Get Mystery Box with random crypto!

AddisWalta - AW

የቴሌግራም ቻናል አርማ waltatveth — AddisWalta - AW A
የቴሌግራም ቻናል አርማ waltatveth — AddisWalta - AW
የሰርጥ አድራሻ: @waltatveth
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 45.24K
የሰርጥ መግለጫ

This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.
For more updates please visit https://shorturl.at/ehosX https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 341

2022-05-15 21:59:46
ከንቲባዋ የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችን በመዲናዋ የሚገኙ ሜጋ ፕሮጀክቶችን አስጎበኙ

ግንቦት 7/2014 (ዋልታ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችን የአብርሆት ቤተመጻሕፍት፣ መስቀል አደባባይ፣ የማዘጋጃ ቤት ህንፃ እድሳትን ጨምሮ ሌሎችንም አገልግሎት እየሰጡ ያሉና ግንባታቸው በመጠናቀቅ ላይ ያሉ ሜጋ ፕሮጀክቶችን አስጎብኝተዋል።

እየተጎበኙ ያሉ ሜጋ ፕሮጀክቶች በለውጡ አመራር በአጭር ጊዜ የግንባታ ሥራቸው ተጠናቆ ለሕዝባዊ አገልግሎት ክፍት የተደረጉ መሆናቸው የተገለፀ ሲሆን አመራሩ በዚሁ ልክ በትኩረት ሥራዎችን መጀመርና ማጠናቀቅን ባሕል ማድረግ አለበት ተብሏል።

በጉብኝቱ ወቅት አስተያየታቸውን የሰጡት ከንቲባ አዳነች አቤቤ ብልፅግና ሰው ተኮር ነው የምንለው በርካቶችን ተጠቃሚ ማድረግ የቻሉ ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ ያደረገ በመሆኑ ነው ብለዋል፡፡

የምገባ ማእከላት አሁን ካሉት ስድስት በተጨማሪ አስተዳደሩ ሌሎች ስድስት በቅርብ ጊዜ ገንብቶ አጠናቆ አስራ ሁለት የምገባ ማእከላት ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ገልፀው የትኛውም የኑሮ ጫና ያለበት በቀን አንድ ጊዜ መመገብ የማይችል ማንኛውም የከተማችን ነዋሪ ሄዶ የሚመገብባቸው ይሆናሉ ሲሉም ገልጸዋል፡፡

በተጨማሪም የከተማው ሕዝብ ካስተባበሩት መልካም ሕዝብ መሆኑን አዲስ አበባ ማሳያ ናት ያሉ ሲሆን ባለፉት ወራት ከኅብረተሰቡ አንድ ቢሊየን ብር በማእድ ማጋራት ሰብስበን ኅብረተሰቡ መድረስ የሚችልበት ሲሆን ወደ ሰባት ቢሊየን የሚሆን ደግሞ በድርቁም ለተፈናቀሉም በማዋጣት አብሮነቱን ያረጋገጠበት ጭምር ነው ብለዋል፡፡ https://www.facebook.com/489211707826282/posts/5428583513889052/
1.5K views18:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 19:26:45
የ"መቀመጭት" ተራራ በአቡነ ኤርምያስ ስም ተሰየመ

ግንቦት 7/2014 (ዋልታ) ወልድያ ከተማ አስተዳደር የ"መቀመጭት ተራራን" "አቡነ ኤርምያስ ተራራ" ብሎ መሰየሙን አስታውቋል።

የተራራውን ስያሜ የሰጠው ከተማ አስተዳደሩ አቡነ ኤርምያስ ያደረጉትን ውለታ በማሰብ እና ተያያዥ የልማት የቤት ሥራዎች ለመስጠት መሆኑን ገልጿል።

የዕፅዋት ሳይንስ መድኃኒት ቅመማ ጋር ተያይዞ ለምርምር የሚሆኑ ሀገር በቀል ዕፅዋቶች በስፋት የሚገኙበት ተራራ በመሆኑ የጥንት መጻሕፍትን በመተርጎም የሚመራመሩ ሊቃውንትን በተራራው በማሰማራት የምርምር ማዕከል እንደሚያደርጉት ታላቅ ተስፋ ስለተጣለባቸው ስያሜው የተሰጠበት አንደኛው ምክንያት እንደሆነ ተገልጿል።

ከከተማዋ መስፋፋት ጋር ተያይዞ እየተስፈፋ የመጣን የደን መራቆት ለመግታት ተራራው በርሳቸው ስም መሰየሙ ደኑ ይበልጥ ተከብሮ እንዲቀጥል ትልቅ አቅም መሆኑን በማመመን እንደሆነም ነው የከተማ አስተዳደሩ የገለፀው።

