Get Mystery Box with random crypto!

ትምህርት በቤቴ🔝

የቴሌግራም ቻናል አርማ temhert_bebete — ትምህርት በቤቴ🔝
የቴሌግራም ቻናል አርማ temhert_bebete — ትምህርት በቤቴ🔝
የሰርጥ አድራሻ: @temhert_bebete
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.20K
የሰርጥ መግለጫ

A channel created for sharing
🔺study tips,
🔺short notes,
🔺tutorials,
🔺educational news,
🔺life tips and some motivational quotes ...
For comment @Tmhert_bebete_info_bot
Buy ads: https://telega.io/c/temhert_bebete

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 17

2022-08-25 22:21:56
በ2014 ዓ.ም የመመሪያ ጥሰት ፈጽመው እርምት እንዲያደርጉ ውሳኔ ተላልፎባቸው ተግባራዊ ያላደረጉ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በወንጀልና በፍትሐ ብሔር ተጠያቂ ሊደረጉ ነው፡፡ 

የትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት ነው ተቋማቱን ተጠያቂ የሚያደርገው።

ባለሥልጣኑ በ2014 ዓ.ም በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች ባካሄደው ድንገተኛ ፍተሻ የሥነ ሥርዓት መመርያ ጥሰት ፈጽመው የተገኙ የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ላይ የማስተካከያ ዕርምጃ እና ማጋለጥ ሲያደረግ ቆይቷል።

ውሳኔውን ተግባራዊ ያላደረጉ ተቋማትን በወንጀል እና በፍትሐ ብሔር ተጠያቂ ለማድረግ እንቅስቃሴዎች መጀመራቸውን የባለሥልጣኑ የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር ታረቀኝ ገረሱ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

የተለያዩ የመመርያ ጥሰቶች በፈጸሙ 373 የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ካምፓሶች ላይ ባለሥልጣኑ በ2014 ዓ.ም ዕርምጃ መውሰዱን ኃላፊው አስታውሰዋል።

ተማሪዎችን እንዲበትኑ፣ ካምፓሶቻቸውን እንዲዘጉ እንዲሁም ሙሉ በሙሉ ተቋማቸውን እንዲዘጉ ትዕዛዝ የተላለፈባቸው የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለተላለፈባቸው ውሳኔ ተገዥ መሆናቸውን ባለሥልጣኑ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን ክትትል ማድረግ መጀመሩን ገልጸዋል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete
9.3K views19:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 11:31:25 "ሁሉም ሰው ጂኒየስ ነው፤ ግን አሳ ከዛፍ ዛፍ በመዝለል ችሎታው ከተመዘነ እድሜ ልኩን የማይረባ እንደሆነ ያምናል" ይለናል አልበርት አንስታይን።

ድክመታችንን ከሌሎች ጥንካሬ ጋር ካወዳደርነውማ ሁሌም የበታችነት ይሰማናል፤ ከሌሎች ዝቅ ያልን ይመስለናል። እኛን የሚዳኘን የራሳችን መስፈርት ነው፤ የሌሎች መንገድማ የሌሎች ነው!

@temhert_bebete
@temhert_bebete
9.3K viewsedited  08:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 09:31:02
ፍቅረኛዬ ፈተና ወደቀች በሚል ትምህርት ቤቱን ያቃጠለዉ አፍቃሪ

በግብጽ ሜኑፊያ ግዛት ነዋሪ የሆነዉ የ21 ዓመት ወጣት ፍቅረኛዉ የነበረባትን የትምህርት ፈተና ማለፍ ባለመቻሏ ትምህርት ቤቱን በእሳት አጋይቷል፡፡የሀገሪቱ ጠቅላይ አቃቤ ህግ እንደገለጸው በእሳት አደጋዉ የሞተ ሆነ የተጎዳ ሰው የለም ብሏል፡፡

ግለሰቡ በቁጥጥር ስር የዋለ ሲሆን እጮኛው የትምህርት ቤቱን ፈተና መዉደቋ ክፍል እንድትደግም የሚያስገድዳት ሲሆን ይህ ደግሞ የሰርጋችንን ቀን ይገፋብናል ሲል ተናግሯል። ድርጊቱን ከፈጸመ በኃላ ከአካባቢዉ ተሰዉሮ የነበረ ሲሆን የዓይን እማኞች ለፖሊስ በሰጡት መረጃ በቁጥጥር ስር መዋሉን ገልፍ ዴሊ ኒውስ ዘግቧል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete
12.9K viewsedited  06:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-23 14:39:36 የ 12ኛ ክፍል ፈተና በ 2ት ዙር ይሰጣል።

1ኛ ዙር---Social Science ከ መስከረም 30 እስከ ጥቅምት 3

2ኛ ዙር ---Natural Science ከ ጥቅምት 8 እስከ 11

በዚህ አመት 984,000 በላይ ተማሪዎች የ12ኛ ክፈል ፈተናን ይወስዳሉ።

Social Science .......622,739 ናቸው።

Natural Science.....361,279 ናቸው።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete
17.9K views11:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-23 09:43:55
የትምህርት ሚኒስቴር "የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአካዳሚክ ፕሮግራሞችና ሥርዓተ ትምህርት ቀረፃ፣ ክለሳና ማፅደቂያ መመሪያ"ን አጽድቋል።

