Get Mystery Box with random crypto!

AddisWalta - AW

የቴሌግራም ቻናል አርማ waltatveth — AddisWalta - AW A
የቴሌግራም ቻናል አርማ waltatveth — AddisWalta - AW
የሰርጥ አድራሻ: @waltatveth
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 45.24K
የሰርጥ መግለጫ

This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.
For more updates please visit https://shorturl.at/ehosX https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 346

2022-05-13 17:06:15
የህግ የበላይነትና የሃይማኖት ጽንፈኝነት ላይ ያተኮረ ውይይት በቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ተካሄደ

ግንቦት 5/2014 (ዋልታ) ትኩረቱን በሀገር ሰላም፣ የኑሮ ውድነት፣ ሥራ አጥነት፣ የህግ የበላይነት እና የሃይማኖት ጽንፈኝነት ላይ ያደረገ ውይይት በቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ዛሬ ተካሂዷል፡፡

ውይይቱ "የዜጎች ቀጥተኛ ሚና ለሁለንተናዊ ብልጽግና " በሚል መርህ ሃሳብ የተካሄደ ሲሆን የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር ካውንስል አባላት፣ መምህራን እና የአስተዳደር ሰራተኞች ተሳትፈውበታል፡፡

የውይይት መድረኩን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የመንግሥት ዋና ተጠሪ ፀጋዬ ማሞ እና የዩኒቨርስቲው ፕሬዚዳንት ጴጥሮስ ወ/ጊዮርጊስ (ዶ/ር) የመሩት ሲሆን የመንግሥት ዋና ተጠሪው የውይይት መነሻ ሰነድ አቅርበው ውይይት ተካሂዶበታል።

የክልሉ መንግሥት ዋና ተጠሪ ፀጋዬ ፤ የዜጎችን ሰላምና ደኅንነት ማረጋገጥ በዋናነት የመንግሥት ኃላፊነት ቢሆንም ሁሉም ዜጋ ለዘለቄታዊ ሰላም የበኩሉን አስተዋጽኦ ማበርከት እና ኅብረ ብሔራዊ ወንድማማችነት እና እህትማማችነት ማጠናከር እንዳለበት መግለጻቸውን ከዩኒቨርሲቲው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
1.5K views14:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 17:02:48
10ኛው ሀገር ዐቀፍ የምርምር ኮንፈረንስ ተካሄደ

ግንቦት 5/2014 (ዋልታ) 10ኛው ሀገር ዐቀፍ የምርምር ኮንፈረንስ “በተግባራዊ ምርምር እና የፈጠራ ሥራዎች የማኅበረሰብን የመቋቋም አቅም መገንባት” በሚል መርህ በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት ተካሄደ።

በኮንፍረንሱ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የተውጣጡ ምሁራን፣ የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማሌዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተሳትፈዋል።

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ምርምርና ማኅበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት መስፍን ቢቢሶ (ዶ/ር) ዩኒቨርሲቲው ጥራት ያለውን ትምህርት ተደራሽ በማድረግ፣ ችግር ፈቺ የጥናትና ምርምር ሥራዎችን በማካሄድ እንዲሁም የቴክኖሎጂ ሽግግርና ስርፀትን በማስፈን የማኅበረሰብ አገልግሎትን ተደራሽ ማድረጉን ገልፀዋል፡፡

በተያዘው ዓመት ለምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ሥራዎች 49 ሚሊየን፣ ለማኅበረሰብ አገልግሎት 36 ሚሊየን እንዲሁም ከተለያዩ ፕሮጀክቶች በተገኘው 32 ሚሊየን ብር 155 የጥናትና ምርምር፣ 10 የቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲሁም 54 የማኅበረሰብ አግልግሎት ሥራዎች ተከናውነዋል ነው ያሉት።

የዩኒቨርሲቲው ሥራ አመራር ቦርድ አባል እና የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አክሊሉ ለማ ጥልቀትና ጥራት ያለው ጥናትና ምርምር ሥራዎች ካልተሰሩና የተሰሩትም ወደ ተግባር ተቀይረው ውጤት ካላመጡ በሀገር ደረጃ በማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ዘርፎች አዎንታዊ ለውጥን ማምጣት አይቻልም ብለዋል፡፡

ዓመታዊ የጥናት እና ምርምር ኮንፈረንሱ ልምድና ተሞክሮዎችን ለመለዋወጥ ያስችላል የተባለ ሲሆን ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የመጡ ምሁራን የምርመር ሥራዎቻቸውን አቅረበዋል።

