Get Mystery Box with random crypto!

ሰሌዳ | Seleda

የቴሌግራም ቻናል አርማ seleda_business — ሰሌዳ | Seleda
የቴሌግራም ቻናል አርማ seleda_business — ሰሌዳ | Seleda
የሰርጥ አድራሻ: @seleda_business
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 80.41K
የሰርጥ መግለጫ

ጠንካራ በመረጃ የተደገፈ የቢዝነስ ውሳኔዎች!
ቢዝነስ እና ቴክ ተኮር መረጃዎች
ጨረታዎች እና ሃራጆች

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-10-11 14:39:36
በፈረንጆቹ 2030 በከፍተኛ ሙቀት ምክንያት ከ2 ነጥብ 4 ትሪሊየን ዶላር በላይ ኪሳራ ይከሰታል ተባለ።

ዓለማችን በፈረንጆቹ 2030 ከከፍተኛ ሙቀት መጨመር ጋር ተያይዞ ከ2 ነጥብ 4 ትሪሊየን ዶላር በላይ የኢኮኖሚያ ኪሳራ እንደሚያጋጥማት ዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ኮሚቴ እና የተመድ የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ጽኅፈት ቤት (ኦቻ) ሰኞ ዕለት በጋራ ባወጡት ሰነድ ይፋ አድርገዋል፡፡

ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው በዝቅተኛ የኢኮኖሚ ደረጃ ላይ የሚገኙ የኅብረተሰብ ክፍሎች የሚኖሩባቸው ከተሞች ለሙቀት መጨመር የሚኖራቸው ተጋላጭነት ይበልጥ እንደሚጨምር ነው ሠነዱ በትንበያው ያመላከተው፡፡ እንደ ሠነዱ ትንበያ ከሆነ እስከ 2050ዎቹ ድረስ የእነዚሁ ከተሞች ነዋሪዎች ቁጥር በሰባት እጥፍ ይጨምራል፡፡

በሙቀት መጨመር እንዲሁም ከዓየር ንብረት ለውጥ ጋር ተያይዞ በሚከሰቱ የካንሰር እና ሌሎች ተላላፊ በሽታዎች የሚከሰት ሞት በአሃዝ እንደሚጨምርና በተለይም ታዳጊ ሀገራት ይበልጥ የችግሩ ገፈት ቀማሽ እንደሚሆኑም ነው የተመላከተው። በዓየር ንብረት ለውጥ የሚከሰቱ የተፈጥሮ ሐብቶች መራቆት ፣ ሥደት እና የመሠረተ-ልማት ውድመቶችም ዓለማችን የምትጋፈጣቸው ችግሮች ናቸው ተብሏል፡፡
9.7K views11:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-11 09:01:29
ሁሉንም ዓይነት የጥበብ ስራዎችን በቀላሉ ማግኘት የሚያስችል “ሰዋሰው” የተሰኘ መተግበሪያ ይፋ ሆነ።

በቱ ኤፍ ካፒታል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር የተመሰረተው መተግበሪያው የተለያዩ የጥበብ ስራዎችን በክፍያም ሆነ ያለክፍያ አማራጮች መከታተል የሚያስችል ነው ተብሏል። ወደ 80 ገደማ የሚሆኑ አንጋፋና ወጣት ድምጻውያን ከአንድ ሺህ በላይ ሙዚቃዎችን ብሎም በመቶዎች የሚቆጠሩ የኪነጥበብ የፈጠራ ውጤቶችን ለማዘጋጀት ከድርጅቱ ጋር ውል አስረዋል።

የስነ ጥበብ ሰዎች ከቅጂ እና ተዛማጅ መብቶች ጋር በተያያዘ የሚገጥማቸውን ችግር ይቀርፋል የተባለው ይህ መተግበሪያ ለባለመብቶች የሮያሊቲ ክፍያ በአግባቡ የሚከፈልበት ስርዓት እንዳለውም ተገልጿል። ቱ ኤፍ ካፒታል በይፋ ካስመረቀው የሰዋሰው መልቲሚዲያ መተግበሪያ በተጨማሪ የፕሮዲዩሰርነት ስራ እንደሚሰራም የገለጸ ሲሆን በዚህም ተሰጥኦ ላላቸው የጥበብ ሰዎች ቅድመ ክፍያ በመክፈልና ወጪያቸውን በመሸፈን ሙዚቃቸውን እንዲያሳትሙ እንደሚያደርግ ሰምተናል ።
9.9K views06:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-10 20:23:51
ከአዲስ አበባ ወደ ኦሮሚያ ክልል የተካለሉ አካባቢዎች የቤት ግብይት አገልግሎት ተቋረጠ

