Get Mystery Box with random crypto!

Top Mereja

የቴሌግራም ቻናል አርማ topmereja — Top Mereja T
የቴሌግራም ቻናል አርማ topmereja — Top Mereja
የሰርጥ አድራሻ: @topmereja
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 29.48K
የሰርጥ መግለጫ

-ማስታወቂያ ለማሰራት እና ለአስታየት :- @NatnaelAbreham1
የ Twitter አድራሻ : http://twitter.com/BoleMereja?t=watBbei5PnmgrUd80qQrnw&s=09
ዩቲዩብ : https://youtube.com/channel/UCXcMdhLzUAPeRAxW48JFClQ

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2023-10-16 15:00:12 የኤርትራ መንግስት በቀይባህር ጉዳይ ከማንም ጋር ለድርድር እንደማይቀመጥ አሳወቀ

የኤርትራ መረጃ ሚኒስቴር ባወጣዉ አጭር መግለጫ በቀይባህር ጉዳይ ከማንም ጋር ለድርድር እንደማይቀመጥ አሳዉቋል።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ስለ ውሀዊ አካሎችና ስለ ባህር በሮች የተባለውንና ''ተብሏል'' የተባለው ነገር ቁጥር የለውም ያለዉ ሚኒስቴሩ በዚም ያልተገረመ ታዛቢ የለም ሲል ገልጿል።

የኤርትራ መንግስትም እንደሁልጊዜው በእንደዚህ ዓይነቱ ጉዳዮች ላይ ለውይይት እንደማይታደም ማረጋገጡን ዳጉ ጆርናል ከሚኒስቴሩ ያገኘዉ መረጃ ያመላክታል።

ይህ ነገር ይመለከተናል የሚሉ ሁሉም አካላት ጉዳዩን እንዳይነኩት የኤርትራ መንግስት አስጠንቅቋል። በቅርቡ በመንግስት የመገናኛ ብዙኃን በተሰራጨ መልዕክት ጠ/ሚ ዐቢይ የባህር በር ጉዳይን አንስተዉ ለህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባላት ማወያየታቸዉ ይታወሳል።

@Topmereja
15.2K views12:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-10-16 11:35:16 “የተማሪዎች መውደቅ የትምህርት ሥርዓቱንና የትምህርት ሥርዓቱን የሚመራውን ተቋም ውድቀትና ክሽፈት ማሳያ ነው” እናት ፓርቲ
ፓርቲው ኹሉም ተማሪዎች ፈተናውን በድጋሚ እንዲፈተኑ ጠይቋል
የ2015 የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን 817 ሺሕ 832 ተማሪዎች መውደቃቸው የትምህርት ሚኒስቴርን የአሰራር ሂደት፣ የፈተና አወጣጥ፣ የግምገማ እንዲሁም መለኪያ መንገዶች ተአማኒነትን ጥያቄ ውስጥ ከማስገባቱ ባሻገር፤ ኹኔታው የተፈታኝ ተማሪዎችን መውደቅ ሳይሆን የትምህርት ሥርዓቱንና የትምህርት ሥርዓቱን የሚመራውን ተቋም ውድቀትና ክሽፈት ማሳያ ነው ሲል እናት ፓርቲ ገለጸ።

ፓርቲው የ2015 የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤትን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ፤ “በትምህርት ሚንስቴር ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ መግለጫ የተሰጠበት የፈተናው ውጤት፤ ጥሮ ግሮ በመስራት "ልጄን ለቁምነገር አበቃለሁ" ብሎ ለዘመናት ያስተማረውን የአገራችንን ሕዝብ ክፋኛ አሳዝኗል፡፡” ብሏል።

በተጨማሪም ውጤቱ በተማሪዎች ላይ ከፍተኛ የሆነ ተስፋ መቁረጥ እና የማይሽር ሥነ-ልቦናዊ ተጽእኖን ማሳደሩን ገልጿል።

ፓርቲው አክሎም፤ “አገራችን በጦርነት እና አለመረጋጋት ወስጥ መሆኗ እየታወቀ "97% ያህል ተማሪዎች ወድቀዋል" ማለት፤ የትምህርት ሚኒስቴር መስርያ ቤቱ ከመንግሥት ጋር የተዋዋለው ድብቅ አጀንዳ እንዳለው ያመለክታል።” ሲል ገልጿል፡፡