መመሪያው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአካዳሚክ ፕሮግራሞችና ሥርዓተ ትምህርቶች ከዓለም አቀፍ፣ ከቀጠናዊ እና ከአካባቢያዊ የልማት አጀንዳዎች ጋር ተጣጥመው እንዲሄዱ ለማድረግ ያስችላል ተብሏል።

ሚኒስቴሩ የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚከፍቷቸውን ፕሮግራሞች ከሀገሪቱ የልማት ቀረፃና አስፈላጊነት አንፃር ተጠንተው ሲቀርቡለት አግባብነታቸውን አረጋግጦ የማጽደቅ ስልጣን እንዳለው በአዋጅ ተደንግጓል።

መመሪያ ቁጥር 917/2014 ሆኖ በፍትህ ሚኒስቴር የጸደቀውን አዲሱን መመሪያ፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተግባራዊ እንዲያደርጉ በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ተፈርሞ መሰራጨቱ ታውቋል።

አምስት ክፍሎች እና 22 አንቀጾች ያሉት አዲሱ መመሪያ፤ ከነሐሴ 01/2014 ዓ.ም ጀምሮ የጸና እንደሆነ ተደንግጓል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete
12.4K views06:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 21:54:08
“የዘንድሮው ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና ተሰርቆ ወጥቷል” መባሉ ስህተት ነው - ኢትዮጵያ ቼክ

ከ865 ሺህ በላይ ተከታዮች ያሉትና "Mereja TV" የሚል ስያሜ ያለው የፌስቡክ ገጽ “የዘንድሮው ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና ተሰርቆ ወጥቷል” የሚል መረጃ ማጋራቱን ታይቷል። ኢትዮጵያ ቼክ የመረጃውን ትክክለኛነት ለማጣራት የተጋራውን ቡክሌት የመረመረ ሲሆን መረጃው ሀሠተኛ መሆኑን አረጋግጧል።

ኢትዮጵያ ቼክ ባደረገው ማጣራት “የዘንድሮ” ነው ተብሎ የተጋራውን የታሪክ ፈተና ቡክሌት በ2013/14 ዓ.ም የተሰጠ እንጂ አዲስ አለመሆኑን ተመልክተናል። በተጨማሪም ጉዳዩን በተመለከተ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳሬክተር ዶ/ር እሸቱ ከበደ የተሰራጨውን መረጃ መመልከታቸውን ገልጸው ሀሠተኛ መሆኑንና የተጋራው የፈተና ቡክሌት በ2013/14 (2021) ዓ.ም የተሰጠ መሆኑን ለኢትዮጵያ ቼክ አስረድተዋል።

@Temhert_Minister
@Temhert_Minister
9.9K views18:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 18:56:39 ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለ መምህራን እና ዩኒቨርሲቲዎች ምን አሉ ?

ጠ/ሚር ዶክተር ዓብይ አህመድ ትላንት ከወጣቶች ጋር በተወያዩበት መድረክ ስለዩኒቨርስቲዎች እና ስለ መምህራን ተነስቶላቸው የሚከተለውን ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፦

" የዩኒቨርስቲ መምህራን እናንተም መገንዘብ ያለባችሁ ኢትዮጵያ ደሃ አገር ናት። አሜሪካ እንኳን ዩኒቨርስቲ ተማሪ አስገብታ አትቀልብም።

ዩኒቨርስቲ ሰው ከደረሰ ራሱን ነው ማስተማር ያለበት እንጂ ለአስተማሪም ደመወዝ ፣ ለተማሪ ቀለብ አይነት ጥያቄ እንደኢትዮጵያ ላሉ ድሃ አገራት ኢኖቬተርስ አይፈጥርም።

ዩኒቨርስቲዎች አውቶነመስ ሆነው ራሳቸውን ማስተዳደር አለባቸው። ሃይስኩል ላይ ኢንቨስት ካደረግን እኛ እሱ እንደ በቂ መወሰድ አለበት።

ዩኒቨርስቲ ሆኖ ገንዘብ አምጥቶ የራሱን ደመወዝ መክፈል የማይችል ከሆነ ኢትዮጵያን ማሳደግ አይችልም ማለት ነው።

ሃርቫርድ መንግሥትን አይጠይቅም በጀት፣ ኦክስፎርድ አይጠይቅም በጀት፣ ኬንያም ዩጋንዳንም ብትሄድ አይጠይቅም በጀት፣ እዚህ ግን ቀለቡም፣ ደመወዙም ሁሉም ነገር የሚጠየቅ ከሆነ ችግር አለ።