የአዲስ አበባ እና ኦሮሚያ ክልል ወሰን መካለሉን ተከትሎ ከአዲስ አበባ ወደ ኦሮሚያ ክልል የተካለሉ አካባቢዎች ላይ የቤት ግብይት እና እግድ አገልግሎት መቋረጡን አዲስ ማለዳ ዘግባለች። በተካለሉት አካባቢዎች የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች፤ የቤት ሽያጭ፣ ግዢ፣ ሥም ዝውውርና እግድ አገልግሎት ከተቋረጠ በኋላ በአካባቢዎቹ የቤት ግብይት ቆሟል።

ከአዲስ አበባ ወደ ኦሮሚያ ክልል የተካለሉ አካባቢዎች ፋይል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና ኦሮሚያ ክልል ርክክብ ማድረጋቸውም ተሰምቷል። ምንም እንኳን የፋይል ርክክቡ የተከናወነ ቢሆንም፣ የኦሮሚያ ክልል አገልግሎት መስጠት አልጀመረም። ክልሉ ከአዲስ አበባ ከተማ ለተረከባቸው አካባቢዎች መቼ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር እና አገልግሎቱ የት እንደሚሰጥ በውል የታወቀ ነገር የለም።

via - አዲስ ማለዳ
10.8K views17:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-10 19:17:54
ፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት ከወንጀል ተግባር ጋር ግንኙነት ያላቸው የባንክ ሂሳቦችን አገደ::

ከህገ-ወጥ የውጭ አገራት ገንዘብ ማስተላለፍ ወንጀሎች ጋር ግንኙነት እንዳላቸው የተጠረጠሩ 665 የባንክ ሂሳቦች የታገዱት ህጋዊ የውጭ አገራት ገንዘብ ማስተላለፍ ፈቃድ ሳይኖራቸው፣ በህገ-ወጥ መንገድ በአገር ውስጥ እና በውጭ አገራት ከሉ አካላት ጋር ትስስር በመፍጠር በህገ-ወጥ መንገድ የገንዘብ ማስተላለፍ ተግባር ላይ ተሰማርተው የተገኙ መሆናቸውን የኢፌዲሪ የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት አስታዉቋል፡፡

የተለያዩ የወንጀል ድርጊቶችን በመፈፀም የተገኘን ሃብት ከህጋዊ ምንጭና በህጋዊ መንገድ የተገኘ በማስመሰል የመጠቀም ወንጀሎች አፈፃፀም በየጊዜው እየተቀያየረ ያለ ወንጀል ከመሆኑም ባሻገር፣ ከወንጀል ድርጊቶቹ የተገኘው ሃብት ሽብርተኝነትን በገንዘብ የመርዳት ወንጀል መፈፀሚያ ጭምር የሚውል በመሆኑ የመከላከልና መቆጣጠር ስራው በተጠናከረ አግባብ በመከናወን ላይ ነዉ ብሏል አገልግሎቱ።
10.8K views16:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-10 18:03:35
በአዲስ አበባ ከ18 ሺህ በላይ የንግድ ተቋማት ላይ እርምጃ ተወሰደ።

በመዲናዋ የዋጋ ንረቱን በማባባስና የንግድ ህጎችን በመጣስ ከ 18 ሺህ በላይ የንግድ ተቋማት ላይ ህጋዊና አስተዳዳራዊ እርምጃ መወሰዱን የከተማዋ ንግድ ቢሮ አሳውቋል። ቢሮው ከ95 ሺህ በላይ በሚሆኑ ተቋማት ላይ ክትትል አድርጎ ነው ከ18ሺህ በላይ ተቋማት ላይ እርምጃ የወሰደው። ከአስተዳደራዊ እርምጃው ባሻገር በ182 ተቋማት ላይ ህጋዊ እርምጃ ለመውሰድ ክስ መስርቷል።

ቢሮው የዋጋ ንረቱን ለማረጋጋት ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ ለህብረት ስራ ማህበራት የስራ እንቅስቃሴ መመደቡን የገለፀ ሲሆን የሸማቾች ህብረት ስራ ማህበራትን ቀጥታ ከአርሶ አደሮች ጋር በማገናኘት ምርት በብዛት ወደ አዲስ አበባ እንዲገባ መደረጉን ገልጿል። ከዚህም በተጨማሪ በከተማዋ 97 የእሁድ ገበያዎችን በማቋቋም ህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲገበያይ ማድረጉን አሳውቋል።

via - Reporter
10.3K views15:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-10 15:02:57
በቅጣት ምክንያት የተሽከርካሪዎችን ሰሌዳ የመፍታት እርምጃ እንዲቆም ጥያቄ ቀረበ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንገድ ደህንነት ምክር ቤት የተጠናቀቀው የበጀት አመት እቅድ አፈፃፀምን አስመልክቶ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ባደረገው ዉይይት ወቅት የትራፊክ ደንብ በተላለፉ አሽከርካሪዎች ላይ ለቅጣት በሚል ምክንያት የተሽከርካሪዎችን ሰሌዳ የመፍታት እርምጃ ህግን ካለማስከበሩም ባሻገር ለሀገር ሀብት ብክለት ምክንያት በመሆኑ እርምጃው ሊጤንና ሊቆም እንደሚገባ ጥያቄ ቀርቧል።

