Get Mystery Box with random crypto!

ትምህርት ሚኒስቴር

የቴሌግራም ቻናል አርማ timihert_minister — ትምህርት ሚኒስቴር
የቴሌግራም ቻናል አርማ timihert_minister — ትምህርት ሚኒስቴር
የሰርጥ አድራሻ: @timihert_minister
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 9.06K
የሰርጥ መግለጫ

ተጨማሪ መረጃዎችን
በዌብሳይት - www.moe.gov.et
በሊንክዲን - https://www.linkedin.com/company/ministry-of-education-ethiopia
በትዊተር - http://twitter.com/fdremoe
በፌስቡክ -https://www.facebook.com/fdremoe/
በቴሌግራም-https://t.me/timihert_minister
ይከታተሉ።

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2023-03-28 16:48:07
567 views13:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-28 16:48:07
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ዛሬ የመንግስትን የስድስት ወራት ሪፖርት መነሻ በማድረግ በምክር ቤቱ ለሚነሱ ጥያቄዎች ምላሽ እየሰጡ ይገኛል
---------------//---------------

ምክር ቤቱ ዛሬ በሚያካሂደው 11ኛ መደበኛ ስብሰባው በኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ከምክር ቤቱ አባላት ለሚነሱ የተለያዩ ወቅታዊና ሀገራዊ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ይገኛል።

በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የትምህርት ዘርፉን በተመለከተ የተነሱ ጥያቄዎች:-

1)መንግስት የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ባለፉት ዓመታት የሰራቸው ስራዎች አበረታች ቢሆኑም አሁንም የተለያዪ ማነቆዎች ይስተዋላሉ

ከነዚህም መካከል የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መማሪያ መፅሐፍ ማሳተም የፌድራል ድርሻ ቢሆንም እስካሁን ያለመድረሱ፣

የመሠረተ ልማት አቅርቦት የመብራትና ኢንተርኔ ያለመኖር እንዲሁም የመምህራን አቅም ግንባታ እጥረት ለትምህርት ጥራት ችግር ሆነዋል።

የወልዲያ ዩኒቨርስቲ በጦርነቱ ምክንያት ተጎድቶ ለትምህርት ስራ ምቹ ያለመሆኑ ይጠቀሳል።

በመሆኑም በትምህርት ዘርፉ ያለውን ችግር ለማሳካት መንግስት ምን አስቧል የሚል ጥያቄ የተጠየቀ ሲሆን
የጠቅላይ ሚኒስትሩን ምላሽ

https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid02xAS66Qo9142mybqmKjNZPpWYhkqTafZCbWgZCCrRq9ZXKzmjrirCiiVifTq1wYpBl&id=100064682287722&mibextid=Nif5oz
539 views13:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-28 16:48:06 የ2015ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎች ምዝገባ ከ መጋቢት 20 - ሚያዚያ 15 ይከናወናል።
------------------------
የ2015ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎች ምዝገባ ከ መጋቢት 20 - ሚያዚያ 15,2015ዓ.ም እንደሚከናወን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ገለፀ።

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2015ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተናን የሚወስዱ ተማሪዎች ምዝገባን በተመለከተ መግለጫ ሰጥቷል።

መግለጫውን የሰጡት የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) የ2015ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ምዝገባ በበይነ መረብ እንደሚከናወን ገልፀዋል።

መረጃዎችን በትክክል ባለመሙላት ምክንያት የፈተና ሂደት ላይ ችግር እንደሚፈጥር የገለፁት ዋና ዳይሬክተሩ ይህንን ለማስቀረት ተማሪዎች መረጃዎቻቸውን በወቅቱ ማስመዝገብ እንዳለባቸውም ተናግረዋል።

ያልተመዘገበ ተማሪ የ 2015ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን እንደማይፈተንም ዶ/ር እሸቱ ገልፀዋል።

በ 2014ዓ.ም በነበረው የምዝገባ ሂደት የተፈታኞች ምዝገባ መረጃ ጉድለት የነበረበት እንደነበር እና በዚህም ምክንያት የፈተና አሰጣጥ ሂደቱ የተራዘመ እንዲሆን እንዳደረገው በመግለጫው ተነስቷል ።

