Get Mystery Box with random crypto!

ትምህርት በቤቴ🔝

የቴሌግራም ቻናል አርማ temhert_bebete — ትምህርት በቤቴ🔝
የቴሌግራም ቻናል አርማ temhert_bebete — ትምህርት በቤቴ🔝
የሰርጥ አድራሻ: @temhert_bebete
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.20K
የሰርጥ መግለጫ

A channel created for sharing
🔺study tips,
🔺short notes,
🔺tutorials,
🔺educational news,
🔺life tips and some motivational quotes ...
For comment @Tmhert_bebete_info_bot
Buy ads: https://telega.io/c/temhert_bebete

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 20

2022-06-08 14:54:52
የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያ ዲግሪ በCOC Level IV በማታ እና በቅዳሜና እሁድ ለመማር አመልክታችሁ የተመረጣችሁ የመግቢያ ፈተና እሁድ ሰኔ 05/2014 ዓ.ም እንደሚሰጥ ገልጿል።

ፈተናው በተጠቀሰው ቀን ከጠዋቱ 2:00 ጀምሮ በዩኒቨርሲቲው ግቢ ይሰጣል።

ለፈተናው የተመረጡ አመልካቾች ዝርዝርን በተከታዩ ሊንክ ይመልከቱ፦

http://www.ecsu.edu.et/notice/list-candidates-ba-extension-and-weekend

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete
3.8K views11:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-08 08:45:16
FreelanceEthiopia

በትርፍ ሰዓትዎ ከሚሰርዋቸው ሥራዎች ጀምሮ እንደ ትምህርት ደርጃዎ፣ የሥራ ልምድዎ እና ፍላጎትዎ በሁሉም አይነት ዘርፎች ሁሉንም አይነት ሥራዎች በአንድ ቦታ ያገኛሉ።
1.4K views05:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-07 22:56:57
ማሳሰቢያ

“የኢትዮጵያ አገር በቀል እውቀት ዩኒቨርሲቲ” በሚል ስያሜ የተቋቋመ 'ተቋም' እንደሌለ የትምህርትና ስልጣና ባለሥልጣን አሳውቋል።

የትኛውም የከፍተኛ ትምህርት ተቋም መቋቋም የሚችለው በአዋጅ ቁጥር 1152/2011 እንዲሁም በሚንስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 515/2014 መሰረት ከትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ፈቃድ ሲያገኝ ብቻ መሆኑን ባለሥልጣኑ አስታውሷል፡፡

ይሁን እንጂ “የኢትዮጵያ አገር በቀል እውቀት ዩኒቨርሲቲ” በሚል መጠሪያ ግንቦት 29/2014 ዓ.ም እንደተቋቋመ በመግልጽ በማህበራዊ ድረ-ገጽ እየተዋወቀ የሚገኝው "ተቋም" እውቅና የሌለው መሆኑን ባለስልጣኑ ገልጿል።

“የኢትዮጵያ አገር በቀል እውቀት ዩኒቨርሲቲ” በማለት ራሱን እያስተዋወቀ የሚገኘው "ተቋም"፤ ከባለሥልጣኑ ምንም አይነት ፈቃድ ያልተሰጠው እንደሆነ ተመላክቷል።

በቀጣይ አስፈላጊውን ማጣራት በማድረግ ህጋዊ የማስተካከያ እርምጃ እንደሚወስድ ባለስልጣኑ አሳውቋል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete
3.2K views19:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-07 21:08:03
ኢትዮ ቴሌኮም

ኢትዮ ቴሌኮም ከሀገር ውጪ ባለው ከፍተኛ የባንድዊድዝ ተሸካሚ የኢንተርኔት መገናኛ መስመሮቹ ላይ ባጋጠመው ችግር ምክንያት የኢንተርኔት አገልግሎት መቆራረጥ ወይም የፍጥነት መቀነስ ሊያጋጥም እንደሚችል አሳዉቋል፡፡

ደምበኞቹ በትዕግስት እንዲጠብቁም ዛሬ ጠይቋል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete
4.2K views18:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-06 20:29:35
ብሄራዊ ባንክ ለክሪፕቶ መገበያያ ገንዘብ እና ለምናባዊ ንብረት (ቨርቱዋል እሴቶች) ዕውቅና እንደማይሰጥ ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። አንዳንድ ክሪፕቶ ገንዘብን በሕገወጥ መንገድ እየተጠቀሙ እና በወንጀል የተገኘ ገንዘብን ለማሸሽ እያዋሉት እንደሆነ የገለጸው ባንኩ፣ ገንዘቡን የሚጠቀሙ አካላት ላይ ርምጃ እንደሚወስድ ገልጧል። ከአገሪቱ ኦፊሴላዊ መገበያያ ገንዘብ ውጭ ሌላ መገበያያ ዘዴ መጠቀም የሚፈልጉ አካላት፣ መጀመርያ ከባንኩ ፍቃድ ማግኘት እንዳለባቸው ባንኩ ጨምሮ ገልጧል።


መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete
2.6K views17:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-05 20:13:01
የምዝገባ ጥሪ ማስታወቂያ