በመድረኩ እርምጃው ለሌላ አደጋ ስለሚዳርግ ሁሉም ባለድርሻ አካላት መፍትሔ ሊያበጁለት ይገባል የተባለ ሲሆን በተጨማሪም አቅጣጫ ለመያዝ ብቻ ተብሎ ተቆርጠው የሚወጡ ሰሌዳዎች በርካታ በመሆናቸው በዚህ መሀል የሀገር ሀብት እንደሚባክን ተጠቁሟል። አገሪቱ በተጠናቀቀው በጀት አመት በግብአት እጥረት ምክንያት ሰሌዳ ለማምረት ተቸግራ እንደነበርም በመድረኩ ተነስቷል።

via - Reporter
10.9K views12:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-10 13:25:05
ሳፋሪኮም 5ጂ ለማስጀመር ቢያንስ እስከ ሶስት አመት እንደሚጠብቅ አስታወቀ።

ኩባንያው እስካሁን አገልግሎቱን በጀመረባቸው አካባቢዎች ያቀረበው 4ጂ ድረስ ያለውን የኢንተርኔት አገልግሎት ሲሆን የ5ጂ አገልግሎት ለማስጀመር የሚያስችለውን ስፔክትረም ምደባ ለማግኘት ለኢትዮጵያ ኮሚኒኬሽን ባለስልጣን ጥያቄ ማቅረቡ ተሰምቷል። ባለስልጣኑ ጥያቄውን በማየት ላይ እንደሚገኝና ማብራሪያ የሚፈልጉ ጉዳዮች ላይ ጥያቄ ማቅረቡን ገልጿል።

እንደ ኩባንያው ስራ አስፈፃሚ አንዋር ሶላ ገለፃ ሳፋሪኮም 5ጂ የሚያስጀምርበት ጊዜ የሚወሰነው በሀገሪቱ ውስጥ ምን ያህል 5ጂ የሚያስጠቅሙ መሳሪያዎች አሉ በሚለው ላይ ተመስርቶ ነው። 5ጂ የሚጠቀሙ ሰዎች ቁጥር አነስተኛ በመሆኑ 5ጂ የሚያስጠቅሙ መሳሪያዎች በብዛት እስከሚገኝ ድረስ እንደሚጠብቅ ገልፀዋል።

via - Reporter
10.5K views10:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-10 12:09:31
ኢትዮጵያ ለጎረቤት ሀገራት ከሸጠችው የኤሌክትሪክ ሃይል ከ13 ሚሊየን ዶላር በላይ ገቢ ማግኘቷ ተገለፀ።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባለፉት ሁለት ወራት ለሱዳን እና ጂቡቲ 232 ነጥብ 76 ሚሊየን ኪሎ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ የ13 ነጥብ 04 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ሽያጭ በማከናወን የዕቅዱን 70 በመቶ ማሳካት መቻሉን አስታውቋል፡፡ ምንም እንኳን ለኹለቱ አገራት የተከናወነው ሽያጭ በጥቅል ሲታይ ከዕቅዱ በታች ቢሆንም፤ ከጅቡቲ የተገኘው ገቢ ግን ከዕቅዱ የ15 ነጥብ 38 በመቶ ብልጫ ያሳየ እንደነበር ተገልጿል፡፡
 
ለሱዳን 112 ነጥብ 36 ሚሊየን ኪሎ ዋት ሰዓት ኃይል በማቅረብ የ5 ነጥብ 61 ሚሊየን ዶላር የተገኘ ሲሆን ለጂቡቲ ደግሞ 120 ነጥብ 39 ሚሊየን ኪሎ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ የ7 ነጥብ 42 ሚሊየን ዶላር መገኘቱ ተጠቁሟል፡፡ በሁለቱ ወራት ለጎረቤት ሀገራት የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ ከተገኘው ገቢ በተጨማሪ ከሀገር ውስጥ የኃይል ሽያጭና ከፋይበር ኦፕቲክስ ኪራይ ከ2 ነጥብ 74 ቢሊየን ብር በላይ መገኘቱ ተጠቁሟል፡፡

via - ENA
10.6K views09:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-10 10:09:26
ግዙፉ የብስኩት ፋብሪካ ቱ ብራዘርስ ፉድ ኮምፕሌክስ በግብዓት እጥረት ምክንያት ስጋት ላይ መሆኑን አስታወቀ።