በመግለጫው ምዝገባው ከ መጋቢት 20 እስከ ሚያዚያ 15,2015ዓ.ም ድረስ ለመደበኛና የማታ ተማሪዎች በመንግስት የመደበኛ ትምህርት ቤቶች ለ ድጋሜ ተፈታኞች እና የርቀት ትምህርት ተማሪዎች በተመረጡ የወረዳ ትምህርትጽ/ቤቶች አማካኝነት በበይነ መረብ ብቻ እንደሚያካሂዱ ተገልጿል።

መደበኛ ተመዝጋቢዎች ከ 9-12ኛ ክፍል በተከታታይ ሲማሩ የነበሩ እና በ2015 ዓ.ም በመማር ላይ መሆን እንደሚጠበቅባቸው የተገለፀ ሲሆን
የማታ እና የርቀት ተማሪዎች የ11ኛ ክፍል ሶስት ሴሚስተር እንዲሁም ለ12ኛ ክፍል የሁለት ሴሚስተር የትምህርት ማስረጃ ማሟላት እንደሚጠበቅባቸው ተገልጿል።

ድጋሜ ተፈታኞችም ከዚህ ቀደም የተፈተኑበትን የትምህርት ማስረጃ በመያዝ መመዝገብ እንደሚችሉ ተነግሯል።

ተማሪዎች ለምዝገባ ሲመጡም ማንነታቸውን የሚገልፅ መታወቂያ በመያዝ በአካል ተገኝተው በበይነ መረብ መመዝገብ እንደሚጠበቅባቸው ተገልጿል።

በመግለጫውም ተማሪዎች፣ ወላጆች ፣ መዝጋቢዎች እና መምህራን የሚጠበቅባቸውን ሃላፊነት እንዲወጡ ጥሪ ቀርቧል።

ፈተናው የሚሰጥበት ቀንን በተመለከተም ፈተናው በዩኒቨርስቲ ውስጥ እንደሚሰጥና ቀኑ ወደ ፊት የሚገለፅ መሆኑን ዋና ዳይሬክተሩ ገልፀዋል።
619 views13:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-28 16:48:06
603 views13:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-23 17:23:59
ትምህርት ቤቶች ለስርዓተ ፆታና አካቶ ትምህርት ምላሽ ሰጪና ምቹ እንዲሆኑ ማድረግ እንደሚገባ ተገለጸ፡፡
-------------------------------------------------
መጋቢት 14/2015ዓ.ም. (የትምህርት ሚኒስቴር) የትምህርት ሚኒስቴር ከብሪቲሽ ካውንስል ጋር በመተባበር በስርዓተ ፆታና አካቶ ትምህርት ላይ ትኩረት ያደረገ የአሰልጣኞች ስልጠና ከክልልና መምህራን ትምህርት ኮሌጆች ለተውጣጡ መምህራንና የክልል ትምህርት ቢሮ የስርዓተ ጾታ ባለሙያዎች ሰጥቷል፡፡

የስልጠናው ዓላማም የስርዓተ ፆታና አካቶ ትምህርት ተሳትፎ ውጤታማነትን ለማሻሻል እና ጥራት ያለው ትምህርት ለመስጠት የሚያስችል ክህሎት ለመገንባት መሆኑ ተገልጿል።

በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጌታቸው ተፈራ ስልጠናው ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ስርዓተ ፆታ ተኮር ጉዳዮችን መሰረት ያደረጉ አካታች ውጤታማ ትምህርት ቤቶችን ለመፍጠር የሚያደርገውን ጥረት ለማሳካት የሚያግዝ መሆኑን ገልጸዋል ፡፡

ሁሉም ልጆች የመማር እድል እንዲያገኙ ለማስቻል ትምህርት ቤቶችን አካታችና ምቹ የትምህርት አካባቢ ማድረግ ይገባልም ብለዋል፡፡

በተለይም በትምህርት ዘርፉ የስርዓተ ፆታ እኩልነትን ለማስፈንና ልዩ ፍላጎት ያላቸውን ልጆች ተሳትፎን ለማሳደግና ውጤታማነትን የሚያረጋግጥ አካታች ትምህርት መስጠትና የሴት ልጆችን ውጤታማትነት ማሳደግ ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት ይገብልም ተብሏል፡፡