“ተማሪዎች የአገራችን ተስፋዎች ናቸው።” ያለው ፓርቲው፤ እነዚህን የነገ አገር ተረካቢ ኃይሎች በኢትዮጵያ ተስፋ እንዳያደርጉ ከጅምሩ ማምከን ተገቢ አለመሆኑን አመላክቷል፡፡

እንዲሁም “ባለፋት አምስት ዓመታት "ለውጥ እናመጣለን" በሚል ሰበብ እንዲሁም በቂ ምክክር፣ ምርምር እና ግምገማ ያልተደረገበትን አዲስ የትምህርት ፍኖተ ካርታ በፖለቲካዊ ውሳኔ በትውልዱ ላይ ለመጫን የተደረገው እርብርብ ትልቅ ኪሳራ አሳድሯል።” ብሏል፡፡

“ለትምህርት ሴክተሩ እየተሰጠ የሚገኘው ትኩረት አናሳ መሆን፣ ለተማሪዎች የመጻሕፍት አቅርቦት አለመኖር፣ ትክክለኛ የትምህርት ሰነዶችን የማጣራት ዘመቻው ደካማና የይምሰል መሆኑ፣ የተንሸዋረረ የጥያቄ አወጣጥ፣ የምዘና ሥርዓቱ ዝርክርክነት፣ የጥያቄዎቹ መልስ ይፋ አለመደረጉ፣ ዝቅተኛ የበጀት ድልድል ወዘተ… አሁንም በዋልፈሰስ መቀጠላቸው፤ ቀጣዩ ትውልድ በትምህርት መስክ ተስፋ እንዳያደርግ ምክንያት ይሆናሉ” ብሎ እንደሚያምንም ፓርቲው ገልጿል፡፡

በተጨማሪም ባለፋት ሰላሳ ኹለት ዓመታት መምህራን ክብር እንዲያጡ፣ በሙያቸው ከመኩራት ይልቅ እንዲሸማቀቁ፣ መሠረታዊ ፍላጎታቸውን መልሰው በችግር ፈቺ የምርምር ሥራዎች ላይ እንዳያተኩሩ የተፈጸመባቸው በደል ሁንም ተጠናክሮ መቀጠሉ ፓርቲውን እንደሚያሳስበው አመላክቷል፡፡

ስለሆነም “የትምህርት ሚኒስቴር የአሰራር ሥርዓቱን ከወሬ በዘለለ በተግባር ከፖለቲካ ጥገኝነት እንዲያላቅቅ” የጠየቀው ፓርቲው፤ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ከሥር መሠረቱ ስትራቴጂካሊ መስራት ሲገባው በስሜት ከአናቱ ለማስተካከል የሄደበት እርቀት የተሳሳተ በመሆኑ ሊታረም ይገባል ብሏል፡፡

እንዲሁም፤ የተማሪዎች ኹለንተናዊ አቅም እንዲያድግ መንግሥት በዋናነት ደሞዝን ጨምሮ የመምህራን አኗኗርና ሕይወት እንዲቀየር አፋጣኝ ወሳኔ በመስጠት ለተግባራዊነቱ እንዲሰራ አሳስቧል፡፡

በተጨማሪም፤ በ2015 የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የወደቁ የተማሪዎች ቁጥር እጅግ በጣም ከፍተኛ (817 ሺሕ 832) በመሆኑ፤ እንዲሁም የምዘና ሂደቱን በግልጽ ጥያቄ ውስጥ የሚከት በመሆኑ የተስተዋሉ ችግሮች በአግባቡ ተቀርፈው ኹሉም ተማሪዎች በድጋሚ እንዲፈተኑ ፓርቲው ጠይቋል፡፡

@Topmereja
13.7K views08:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-10-12 17:08:51
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ 445 ሚሊዮን ዶላር ባለ 62 ወለል ሰማይ ጠቀስ ህንፃ ሊገነባ ነዉ !