በሦስተኛ ደረጃ ብፁዕነታቸው ከአሸባሪው ሕወሓት ወረራ በኋላም ከቆላ እስከ ደጋው እምነት ሳይለዩ በመልሶ ግንባታ በሚያደርጉት መልካም ሥራ ሁሉንም በማስተባበር አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ሙሉ እምነት በማሳደር "አቡነ ኤርምያስ ተራራ" በማለት ተራራው በስማቸው መሠየሙ ተጠቁሟል።

ተራራው ከፍ ያለ ዕይታ ባላቸው አባት ስም መሰየሙ ክብሩ ለተሰየመለት ሰው ብቻ ሳይሆን የብፁዕነታቸውን አገልግሎት ለደረሰውና ለመላው የወልድያና አካባቢው ሕዝብ እና ከተማ አስተዳደሩ ጭምር ነው ሲል ወልድያ ከተማ ኮምዩኒኬሽን አስታውቋል።

አቡነ ኤርምያስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሰሜን ወሎ፣ የደቡብ ወሎና በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የኦሮሞ ብሔረስብ አስተዳደር ሊቀ ጳጳስ ናቸው።
2.5K views16:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 19:12:45
ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሀመድ በደጋህሌ ለገበያ የቀረበ የፍራፍሬ ምርት ጎበኙ

ግንቦት 7/2014 (ዋልታ) የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሀመድ በፋፈን ዞን ደጋህሌ ከተማ በግብርና ሥራ የሚተዳደሩ ዜጎች ለገበያ ያቀረቡትን ፍራፍሬ ጎበኝተው አርሶ አደሮቹን አበረታተዋል።

የደጋህሌ ከተማ ለግብርና ምቹ ከሆኑ የክልሉ ከተሞች አንዷ ስትሆን አርሶአደሮች የሚያመርቱትን ፍራፍሬ ለአከባቢው በተለይ ለጅግጅጋ ከተማ ገበያ ያቀርባሉ።

በጉብኝታቸውም የክልሉ መንግሥት ለግብርና ልማት ልዩ ትኩረት እንደሰጠና በዘርፉ ለተሰማሩ አርሶአደሮች ድጋፍ እንደሚደረግ ገልጸዋል።

አክለውም፤ አርሶአደሮቹ በምግብ እራስን ለመቻል የሚደረገው ጥረት አካል እንደሆኑ ገልፀው፣ መንግሥት ከምርት እስከ ገበያ ትስስር ያለውን ሂደት እንደሚያመቻች ተናግረዋል።

የክልሉ መንግሥት በ2015 የምርት ዘመን ከ20 ሚልየን ኩንታል በላይ ምርት ለማምረት ማቀዱን የክልሉ መንግሥት ኮሙዩኒኬሽን መረጃ አመላክቷል።

ለፈጣን መረጃዎች፦
ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW
ቴሌግራም https://t.me/WALTATVEth
ዩቲዩብ https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured
ቲዊተር https://twitter.com/walta_info
አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን
2.2K views16:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 19:06:51
ማታ 1፡00 ዜና በቀጥታ ከዋልታ ቴቪ ግንቦት 7/2014

https://fb.watch/d0TCqiAD3K/
2.0K viewsedited  16:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 18:22:12
በቦቆጂ ለመጀመሪያ ጊዜ ታላቁ ሩጫ ተካሄደ

ግንቦት 7/2014 (ዋልታ) "ኢትዮጵያ ትሮጣለች” በሚል መሪ ቃል በአርሲ ዞን ቦቆጂ ከተማ ለመጀመሪያ ጊዜ ታላቁ ሩጫ ተካሄደ።

በመርኃ-ግብሩ የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ ሰላማዊት ዳዊት፣ የኦሮሚያ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ሰዓዳ ኡስማን ጨምሮ የተለያዩ የዞንና የከተማ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

በአዋቂዎች 7 ኪሎ ሜትር ሩጫ፣ 15 ኪሎ ሜትር ብስክሌት ውድድርና የህጻናት ሩጫ ተካሂዷል።

በአዋቂ ወንዶች የ7 ኪሎ ሜትር ውድድር አትሌት ደጀኔ ኃይሉ በቀዳሚነት ሲያጠናቅቅ አትሌት ቱሉ አበበ ሁለተኛ፣ አትሌት ብርሃኑ ቱሉ ደግሞ ሶስተኛ ደረጃ ይዘው አጠናቀዋል።