ሙሉ ዜናውን

https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid07niRKUxkegNSwc3YAC6aRGAraHNWfKdD7hp76oXTRPHQK46g6WvE89zU96J8Kodml&id=100064682287722&mibextid=Nif5oz
1.1K views14:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-21 17:53:25
የአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ቆጮን በዘመናዊ መንገድ ማምረት የሚስችል ቴክኖሎጂን በስፋት ለህብረተሰቡ ለማድረስ እየሰራ እንደሚገኝ አስታወቀ፡፡
-------------------------------------------------
መጋቢት 12/2015ዓም.(የትምህርት ሚኒስቴር) የአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ እንሰትን በዘመናዊ መንገድ በማምረት ለምግብነት ለማዋል የሚያስችል ቴክኖሎጂን በማልማት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ የዩኒቨርሲቲው የእንሰት ፕሮጀክት ተመራማሪና አስተባባሪ አዲሱ ፈቃዱ( ዶ/ር) ገልፀዋል፡፡

እንሰት በባህላዊ መንገድ ሲዘጋጅ ብዙ ተግዳቶች ያሉበት፣ የመብላላት ሂደቱ ረጅም ጊዜ የሚፍጅና ከፍተኛ ጉልበት የሚጠይቅ በመሆኑ ዩኒቨርሲቲው ይህንን የሚቀይር ሳይንሳዊ ሂደቱን የተከተለ የተሻለ ቴክኖሎጂ በመፍጠር አርሶ አደሩን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉንም ተናግረዋል፡፡

በዚህም በቀላሉ እንሰትን መፋቅ የሚያስችል የእንሰት መፋቂያ ማሽን በመስራት የቆጮውን ጥራት ከመጠበቅ ባለፈ የእናቶችን ድካም በከፍተኛ መጠን ማስቀረት የሚያሰችል ቴክኖሎጂ መፍጠር መቻሉን ተመራማሪው ገልፀዋል፡፡

አዲሱ ቴክኖሎጂ ብክነትን ከመቀነስ ባሻገር አርሶ አደሩ ድረስ በመሞከረና ውጤታማነቱን በማረጋገጥ አርሶ አደሩ ጥቅም ላይ እንዲያውለው መደረጉንም ዶ/ር አዲሱ አብራርተዋል፡፡


ሙሉ ዜናው
https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid0DXNH36xxwsfGpCJbcdGctnQeLdn6gwcg8U9ATqBrSGqEu5oVE1hCzAujR4hkLB5yl&id=100064682287722&mibextid=Nif5oz
552 views14:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-19 18:17:58
የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ የዘላቂ ኃይል ልማት ለገጠር ሥራ ፈጠራ በተሰኘ ፕሮጀክት የማህበረሰብ አገልግሎቶችን እየሰጠ ይገኛል፡፡
======================

መጋቢት 10/2015ዓም. (የትምህርት ሚኒስቴር) የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ የዘላቂ ኃይል ልማት ለገጠር ሥራ ፈጠራ በተሰኘ በምርምር በታገዘ ፕሮጀክት ውጤታማና ዘርፈ ብዙ የማህበረሰብ አገልግሎቶችን እየሰጠ እንደሚገኝ አስታውቋል፡፡

በባህርዳር ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት ተስፋየ ሸፈራው (ዶ/ር) ዩኒቨርሲቲው በታዳሽ ኃይል አቅርቦት፣በሶፍትዌር ኢንጅነሪኒግ፣በግብርና እና በሌሎችም ዘርፎች በአሁኑ ወቅት ማህበረሰቡ እየተገለገለባቸው ያሉ በርካታ የምርምር ውጤቶችን ማበርከቱን ገልጸዋል፡፡

ዶ/ር ተስፋየ ዩኒቨርስቲው ችግር ፈቺ የሆኑ ስራዎችን ለመስራት አቅም ያለው መሆኑን ገልፀው ይህንን ለማድረግም ከህብረተሰቡ፣ ከባለሀብቶች እና ከኢንዱስትሪዎች ጋር በቅርበት መስራት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።

በዩኒቨርሲቲው የዘላቂ ኃይል ልማት ለገጠር ሥራ ፈጠራ ፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ ነገሰ ያዩ የዘላቂ ኃይል ልማት ለገጠር ሥራ ፈጠራ ፕሮጀክት ዩኒቨርሲቲው ውጤታማ ከሆነባቸው በምርምር ታግዘው ከሚሠሩ በርካታ የማህበረሰብ አገልግሎት ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ መሆኑን ተናግረዋል።