ለክረምት መርሀ-ግብር ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ፦

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲበ 2014 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በመጀመሪያ ዲግሪ፣ በሁለተኛ ዲግሪ እና በ PGDT ፕሮግራም በት/ት ሚኒስቴር መስፈርት መሰረት አዲስ አመልካቾችን ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል። በመሆኑም መስፈርቱን የምታሞሉ አመልካቾች ከዚህ በታች በተገለፁት የትምህርት መስኮች ከግንቦት 29/2014 እስከሰኔ 17/2014 ዓ.ም መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን። #ዩንቨርሲቲው


መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete
3.4K views17:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-05 16:39:47
DON'T MISS THIS GREAT OPPORTUNITY FOR THE COMING SEPTEMBER 2022 INTAKE

For Masters Degree
- Secure your full scholarship plus pocket money of 5300€ per year to cover your expenses
- For all fields

For those who want to apply for bachelor's, send us a message on our telegram channel

@abeltravels

- Apply with your Transcript and Passport

For more info, feel free to contact us at:

+251913793620
+393382688535 (whatsapp)

ADDRESS:
22, Tigat Building
3rd floor, Office no.32
4.3K views13:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-04 08:31:19 ነገን በምን አውቀን ነው ተስፋ የምንቆርጠው !

ዛሬ ላይ ቆመህ ስታይ ትላንት እንዲህ ትሆን እንደነበር ታውቀው ነበር? ዛሬ አዲስ እና ያልተጠበቀች ቀን ነች አይደል? ችግሩ ፣ የሚያስከፋህ ነገር ፣ ደስታው ፣ እድሉ ሁሉም ዛሬን በመኖራችን የተሰጡን ሽልማቶች ናቸው።

ታድያ ነገስ ምን ይዞልህ እንደሚመጣ መች አወቅከውና ነው ተስፋ የምትቆርጠው! መኖር ደጉ ብዙ ያሳየናል አይደል የሚባለው እንዳንተ ያልታደሉ ዛሬን እየናፈቁ ያላዩ ስንት አሉ? እህቴ መኖርሽን አጣጥሚው ይሄን አለም እንጂ ያን መች አየሽው ነገንስ መች አወቅሽው መኖርን የሚያህል እድል የሠጠሽ አምላክሽ ታሪክሽን ለመቀየር ይሳነዋል እንዴ ?


ምርጥ ቀን ተመኘን
#Inspire_Ethiopia

@temhert_bebete
@temhert_bebete
4.5K viewsedited  05:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-03 17:54:27
ክቡር ኮሌጅ በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስደው ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ለመግባት ዝግጅት ላይ ለሚገኙ ተማሪዎች ሲሰጥ የቆየውን ነጻ የክህሎት ስልጠና ነገ ያጠናቅቃል።

ከአዲስ አበባ እና ከሰበታ ከተማ ከሚገኙ ከ75 በላይ የመንግስት እና የግል ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ ከ500 በላይ ተማሪዎች በስልጠናው ተሳትፈዋል።

College and Career Readiness Bootcamp የተባለው ስልጠናው፤ ተማሪዎቹ ለቀጣይ ሙያቸውና ህይወታቸው የሚያስፈልጋቸውን ክህሎት ያገኙበት መሆኑን የክቡር ኮሌጅ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ደሳለኝ መኩሪያ ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ገልጸዋል።

ከግንቦት 04/2014 ዓ.ም ጀምሮ በተሰጠው ስልጠና፤ ተማሪዎቹ በ12 የስልጠና አይነቶች የህይወት እና የቴክኖሎጂ ክህሎታቸውን እንዲያዳብሩ መደረጉን ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል።

የስልጠናው ማጠቃለያ ዝግጅት ነገ ግንቦት 27/2014 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ጀምሮ ብስራተ ገብርኤል በሚገኘው አዶት ሲኒማ ይካሄዳል ተብሏል።

ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምሁራን፣ የፈጠራ ባለሙያዎች እና ሌሎችም በማጠቃለያ መርሃ ግብሩ እንደሚገኙ ይጠበቃል።

በመድረኩ ምሁራን ልምዳቸውን የሚያካፍሉ ሲሆን ለሰልጣኞች የተሳትፎ ምስክር ወረቀት ይሰጣል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete
4.0K views14:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-02 21:50:07
ኢትዮ ቴሌኮም 66 ትምህርት ቤቶችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የዲጂታል ትምህርት ማዕከል ፕሮጀክት አስጀምሯል።

ፕሮጀክቱ በአገር ዐቀፍ ደረጃ 66 ትምህርት ቤቶችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ሲሆን 48 ትምህርት ቤቶች በክልሎች እና 18 ትምህርት ቤቶች በአዲስ አበባ እንደሆኑ ተገልጿል፡፡

Bridging Divide Digital Center የተባለው ፕሮጀክቱ፤ 140 ሺህ 596 ተማሪዎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ የኢትዮ ቴሌኮም ሥራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ ገልጸዋል።

ትምህርት ቤቶቹ የመሠረተ ልማት ችግር ያለባቸው መሆኑን የገለጹት ሥራ አስፈጻሚዋ፤ ለትምህርት ቤቶቹ የኮምፒውተር፣ የኢንተርኔት እና የትምህርት መሠረተ ልማቶች የተሟላላቸው መሆኑን ተናግረዋል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete
2.1K views18:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