የፋብሪካው የፕሮዳክሽን ኃላፊ አቶ አደም ከማል የፋብሪካው በርካታ የማምረቻ መሳሪያ ጥሬ እቃዎች ከውጭ እንደሚገቡ ገልፀው የውጭ ምንዛሬ እጥረቱ ሥራውን በአግባቡ እንዳይሰራ ከፍተኛ ተግዳሮት እንደሆነበትና ይህንንም በተቻለ መጠን የሚመለከተው የመንግሥት አካል ትኩረት እንዲሰጠው መጠየቃቸውን ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ተናግረዋል።

እንደ ሀላፊው ገለፃ ፋብሪካው አሁን ላይ 34 የብስኩት አይነቶችን ለአገር ውስጥ ገበያ ለማምረት የሚያስችል ማሽነሪዎች ቢኖሩትም፤ በቅርቡም ከኢትዮጵያ አልፎ የብስኩት ምርቱን ወደ ጎረቤት ሀገራት ኤክስፖርት ለማድረግ ለያዘው እቅድ የተፈጠረው የዶላር ችግር ከውጭ የሚያስፈልጉ ጥሬ ዕቃዎችን እንዳያስገባ ከፍተኛ የሆነ ተግዳሮት ሆኖበታል ብለዋል።

በኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የወጪ ምርቶች መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዘሪሁን አበበ በበኩላቸው፤ የውጭ ምንዛሬ ፍላጎቱ ከአጠቃላይ አገራዊ ጉዳይ ጋር ተያይዞ የመጣ ተጽእኖ መሆኑን ተናግረው ከውጭ ምንዛሬ ፍላጎት ጋር ተያይዞ ኤክስፖርት የሚያደርጉ እንዱስትሪዎችና ስትራቴጂ ተኪ ኢንዱስትሪዎች እንደ የሁኔታቸው እየታየ ቅድሚያ የሚያገኙበት ሁኔታ ለማመቻቸት ውይይት መደረጉንና አቅጣጫ እስኪሰጥበት እየተጠበቀ መሆኑን አስታውቀዋል።

via - ENA
10.7K views07:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-10 08:40:30
መንግስት የገንዘብና የበጀት ፖሊሲውን ለመከለስ ውይይት እያደረገ መሆኑን ተነገረ።

መንግስት የገንዘብ፣ የበጀት እና ሌሎች ዘርፎችን የሚነኩ ፖሊሲዎችን ክለሳ በማድረግ ለመተግበር ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ዋዜማ ዘግባለች። በቁጥጥር ስር ሊውል ያልቻለው የዋጋ ንረት ፣ የውጭ ምንዛሬ እጥረት ፣ እንዲሁም እጥረቱን ተከትሎ በባንክ እና በጥቁር ገበያ መካከል የተፈጠረውን የተጋነነ የዋጋ ልዩነት ምክንያት ሆኖ በቅርቡ አዲስ የፖሊሲ ማሻሻያዎች እንደሚኖሩም ዘገባው ጠቅሷል።።

መንግስት የገንዘብ ፖሊሲን አሁን የሚያሻሽል ከሆነ በአንድ ዓመት ለሶስተኛ ጊዜ ይሆናል። ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ የዋጋ መረጋጋት ያመጡልኛል ያላቸውን ሁለት የገንዘብ ፖሊሲ ማሻሻያዎችን ቢተገብርም የዋጋ ንረቱ የመቀነስ አዝማሚያን አላሳየም። በተቃራኒው ማሻሻያዎቹ የዋጋ ንረቱን ያባብሳሉ የሚሉ ትችቶች በኢኮኖሚ ባለሙያዎች ሲቀርቡበትም ቆይቷል።

ባለፈው አመት በጥቁር ገበያው የአንድ አሜሪካ ዶላር ዋጋ 65 ብር ደርሶ ከባንክ ምንዛሬ ጋር የ20 ብር ልዩነትን ማሳየቱን ተከትሎ መንግስት የኢኮኖሚ አሻጥር ውጤት ነው በሚል የተለያዩ እርምጃዎችን መውሰዱ ይታወሳል።  በዚህም የቤት ሽያጭን እንዲሁም የባንክ ብድርን ወዲያው ነበር ያገደው።

እርምጀውን ተከትሎም የጥቁር ገበያው ዋጋ ወርዶ ከባንክ ጋር ያለው ልዩነት ጠቦ ቢቆይም በሂደት የተቀመጡ እግዶች ሲነሱ የሰሜኑም ጦርነት ለሶስተኛ ጊዜ ሲያገረሽ የውጭ ምንዛሬ መዛነፎች እንደገና አገርሽተዋል። አሁን መንግስት እያደረገ ያለውን ምክክር ሲያጠቃልል ከፖሊሲ እርምጃዎችና ከገንዘብ ባለፈ የበጀት እና ሌሎች ማእቀፎችን አካቶ ተግባራዊ እንደሚሆን ይጠበቃል ።

via - wazema
10.9K views05:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