2023-05-13 09:02:41
አቶ አወቀ ስንሻው ከታፈነ ዛሬ ዘጠንኛ ቀኑ ተቆጠረ
ንሥር ብሮድካስት
ግንቦት 5/2015
አቶ አወቀ ስንሻው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሰራተኛና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሰራተኞች ማህበር ስራ አስፈፃሚ ነው።
ከሚኖርበት ልደታ ትፈለጋለህ ተብሎ ከተወሰደ ዛሬ 9 ቀኑ አልፏል።
ለህጋዊ ጠበቃዎችም ሆነ ለቤተሰቡ የአካል ደህነነቱንም ሆነ የት እንዳለ አፈና የፈፀሙበት አካላት አላሳወቁም።
አወቀ እጅግ በተቀለጠፈ የተግባቦት ችሎታው ከሁሉ የሚጫወት ቀና ወንድም ነው።
የፍኖት ማይክሮ ፋንናንስ መስራችና መሪ ነው እንስራ እንለወጥ ከማለት ውጭ ምንም አይነት የፖለቲካ ተሳትፎ የለውም።
የአንድ ህፃን ልጅ አባት የሆነው አወቀ እስካሁን የት እንዳለ ማወቅ አልተቻለም።
ወቅታዊ ፤ ትኩስ እና የተሟላ መረጃዎችን ለማግኘት
Youtube: https://www.youtube.com/@nisir/videos
FaceBook Page 1 : https://www.facebook.com/Nisirbroadcast
FaceBook Page 2: https://www.facebook.com/Nisirmereja
Telegram: https://t.me/nisirbroadcasting
Website: https://nisirbroadcasting.com
Twitter: https://twitter.com/NISIRInternati1
Instagram: https://www.instagram.com/nisirbroadcast/
ንሥር ብሮድካስትን በወዳጅነት ይከታተሉን።
1.4K views06:02