ሙሉ መረጃው

https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid02CpC9wmcTzwcqzQJuishKThaPM8x9F5UnPmETRXUUtLszwjKdqtbgKjyWYW3Tbs8Fl&id=100064682287722&mibextid=Nif5oz
1.2K views15:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-17 22:19:17
አዲሱ የአጠቃላይ ትምህርት ስርዓተ-ትምህርት ተማሪዎች በሚፈልጉት የትምህርት መስክ በቂ እውቀት እንዲይዙ እድል የሚፈጥር እንደሆነ ተማሪዎች ተናገሩ
-----------------------------------

የትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ሰርዓተ-ትምህርት ላይ ክለሳ በማድረግ ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ አዲሱን የአጠቃላይ ትምህርት ስርዓተ-ትምህርት ከቅድመ መደበኛ እስከ 8ኛ ክፍል ሙሉ ለሙሉ እንዲሁም በ9ኛ እና 10ኛ ክፍል ደግሞ የሙከራ ትግበራ ላይ ይገኛል።

አዲሱ ሰርዓተ-ትምህርት ሀገር በቀል እውቀትን በማካተት ከንድፈ ሃሳብ በተጨማሪ ለተግባር ትምህርት ትኩረት በመስጠት እና የግብረ-ገብ ትምህርትን በማካተት እንዲሁም በቴክኖሎጂ የተደገፈ ሆኖ 21ኛው ክፍለ ዘመን የሚጠይቀውን እውቀትና ክህሎት ማስጨበጥ በሚችል መልኩ ተዘጋጅቶ ወደ ሰራ ተገብቷል።

በአሁን ሰዓት በ9ኛ እና 10ኛ ክፍል በሙከራ ላይ ያለውን ይህን ስርዓተ-ትምህርት አስመልክቶ የዳግማዊ ምኒሊክ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ሃሳባችውን አካፍለውናል።

በትምህርት ቤቱ የ9ኛ ክፍል ተማሪ የሆነችው ቅድስት ወንደሰን አዲሱ ስርዓተ-ትምህርት ከንድፈ ሀሳብ ባሻገር ተግባር ተኮር በመሆኑ ተማሪዎች ሙሉ እውቀት እንዲይዙ የሚያስችል መሆኑን ገልፃለች። አዲሱ ስርዓተ-ትምህርት ተማሪዎች በሚፈልጉት የትምህርት መስክ ላይ በቂ እውቀት እንዲይዙ እድል የሚፈጥርም ነው ስትል ትናገራለች።
ሙሉ ዜናው
https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid02GYRmbM4ventmX6FkLTqoaPmXv9g3Q2FB2fpwTMkTbjjmHrXC4iw11pVqc7ivDty7l&id=100064682287722&mibextid=Nif5oz
1.6K views19:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-15 17:05:46
#ማስታወቂያ

በ2014 ዓም. 12ኛ ክፍል የላቀ ዉጤት አምጥታችሁ የዉጪ ሀገር የትምህርት እድል/Scholarship / እድል ለተሰጣችሁ 273 ተማሪዎች

በ2014 ዓም. 12ኛ ክፍል የላቀ ዉጤት አምጥታችሁ የዉጪ ሀገር የትምህርት እድል/Scholarship / እድል የተሰጣችሁ 273 ተማሪዎች የዉጪ ሀገር ትምህርቱ የሚጀመረዉ ከመስከረም/2016ዓም. ጀምሮ በመሆኑ ቀደም ሲል ወደተመደባችሁባቸዉ ዩኒቨርስቲዎች እንድትገቡ እናሳስባለን፡፡

ለዉጪ ሀገር ትምህርታችሁ የሚያግዝ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ትምህርትና ሌሎች የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ከተመደባችሁባቸዉ ዩኒቨርስቲዎች ጋር በመነጋገር የሚፈጸም ይሆናል፡፡

ማስታወሻ፤- በዚህ ጉዳይ በተናጠል ወደትምህርት ሚኒስቴር የሚመጣ ተማሪ የማናስተናግድ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

የትምህርት ሚኒስቴር!
2.2K views14:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-15 17:05:46
#ማስታወቂያ

በአቅም ማሻሻያ (Remedial )ፕሮግራም መቅደላአምባ ዩኒቨርሲቲ ለተመደባችሁ ተማሪዎች ብቻ

በ 2014 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ የ Remedial ፕሮግራም ለመከታተል መቅደላአምባ ዩኒቨርስቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች የተደረገ ማስተካከያ ስላለ ምደባችሁን እንደገና ገብታችሁ እንድታዩ እናሳስባለን፡፡

የትምህርት ሚኒስቴር!
1.9K views14:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