በአረንጓዴ ህንፃ የወርቅ ሰርተፊኬት ደረጃ እየተሰራ እንደሚገኝ የተነገረለት የተቋሙ ዋና መስሪያቤት ዲዛይን ከፀሐይ እና ከንፋስ ኃይል በማመንጨት ለህንፃው ፍጆታ ኃይል ማቅረብ የሚያስችሉ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች እንደሚኖሩት ተነግሯል።

ሜክሲኮ በሚገኘዉ የተቋሙ ቅጥር ግቢ የሚገባዉ ባለ 62 ወለል ህንፃዉ በቀጣይ 4 ዓመታት ዉስጥ እንደሚጠናቀቅ እና ለዚህም 445 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ወጪ እንደሚደረግበት ተቋሙ አስታዉቋል።

Via Capital

@topMereja
12.8K views14:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-10-10 22:18:41
የቀድሞው የሶማሌ ክልል ፕሬዝደንት የነበሩት እና አሁን በእስር ላይ የሚገኙት አቶ አብዲ መሀመድ ኡማር ለጠ/ሚር አብይ አህመድ ጥቅምት 14,2011 ደብዳቤ ፅፈው ነበር። በወቅቱ ደብዳቤው የያዘው ዋና ዋናዎቹ ነጥቦች።

* በክልሉ የሰው ህይወት እንዳይጠፋ እና ንብረት እንዳይወድም አንተ (ጠ/ሚር አብይ) የሰጠኸኝን ምክር እና ሀሳብ ችላ ብያለሁ።
* እንደገናም ችግሩ ከተከሰተ በሁዋላም ሳትተወኝ የሰጠኸኝን ጥሩ ሀሳብ ባለመቀበሌ የለውጡ እንቅፋት ነበርኩ። ለዚህም ከልቤ ተፀፅቻለሁ።
* አሁንም ቢሆን ቃልህን እንደማታጥፍ እና ፊትህን እንደማታዞርብኝ ተስፋ አደርጋለሁ።
* ከመጀመርያ ጀምሮ አመጣጥህንና እያመጣህ ያለውን አመርቂ ለውጥ በጣም አደንቃለሁ።
* እኔም ስህተቴን አርሜ ከህዝብ እና መንግስት ጋር በመሆን የለውጡ ቸርኬ ሆኜ እሰራለሁ።

@topMereja
14.1K views19:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-10-08 22:34:35
በእስራኤል ጥቃት የፈራረሰው መስጂድ !

በጋዛ ምስራቃዊ ክፍል ካሃን ዩኒስ ከተማ የሚገኘው የአል አሚኒ ሞሀመድ መስጂድ በእስራኤል የአየር ድብደባ ፈራርሷል። በጸሎት ላይ የነበሩ ሰዎች ግን በፈጣሪ ተአምር መትረፋቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል ሲል የአል ዐይን ዘገባ ያሳያል።

@topMereja
13.1K views19:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-10-08 19:27:10 https://whatsapp.com/channel/0029VaBmbqg42DciYQ6GHw43
12.9K views16:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-10-08 14:20:50
313 ፍልስጥኤማውያን እና 300 እስራኤላውያን መገደላቸው ተነገረ

እስራኤል በጋዛ እየፈጸመችው ባለው አጸፋዊ የአየር ጥቃቶች 313 ፍልስጥኤማውያን መገደላቸውን የፍልስጥኤም የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር አስታውቋል ሲል ቢቢሲ አስነብበዋል።

ሚኒስቴሩ 2 ሺህ ሰው መቁሰላቸውንም አክሎ ገልጿል። ከእስራኤል በኩል ደግሞ ቢያንስ 300 እስራኤል መገደላቸውን በቱርክ የሚገኘው የእስራኤል ኤምባሲ አስታውቋል።