ሁለተኛ የዩኒቨርስቲ መምህር ስታንዳርድ አለው። በሴሚስተር አራት ክሬዲት ሃወር፣ አምስት ክሬዲት ሃወር አስተምረህ የዩኒቨርስቲ መምህር ነኝ አይባልም። ተጋባዥ መምህር ነኝ ነው የሚባለው። ማነው ሙሉ ጊዜ መምህር ለመባል የሚያበቃ ስራ እየሰራ ያለው የሚለውን ማየት አለባችሁ። ይሄ ብዙ ችግር አለ።

ሁሉም የዩኒቨርስቲ መምህር በርግጠኝነት የምነግራችሁ በቂ ደመወዝ አያገኝም። ደመወዙ ያንሳል ፣ ኑሮው ዝቅተኛ ነው ትክክል ነው። መቀየር አለበት። ነገር ግን ኢትዮጵያንም ማሰብ ጥሩ ነው። እዳ ተጭኖን፣ ዋጋ ግሽበት ሊገድለን፣ ጦርነት እያለብን፣ የዓለም ተጽዕኖ በዝቶብን ፕሮጀክቶች እዚህም፣ እዚያም፣ እዚያም ጥደን እያረሩብን፣ አያዋጣም !

የከፋው ደግሞ የዩኒቨርስቲ መምህር ሃላፊነቱን ዘንግቶ የፖለቲካ አጀንዳ መጫወቻ ሲሆን ደግሞ በጣም መጥፎ ነው። አሉ እንደዛ ምልክቶች! ይሄ መስተካከል አለበት።

የዩኒቨርስቲ መምህራን በሃሳብ እንዲያግዙን እንፈልጋለን። አሁን ካለንበት ችግር ከዋጋ ግሽበቱ ፣ ከፕሮጀክቱም ፣ ከድህነቱም እንድንወጣ ፣ የምንጠብቀው እነሱን ነው። ይቺ አገር ከሌላት አንጡራ ሃብት ላይ መንዝራ መቀነቷን ፈታ አስተምራቸዋለች፣ ያለችበትን ችግር መፍታት የእኔም የእነሱም እዳ ነው። "

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete
11.4K viewsedited  15:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 08:22:29
ማይክ ታይሰን በዘመኑ ስንቱን በፈርጣማ ክንዶቹ ሪንግ ውስጥ ሲያጋድም ፣ ብዙዎች ቀና ብለው በሙሉ አይናቸው ለማየት የሚፈሩት እልኸኛ የነበረ ሰው ነው።

ዛሬ በውልቸር የሌሎች ሰዎችን እርዳታ የሚፈልግ ለመቆም ምርኩዝ የሚፈልግ ደካማ ሆኖዋል።

ወዳጄ ሰው እስከሆንክ ድረስ ጀግንነትህ ጊዜያዊ ነው።

የተሰጠህን የጀግንነት ጊዜ ለነገ ምርኩዝ እንዲሆንህ ትሁት ሁን ፤ ዘላለማዊ ጀግና ፈጣሪ ብቻ ነው።

@temhert_bebete
@temhert_bebete
10.8K viewsedited  05:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-21 11:31:08
ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የአንደኛ ዓመት የድህረ ምረቃ ተማሪዎች የ2014 የትምህርት ዘመን የሁለተኛ ሴሚስተር ምዝገባ ከነሐሴ 26 እስከ 28/2014 ዓ.ም #በኦንላይን ብቻ የሚከናወን መሆኑን ገልጿል።

(ተጨማሪ መረጃ ከላይ ተያይዟል።)

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete
11.3K views08:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-23 18:59:01
በክፍል ዉስጥ የነበሩ 85 ተማሪዎችን ከጎርፍ አደጋ መታደጉን የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ገለጸ፡፡

ዛሬ ከቀኑ 7፡00 ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 ልዩ ቦታዉ ፊጋ እየተባለ በሚጠራዉ አካባቢ በሚገኘዉ ኒዉ ፖራዳይ መዋለ ህጻናት ትምህርት ቤት በክፍል ዉስጥ የነበሩ እድሜያቸዉ ከ4 እስከ 7 የሆኑ 85 ተማሪዎች ከዋናዉ መንገድ ጥሶ በክፍል ዉስጥ በገባዉ ጎርፍ ተከበው እንደነበር ተገልጿል።

የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ወደ ቦታዉ በመገኘት ከትምህርት ቤቱ ማህበረሰብ ጋር በመተባበር ሰማናንያ አምስቱንም ተማሪዎች ምንም ዓይነት ጉዳት ሳይደርስባቸዉ በጎርፍ ከተያዙበት ክፍል ዉስጥ በሰላም ማዉጣት መቻሉን የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያዉ አቶ ንጋቱ ማሞ ተናግረው ክረምቱ የሚበረታ በመሆኑ ሁሉም ህብረተሰብ ከኮሚሽን መስሪያ ቤቱና ከሚመለከታቸዉ ተቋማት የሚተላለፉ የጥንቃቄ መልእክቶችን ተግባራዊ እንዲያደርግም ኮሚሽኑ አሳስቧል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete
3.8K views15:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