መማር ይበልጣል (ከወላይታ ሶዶ)

ለፈጣን መረጃዎች፦
ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW
1.5K views14:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 16:30:38
1 ሺሕ 154 ኢትዮጵያዊያን ከሳዑዲ አረቢያ ተመለሱ

ግንቦት 5/2014 (ዋልታ) ዛሬ በሦስት ዙር በተከናወነ ዜጎችን ከሳዑዲ አረቢያ የመመለስ ሥራ 1 ሺሕ 154 ኢትዮጵያዊያንን ወደ ሀገራቸው መመለሳቸው ተገለጸ፡፡

ከተመላሾቹ ውስጥ 157 ሴቶች ሁለት ህጻናትና 995 ወንዶች መሆናቸው ታውቋል፡፡

ለተመላሽ ዜጎችም ተገቢውን ድጋፍ እና እንክብካቤ በማድረግ ወደ ተዘጋጀላቸው የማቆያ ማእከላት እንዲሄዱ መደረጉን ከሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ አመላክቷል፡፡

እስካሁን ድረስ በተከናወነው ዜጎችን የመመለስ ሥራ ከ22 ሺሕ 600 በላይ ኢትዮጵያዊያንን መመለስ መቻሉም ተመላክቷል፡፡

ለፈጣን መረጃዎች፦
ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW
458 views13:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 16:19:02
ዩኒቨርሲቲው ለአረጋውያንና አካል ጉዳተኞች ተሃድሶ ድርጅት ድጋፍ አደረገ

ግንቦት 5/2014 (ዋልታ) የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ለአብርሃ ባህታ የአረጋውያንና አካል ጉዳተኞች ተሃድሶ ድርጅት የመንቀሳቀሻ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ፡፡
የተሃድሶ ድርጅቱ በሀረር የሚገኝ ሲሆን 2 ሚሊየን ብር ግምት ያለው የአካል ጉዳተኞች መንቀሳቀሻ ቁሳቁስ ድጋፍ ነው የተበረከተለት፡፡

የዩኒቨርስቲው ፕሬዚዳንት ተወካይ እና የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት ጄይላን ወሊይ (ፕ/ር) በድጋፍ ርክክቡ ወቅት እንዳሉት፤ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ከአሜሪካው ክሪስቲያን ሪሊፍ ሰርቪስ ጋር በመተባበር ድጋፉን አበርከተዋል፡፡

በድርጅቱ ለሚገኙ አረጋውያንና አካል ጉዳተኞች የሚያደርገውን ድጋፍ የኒቨርሲቲው አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተናግረዋል፡፡

የሀረሪ ክልል ሰራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ምስራቅ እሸቴ በበኩላቸው የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ከዚህ ቀደም የተለያዩ ድጋፎችን ሲያደርግ መቆየቱን ጠቁመው፤ አሁንም ላደረገው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል፡፡

https://www.facebook.com/489211707826282/posts/pfbid02anHLyuADGbW1gtPFbJbZcNv6oXcfRxjbz1iCXPncVDt226Wc6DySLzdga5st6hNhl/
614 views13:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 16:18:23
ኢቢሲ 10 ሺሕ የሚጠጉ መጻሕፍትን ለአብርሆት ቤተ መጻሕፍት አስረከበ

ግንቦት 5/2014 (ዋልታ) የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) 10 ሺሕ የሚጠጉ መጻሕፍትን ለአብርሆት ቤተ መጻሕፍት አስረከበ፡፡

ኢቢሲ በመጀመሪያ ዙር ያሰባሰበውን መጻሕፍት ለአብርሆት ቤተ መጻሕፍት ያስረከበ ሲሆን በቀጣይም መጻሕፍትን በማሰባሰብ ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል፡፡

በርክክብ ሥነሥርዓቱ የኢቢሲ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ፍስሃ ይታገሱ እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባህል፣ ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ሂሩት ካሳው (ዶ/ር) ተገኝተዋል፡፡

ለንባብ ባህል መጎልበት የንባብ ማዕከላት መስፋፋት ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው የሚገለጽ ሲሆን ከዚህ አኳያ በአዲስ አበባ ለተገነባው የአብርሆት ቤተ-መጻሕፍት በሀገር ዐቀፍ ደረጃ የአንድ ሚሊዮን የመጻሕፍት ማሰባሰቢያ መርኃ ግብር እየተካሄደ ይገኛል፡፡

በብርሃኑ አበራ

ለፈጣን መረጃዎች፦
ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW
520 views13:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 15:52:41
የውጭ ሀገር ዜግነት ባለው ግለሰብ መኖሪያ ቤት የተለያዩ ሀገራት ገንዘቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ

