን በመቀበል በተዘጋጁ የስልጠና ማዕከላት የክህሎት ስልጠና በመስጠት የሚጀመር ሲሆን 100 ሰልጣኞች ባቀረቡት የሥራ ፈጠራ ሃሳብ ተመዝነው ወደ ቀጣዩ ዙር የሚያልፉ ይሆናል፡፡

https://www.facebook.com/489211707826282/posts/pfbid0WjV1AKwL4nUhGo4PxMSMCh5vnfK6sqUJPbbDckYAcXdKfgWEUc5B17BsKhmvYHKBl/
2.1K views15:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-16 16:46:03
የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን በሴካፋ ዋንጫ ለሚሳተፉ 23 ተጨዋቾች ጥሪ አቀረበ

ግንቦት 8/2014 (ዋልታ) የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን በአሰልጣኝ ፍሬው ሀይለገብርኤል በኩል በዩጋንዳ አስተናጋጅነት ለሚካሄደው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ ለሚሳተፉ 23 ተጨዋቾች ጥሪ አቅርቧል፡፡

በዚህም፡-

ግብ ጠባቂ
ታሪኳ በርገና ፣ የምወድሽ ይርጋሽዋ እና ቤቴሌሄም ዮሀንስ

ተከላካይ
ቤቴሌሄም በቀለ፣ ብዙየሁ ታደሰ፣ አሳቤ ሞሶ፣ ቅድስት ዘለቀ፣ ናርዶስ ጌትነት እና ብርቄ አማረ

አማካይ
ኝቦኝ የን፣ እመቤት አዲሱ፣ ገነት ሀይሉ፣ መዓድን ሳህሉ፣ መሳይ ተመስገን፣ ብርቱካን ገብረክርስቶስ

አጥቂ
ረዴት አስረሳኸኝ፣ አረጋሽ ከልሳ፣ ሎዛ አበራ፣ ረሂማ ዘርጋው፣ ሴናፍ ዋቁማ፣ አርየት ኦዶንግ፣ ቱሪስት ለማ እና ንግስት በቀለ መመረጣቸውን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በማኅበራዊ ትስስር ገጹ አስታውቋል፡፡
2.5K viewsedited  13:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-16 16:43:03
1,040 ኢትዮጵያዊያን ከሳዑዲ ዓረቢያ ተመለሱ

ግንቦት 8/2014 (ዋልታ) በዛሬው ዕለት በሦስት ዙር በተከናወነ ዜጎችን ከሳዑዲ ዓረቢያ የመመለስ ሥራ 1 ሺሕ 40 ኢትዮጵያዊያንን ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል፡፡

ከተመላሾች ውስጥም 303 ሴቶች ሲሆኑ 90 የሚሆኑት ደግሞ ህጻናት መሆናቸው ተገልጿል፡፡

ለተመላሽ ዜጎች ተገቢውን ድጋፍ እና እንክብካቤ በማድረግ ወደ ተዘጋጁላቸው የማቆያ ማዕከላት እንዲሄዱ መደረጉም ተጠቁሟል፡፡

እስካሁን ድረስ በተከናወነው ዜጎችን የመመለስ ሥራ ቁጥራቸው ከ23 ሺሕ 640 በላይ ኢትዮጵያዊያንን መመለስ እንደተቻለ ከሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

ለፈጣን መረጃዎች፦
ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW
2.2K views13:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-16 16:38:07
ሊጉ የፕሮግራምና መተዳደሪያ ደንብ ማሻሻያ አደረገ

ግንቦት 8/2014 (ዋልታ) የብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ሊግ የፕሮግራም እና መተዳደሪያ ደንብ ማሻሻያ ማድረጉን አስታውቋል።

ሊጉ ጉባኤ ከማድረግ ባለፈ ተጨባጭ ለውጥ ለማምጣት ዝግጅት ማድረጉን ያስታወቀ ሲሆን የፕሮግራም እና የመተዳደሪያ ደንብ ማሻሻያ ማድረጉንም ገልጿል፡፡

የብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ሊግ ፕሬዝዳንት መሰረት መስቀሌ በሊጉ በቀጣይ ሦስት ወራት የአረንጓዴ ልማት ሥራዎች ላይ ትኩረት በማድረግ 2 ነጥብ 2 ቢሊየን ችግኞችን ለመትከል እቅድ ተይዞ እየተሠራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

የሊጉ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላትም የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማረጋገጥ ውይይት ተደርጎ የአሰራር መመሪያ መፅደቁን አንስተዋል።

በቀጣይ ለሚካሄደው ጉባኤ ቅድመ ዝግጅት አቅጣጫ መቀመጡንም ጠቁመዋል።

በሱራፌል መንግሥቴ

ለፈጣን መረጃዎች፦
ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW
2.0K views13:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