በሴቶች 7 ኪሎሜትር ውድድር ደግሞ አትሌት መሰረት ሂርጳ በአንደኝነት አጠናቃለች።

ቀነኒ ዲቻ እና ሃዊ ጉደታ እንደየ ቅደም ተከተላቸው ሁለተኛ እና ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን ጨርሰዋል።

የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ ሰላማዊት ዳዊት፤ የውድድሩ ዓላማ የስፖርት ቱሪዝምን ለማበረታታት መሆኑን ተናግረዋል።

በቆጂ ኢትዮጵያን በተለያዩ ዓለም ዐቀፍ ውድድሮች ያስጠሩ ጀግኖችን ያፈራች ከተማ መሆኗን አስታውሰው ውድድሩ መካሄዱ ከተማዋን የበለጠ ለማስተዋወቅና የቱሪዝም ተጠቃሚነት ለማሳደግ ይረዳል ብለዋል።

እንደ ሚኒስትር ዴኤታዋ ገለጻ መርኃ-ግብሩ ቱሪዝምን ከማሳደግ በተጨማሪ ታዳጊ ስፖርተኞችን የሚያበረታታ መሆኑን ገልጸዋል።

ታላቁ ሩጫ በቦቆጂ ሲደረግ የመጀመሪያ መሆኑን ገልጸው፤ በቀጣይ በየዓመቱ ለማካሄድ እንደታቀደም ጠቁመዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
2.4K views15:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 16:34:20
ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች የማዕድን ሚኒስቴርን የሪፎርም ሥራዎች ተመለከቱ

ግንቦት 7/2014 (ዋልታ) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ የማዕድን ሚኒስቴርን የሪፎርም ሥራዎች ተመልክተዋል።

ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎቹና አመራሮቹ በሚኒስቴሩ የሚገኘውን የማዕድን ጋለሪ መመልከታቸውን የማዕድን ሚኒስትሩ ታከለ ኡማ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት አስታውቀዋል።

ሚኒስትሩ የሥራ ኃላፊዎቹ በተቋሙ ለነበራቸው ቆይታና ለሰጡት ገንቢ አስተያየት ምስጋና ማቅረባቸውንም ጠቁመዋል።

ለፈጣን መረጃዎች፦
ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW
2.9K views13:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 14:25:14
ከ300 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ ጀነራል ሆስፒታል ሊገነባ ነው

ግንቦት 7/2014 (ዋልታ) በምስራቅ ሐረርጌ ዞን ኮምቦልቻ ወረዳ ከ300 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ በትውልደ ኢትዮጵያዊያን ዳያስፖራዎች የሚገነባ መልቲ ጀነራል ሆስፒታል የመሰረት ድንጋይ ተቀመጠ።

ፕሮጀክቱ በ1 ነጥብ 6 ሄክታር መሬት ላይ የሚያርፍ ሲሆን ወጪው ሙሉ በሙሉ በውጭ ሀገራት በሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን የሚሸፈን ነው።

በወረዳው ለሚገነባው ሆስፒታል የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ጀማል ዪስፍ (ዶ/ር)፣ የኮምቦልቻ ወረዳ አስተዳደር አልዪ ኢብራሂም እና የዲያስፖራ ተወካይ ፈረሃን አህመድ የመሰረት ድንጋዩን አስቀምጠዋል።

በእለቱ ንግግር ያደረጉት የዲያስፖራ ተወካይ ፈርሀን አህመድ ማኅበረሰቡ የተሟላ ጤና አገልግሎት ለማግኘት የሚደርስበትን እንግልት ከግምት በማስገባት ሆስፒታሉን ለመገንባት መነሳሳታቸውን ገልፀዋል።

አያይዘውም ዲያስፖራው ወገኑን ለመርዳት በአሁኑ ወቅት ቁርጠኛ አቋም መያዙን አመልክተዋል።

የሀሮማያ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ጀማል ዩሱፍ (ዶ/ር) ሆስፒታሉ በርካታ ከፍተኛ ህክምና ለሚፈልጉ ህሙማን አገልግሎት የሚሰጥበት እንደሆነ ገልፀዋል።

ሐረር ከተማ የሚገኘው የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የህይወት ፋና ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል 6 ሚሊየን የሚደርስ ተጠቃሚ መኖሩን ገልፀው ሆስፒታሉ መገንባቱ ጫናውን የሚቀንስ ይሆናል ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

የኮምቦልቻ ወረዳ አስተዳዳሪ አሊዪ አብራሂም በበኩላቸው ዲያስፖራው "ለሀገሬ ምን አረኩኝ" በሚል ስሜት በመነሳሳት የወገኑን ችግር ለመቅረፍ ሆስፒተሉን ለመገንባት ወደ ሥራ በመግባታቸው አመስግነዋል።