ግንቦት 5/2014 (ዋልታ) በህገወጥ ተግባር ላይ በተሰማራ አንድ የውጭ ሀገር ዜግነት ባለው ግለሰብ መኖሪያ ቤት ውስጥ በተደረገ ብርበራ ከ5 ሺሕ በላይ የአሜሪካ ዶላርን ጨምሮ የተለያዩ ሀገራት ገንዘቦች እና ከ71 ሺሕ ብር በላይ በቁጥጥር ስር መዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡

ግለሰቡ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ልዩ ቦታው 24 ኮንዶሚኒየም ጀርባ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ባለ 3 ወለል ፎቅ ተከራይቶ የሚኖር ነው ተብሏል፡፡

ተጠርጣሪው ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡ የውጭ ሀገር ዜጎችን እየተቀበለና በመኖሪያ ቤቱ ውስጥ አልጋ እያከራየ የውጭ ሀገር ገንዘብ እንደሚቀበል፣ ከሀገሩ ሴቶችን እያስመጣ ለወሲብ ንግድ እንደሚያሰማራ እና በቤቱ ውስጥ ቁማር እንደሚያጫውት ከኅብረተሰቡ ጥቆማ መምጣቱን ፖሊስ ገልጿል፡፡

የኅብረተሰቡን ጥቆማ መነሻ በማድረግ ፖሊስ እና የብሔራዊ መረጃ እና ደኅንነት ባደረጉት ክትትል ግንቦት 4 ቀን 2014 ዓ.ም በግለሰቡ መኖሪያ ቤት በህግ አግባብ በተደረገ ብርበራ በመኝታ ክፍል ውስጥ 5 ሺሕ 335 የአሜሪካ ዶላር፣ 380 ዩሮ፣ 1 ሺሕ 435 የቻይና ዩዋን እና ሌሎች የተለያዩ ሀገራት ገንዘቦችን ጨምሮ 71 ሺሕ 635 የኢትዮጵያ ብር በቁጥጥር ስር መዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ መረጃ አመላክቷል፡፡

ለፈጣን መረጃዎች፦
ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW
855 views12:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 15:34:38
ቢሮው አዲስ የታሪፍ ማሻሻያ ይፋ እስኪደረግ ድረስ የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች በነባሩ ታሪፍ እንዲሰሩ አሳሰበ

ግንቦት 5/2014 (ዋልታ) በአዲስ አበባ የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ሁሉም ተቋማት፣ የታክሲና ሀይገር ባለንብረቶች ማኅበራትና ግለሰቦች አዲስ የትራንስፖርት ታሪፍ ማሻሻያ ይፋ እስኪደረግ ድረስ በነባሩ የክፍያ ታሪፍ መሰረት አገልግሎት መስጠት እንዳለባቸው የአስተዳደሩ የትራንስፖርት ቢሮ አሳሰበ፡፡

በቢሮው የኦፕሬሽን ዘርፍ ምክትል ኃላፊ ይርጋዓለም ብርሃኔ፤ በመዲናዋ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ሁሉም ተቋማት፣ የታክሲና ሀይገር ባለንብረቶች ማኅበራትና ግለሰቦች አዲስ የትራንስፖርት ታሪፍ ማሻሻያ ይፋ እስኪደረግ ድረስ በነባሩ የክፍያ ታሪፍ መሰረት ልክ እንደከዚህ ቀደሙ በሙሉ አቅማቸው አገልግሎት መስጠት እንዳለባቸው ገልጸዋል፡፡

ከነዳጅ ዋጋ ማስተካከያ ጋር ተያይዞ አገልግሎቱን በተገቢው መንገድ የማይሰጡና ኅብረተሰቡን ለተለያዩ እንግልቶችና አላስፈላጊ ወጪዎች የሚዳርጉ ማንኛውም የሕዝብ ትራንስፖርት ሰጪ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አሳስቧል፡፡

ቢሮው አገልግሎት ሰጪዎቹ ወደ ሥራ እንዲገቡ እና በማይገቡትም ላይ አስፈላጊውን እርምጃ ይወስዳልም ብለዋል፡፡

ከዚህ ጋር ተያይዞ ያለምንም ቅድመ ሁኔታና በህጋዊ መንገድ ለተቋሙ ሳያሳውቁ ከስራ ገበታቸው የወጡት የሸገር ድጋፍ ሰጪ አውቶቡስ አገልግሎት ሰጪ ማኅበራትም በገቡት ውል መሰረት መብታቸውን እየጠየቁ አገልግሎት መስጠት እንዳለባቸው ኃላፊው አስገንዝበዋል፡፡
979 views12:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 15:11:26
ኢትዮጵያ 90 በመቶ መድኃኒት ከውጭ እንደምታስገባ ተገለጸ

