Get Mystery Box with random crypto!

ችሎት ዜና ፍ/ቤቱ  ፖሊስ በጋዜጠኞቹ ላይ የጠየቀውን ተጨማሪ 14 ቀናት የምርመራ ጊዜ ፈቀደ   | NiSiR Int. Broadcasting Co. (Official Telegram Channel)

ችሎት ዜና

ፍ/ቤቱ  ፖሊስ በጋዜጠኞቹ ላይ የጠየቀውን ተጨማሪ 14 ቀናት የምርመራ ጊዜ ፈቀደ

         ንሥር ብሮድካስት
         ግንቦት 4/2015

ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው እና ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ አስፋው ዛሬ ግንቦት 4 ቀን 2015 ዓ.ም ከረፋዱ 4:00 ላይ በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ አንደኛ ወንጀል ችሎት ቀርበው ነበር::

ጋዜጠኞቹ በሁከትና ብጥብጥ ተጠርጥረዋል በሚል ቀደም ሲል አራዳ ፍርድ ቤት ቀርበው በዋስ እንዲወጡ ተወስኖላቸው የነበረ ሲሆን የፌደራል ፖሊስ ውሳኔውን በመተው በሌላ "በሽብር" ጠርጥሬያቸዋለሁ በሚል ነው ወደልደታ ፍርድ ቤት ያዛወራቸው::

ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርበው በጠበቆቻቸው በኩል ጥፋተኛ አለመሆናቸውንና ህጉ ከሚፈቅደው ውጭ ጋዜጠኞቹ በቅድመ እስር እየተጉላሉ መሆኑን  ተከራክረዋል::

በዋስ ወተው ጉዳያቸውን በውጭ እንዲከራከሩም ጠይቀው ነበር::

ይሁንና ፍርድ ቤቱ መርማሪ ፖሊስ የጠየቀውን የ14 ቀን ቀጠሮ ፈቅዷል ሲል ጋዜጠኛ አራጋው ሲሳይ አጋርቷል።

ወቅታዊ ፤ ትኩስ እና የተሟላ መረጃዎችን ለማግኘት
Youtube: https://www.youtube.com/@nisir/videos

FaceBook Page 1 :    https://www.facebook.com/Nisirbroadcast

FaceBook Page 2:  https://www.facebook.com/Nisirmereja      

Telegram:    https://t.me/nisirbroadcasting

Website: https://nisirbroadcasting.com

Twitter:   https://twitter.com/NISIRInternati1

Instagram:  https://www.instagram.com/nisirbroadcast/
ንሥር ብሮድካስትን በወዳጅነት ይከታተሉን።