በመሆኑም ፕሮጀክቱ ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ ድረስ የማኅበረሰቡ ርብርብ አስፈላጊ በመሆኑ ማኅበረሰቡ የበኩሉን ትብብር እንዲያደርግ ጠይቀዋል።
359 views11:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 12:39:00
ርዕሰ መስተዳደሩ በባሕርዳር የተገነቡና በሥራ ላይ የሚገኙ ኢንቨስትመንቶችን ጎበኙ

ግንቦት 7/2014 (ዋልታ) የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ/ር) እና የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በባሕርዳር ከተማ የሚገኙ በሀገር ውስጥና በውጭ ባለሀብቶች የተገነቡና በሥራ ላይ የሚገኙ ኢንቨስትመንቶችን ጎብኝተዋል።

የብልፅግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ግርማ የሸጥላና የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ እንድሪስ አብዱ በጉብኘቱ ላይ ተገኝተዋል።

የተጎበኙት ኢንቨስትመንቶች በአግሮ ኢንዱስትሪው ዘርፍ የባሕር ዳር ፍሬሽ ብሉቨሪ ኢንቨስትመንት፣ የባዮ ፍሬሽ የአበባ ምርት እና በሀገር ውስጥ ባለሀብቶች ተገንብተው ሙሉ በሙሉ ማምረት የጀመሩትን አፍሪካ ብረታ ብረት ፋብሪካና ሙሌ ዘመናዊ የእንሰሳት መኖ ማቀነባበሪያና አማር የሲሚንቶ ከረጢት ማምረቻ ፋብሪካዎች ናቸው።

ርዕሰ መስተዳድሩ በጉብኝታቸው ማጠቃለያ የክልሉ መንግሥት ኢንቨስትመንትን በማስፋፋትና ባለሀብቶችን በመሳብ የክልሉን እምቅ ሀብት ጥቅም ላይ ለማዋልና ለብዙ ወጣቶች የሥራ ዕድል በመፍጠር ድህነትን ለማስወገድ ጥረቱን አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ተናግረዋል፡፡

አክለውም ባለሀብቶች የሚገጥማቸውን ችግር ለመፍታትና አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ ለማድረግ የክልሉ መንግሥት ቁርጠኛ እንደሆነ መግለጻቸውን ከክልሉ ኮሙዩኒኬሽን የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

ለፈጣን መረጃዎች፦
ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW
1.3K views09:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 12:09:15
ከተማ ዐቀፍ የማስ ስፖርት እንቅስቃሴ ተካሄደ

ግንቦት7/2014 (ዋልታ) "አዲስ አበባ የሰላምና የአብሮነት ከተማ" በሚል መሪ ቃል ከተማ ዐቀፍ የማስ ስፖርት እንቅስቃሴ ዛሬ ተካሂዷል።

ዛሬ በተካሄደው ከተማ ዐቀፍ የማስ ስፖርት እንቅስቃሴ ላይ በመላው አዲስ አበባ በ11ዱም ክፍለ ከተሞች በተዘጋጁ ቦታዎች ከማለዳው 12:00 ሰዓት ጀምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ ነዋሪዎች፣ ስፖርተኞችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተፋትፈዋል፡፡

አዲስ አበባ የሰላም፣ የፍቅር፣ የመቻቻልና የአብሮነት ከተማ መሆኗን የሚያመለክቱ መልዕክቶችም ተላልፈዋል።

የአዲስ አበባ የብልፅግና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ መለሰ አለሙን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በየክፍለ ከተሞቹ መድረክ ላይ ተገኝተዋል።

አካል ብቃት እንቅስቃሴ ማስ ስፖርት በኅብረተሰቡ ዘንድ ባህል ሆኖ በመምጣቱ በየሳምንቱ ተጠናክሮ በድምቀት እና በአንድነት እንደሚቀጥልም በመድረኩ ተጠቁሟል።

ከተማ ዐቀፉን የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ያስተናገደው የቦሌ ክፍለ ከተማ ሲሆን በቀጣይ ጉለሌ አስተናጋጁ ክፍለ ከተማ እንደሆነ የአዲስ አበባ ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ አሳውቋል፡፡

በሀብታሙ ገደቤ

ለፈጣን መረጃዎች፦
ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW
1.3K views09:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 12:04:00
የቀን 6፡00 ዜና በቀጥታ ከዋልታ ቴቪ ግንቦት 07/2014
https://fb.watch/d0uS9VsM2_/
1.2K views09:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