ግንቦት 5/ 2014 (ዋልታ) ኢትዮጵያ 90 በመቶ የመድኃኒት አቅርቦትን የምታስገባው ከውጭ መሆኑ ተገለጸ፡፡

ከዚህ ውስጥ ከ85 በመቶ በላይ መሰረታዊ እና ህይወት አድን መድኃኒቶች ከውጭ የሚገባ ሲሆን 15 በመቶ ብቻ ደግሞ በሀገር ውስጥ ምርት የሚሸፈን ነው ተብሏል፡፡

መድኃኒትን ከውጭ ሀገር ታዞ ሀገር ውስጥ እስኪገባ ከ220 ቀናት በላይ እንደሚፈጅም ተገልጿል፡፡

“የፋርማሲዩቲካል አምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍን በአዲስ ምዕራፍ ማጠናከር” በሚል መሪ ሀሳብ ከፋርማሲዩቲካል አምራቾች እና ባለድርሻ አካላት ጋር በዛሬው እለት ምክክር ተካሂዷል፡፡

በመድረኩ ኢትዮጵያ ከውጭ የምታስገባውን የመድኃኒትና የህክምና ግብዓት በሀገር ውስጥ መሸፈን እንዳትችል ያደረጉ ችግሮችን በመለየት የመፍትሄ አቅጣጫ ማስቀመጥን ያለመ ምክክር ነው የተካሄደው፡፡

በሀገሪቱ የመድኃኒትና የህክምና ግብአት የሚያመርቱ ድርጅቶች 28 ብቻ መሆናቸውም በመድረኩ ተጠቁሟል፡፡

የህክምና ግብአትና የመድኃኒት አቅርቦትን በሀገር ውስጥ የሚያመርቱ እነዚህ ተቋማት ታዲያ የሀገር ውስጥ ፍጆታን መሸፈን ቀርቶ ምርታማነታቸውም እየቀነሰ መጥቷል ነው የተባለው፡፡

ለዚህ ደግሞ በዋነኝነት ጥሬ እቃን ከውጭ ለማስገባት የውጭ ምንዛሬ እጥረት ስላለባቸው ነው ተብሏል፡፡

በቀጣይ አራት ዓመታት 60 በመቶ በ8 ዓመት ውስጥ ደግሞ 80 በመቶ የመድኃኒት እና የህክምና ግብዓትን በሀገር ውስጥ ለማሟላት እቀድ መያዙ የተገለፀ ሲሆን በጥሬ እቃ ግዢ የሚስተዋለውን የውጭ ምንዛሬ እጥረት ለመቅረፍ ጥሬ እቃ በሀገር ውስጥ የሚመረትበት ሥርዓት ለመፍጠር መንግሥት ቁርጠኛ መሆኑም ተመላክቷል፡፡

ዘርፉን ለመደገፍም ሁሉም ባለድርሻ አካላት በትብብር ሊሰራ ይገባልም ተብሏል፡፡

በትዕግስት ዘላለም
1.2K views12:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 14:38:55
ጠ/ሚ ዐቢይ በተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች ፕሬዝዳንት ህልፈት የተሰማቸውን ሀዘን ገለጹ

ግንቦት 5/ 2014 (ዋልታ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች ፕሬዝዳንት ሼክ ካሊፋ ቢን ዛይድ አል ናህያን ህልፈት የተሰማቸውን ሀዘን ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በትዊተር ገጻቸው ባስተላለፉት የሀዘን መልዕክት ለተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች አልጋ ወራሽ ሼክ ሞሃመድ ቢንዛይድ አልናህያን እንዲሁም ለተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች ሕዝብ የተሰማኝን ጥልቅ ሀዘን እገልጻለሁ ብለዋል።

የተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች ፕሬዝዳንት ሼክ ካሊፋ ቢን ዛይድ አል ናህያን ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው በተወለዱ በ73 ዓመታቸው በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።

ለፈጣን መረጃዎች፦
ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW
1.3K views11:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 14:27:31
ሕዝቡ ጥቅማቸው የተነካባቸው ግለሰቦች የቆየ የአብሮነት ባህሉን እንዳይሸረሽሩት ጠብቆ መያዝ አለበት - ሻለቃ አትሌት ኃይሌ ገብረሥላሴ
1.3K views11:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