ኤምባሲው የእስራኤልን የጤና ጥበቃ ሚኒስቴርን ዋቢ አድርጎ ባወጣው መረጃ በርካቶች ታግተዋል ብሏል።

በተጨማሪም ወደ 2 ሺህ የሚጠጉ ሰዎች ቆስለው በሆስፒታሎች ህክምና እየተደረገላቸው መሆኑን መግለጫው ጠቅሶ ከእነዚህም ውስጥ 19ቱ በአስጊ ሁኔታ ላይ ይገኛሉ ብሏል። አኃዙን በተመለከተ የእስራኤል መንግሥት በይፋ አላረጋገጠም።

@topMereja
13.6K views11:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-10-04 22:15:35
ይህን መሠል አደጋ እጅግ እየተደጋገመ ነው የአካባቢው የንግድ ቢሮ ቁጭ ብሎ ገንዘብ መሰብሰብ ብቻ ሳይሆን የእንስሳቱ እንቅስቃሴ ላይ ቁጥጥር እና ክትትል በማድረግ ምቹ የገበያ እና የመጓጓዣ ቦታ በማዘጋጀት ሀላፊነቱን ሊወጣ ይገባል በተጨማሪም መንገዱን የሚያስተዳድረው አካል ከዚህም የከፋ አደጋ እንዳይደርስ ተጫማሪ አጥሮችን ቦታው ላይ ሊያረግ ይገባል!!

@topMereja
12.8K views19:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-10-01 12:46:45
ዛሬ መስከረም 20 ቀን 2016 ዓ.ም ንጋት 11 ሰዓት ላይ የሰሌዳ ቁጥሩ 3-B29228 ፒክአፕ ደብል ጋቢና የሆነ ተሽከርካሪ የጉዞ አቅጣጫዉን ወደለገጣፎ አድርጎ ሲጓዝ ጣፎ አደባባይ ጋ ሲደርስ ዋናዉን መንገድ ጥሶ ገደል ዉስጥ በመግባቱ አሽከርካሪዉን ጨምሮ የሁለት ሰዎች ህይወት ሲያልፍ አንድ ሰዉ ላይ ከባድ ጉዳት ደርሷበታል።

የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች የሁለቱን ሰዎች አስከሬንና ተሽከርካሪዉን ከገደል ዉስጥ የአወጡት ሲሆን ይህም ሂደት 1 :20 ሰዓት ፈጅቷል።

በአደጋዉ ጉዳት የደረሰበት ሰዉ ህክምና እየተደረገለት ይገኛል።

በሌላ በኩል ትላንት ቅዳሜ ከቀኑ 9:20 በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ሸጎሌ አካባቢ ከጉድጓድ ዉስጥ በፓምፕ ዉሀ በመሳብ ላይ የነበረ ዕድሜዉ 20 ዓመት የሆነ ወጣት ህይወቱ አልፏአል።

ወጣቱ ህይወቱ ያለፈዉ ጥልቀቱ 10 ሜትር ከሆነ ጉድጓድ ዉስጥ ዉሀ በፓምፕ በመሳብ ላይ እያለ ተንሸራትቶ በመግባቱ ነዉ።

የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች የወጣቱን አስከሬን ከጉድጓድ ዉስጥ አዉጥተዉታል።

ከጉድጓድ ዉስጥ እንዲህ ዓይነት ስራዎች በሚሰሩበት ጊዜ አስፈላጊዉን የደህንነት መስፈርት አስፈላጊ በመሆኑ መሰል ስራዎች ሲከናወኑ ከጥንቃቄ ጋር መሆን ይኖርበታል ሲሉ መረጃውን ለፋስት መረጃ ያደረሱት አቶ ንጋቱ ማሞ የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ህዝብ ግንኙነት ባለሞያ ናቸው።

@topMereja
15.5K views09:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-09-24 22:10:16
ልዩ መረጃ

ዛሬ ጎንደር አከባቢ በተደረገ ዉጊያ በፋኖ የተማረኩ የመከላከያ ሰራዊት አባላት።

@topMereja
15.3K views19:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