Get Mystery Box with random crypto!

The Niles ናይል 🇪🇹

የቴሌግራም ቻናል አርማ nileabay — The Niles ናይል 🇪🇹 T
የቴሌግራም ቻናል አርማ nileabay — The Niles ናይል 🇪🇹
የሰርጥ አድራሻ: @nileabay
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 5.61K
የሰርጥ መግለጫ

news,article ,interview and analysis on nile and international issues .
በአባይ እና ከሃገራችን ጋር ተያያዥ በሆኑ አለምአቀፍ ጉዳዮች ዜና፣ሀተታ ፣ቃለ መጠይቅ እና ትንታኔ ያገኛሉ

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-09-01 21:14:59       በዚህ ረገድ አሁንም ኢትዮጵያውያን መናጋት የለባቸውም፡፡ ነቅተው፣ ተደራጅተውና ተደማምጠው የጠላትን ሴራ ማምከንና ግድቡን ከዳር ለማድረስ መረባረብ ይኖርባቸዋል፡፡ በተለይ ሚዲያዎቻችንና የማኅበረሰብ አንቂዎች፣ ትምህርት ቤቶችና የምርምር ተቋማት ከተለመደው አሰልቺ ነገር ወጥተው ለጉዳዩ ጠንከር ያለ ትኩረት ሊሰጡ ይገባል፡፡ የማንንም ፈቃድ ሳይጠብቁም ለመጪው ትውልድ የተሻለች አገር ለማስረከብ ዓባይ ዓባይ ማለት አለባቸው፡፡

     ሕዝባችንን በበቂ ሁኔታ ስለግብፅም ሆነ ስለሌሎች የኢትዮጵያ ጠላቶች ስትራቴጂካዊና ጂኦ ፖለቲካዊ ፍላጎቶች ማሳወቅ፣ ማስተማርና ማንቃት የዘወትር አጀንዳ መሆን አለበት። ጠላቶቻችን የሚሠሩት ለአሉታዊ ትርክትና ለኢፍትሐዊ ተጠቃሚነትም ሲሆን፣ የራሳቸውን ሕዝብ በማንቃትና ወጥ አመለካከት እንዲኖረው በማድረግ ላይ አተኩረው ነው፡፡

     የእኛ የሕዝብም ይባሉ አብዛኞቹ የግል ሚዲያዎች የጠላትን ፕሮፓጋንዳ ለማምከንና ሕዝባችን ለብሔራዊ  ጥቅሙ መከበር በአንድ እንዲቆም ለማድረግ ብርቱ ሥራ መከወን እንደሚጠበቅባቸው ማስታወስ ያስፈልጋል። የግብፅ ሴራ በውስጥ ካሉ የአገር (የመንግሥት አላልኩም) ባላንጣዎች ዘመቻ ጋር ተቀናጅቶ የቀጠለ ሲሆን፣ ይህን ሰባብሮና አንኮታኩቶ መጣል፣ አሸናፊነታችንን በሁሉም መስክ ማስቀጠል የእኛና የእኛ ኃላፊነት ብቻ መሆን ይኖርበታል፡፡ የካይሮና ሼሪኮቻቸው ሴራ ቢያይልም፣ ዓባይ ለወገኑ ትሩፋት ከመሆን የሚገታው የለም ብሎ አፍ ሞልቶ መናገር የሚቻለውም ይህንኑ በማድረግ ብቻ ነው፡፡
502 views18:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 21:14:59 በስፋት እንዲንቀሳቀሱ የሚያደርግ መሆኑ ነው፡፡

     የግብፅ ሌላኛው ሥልት በሃይማኖቶቻችን መካከል ያሉትን የግንኙነት ድሮች ለመበጣጠስና በሃይማኖት ሰበብ አገር እንዲተራመስ ማድረግ ነው፡፡ ሙስሊሙ ኅብረተሰብ ከመንግሥት ጎን እንዳይሠለፍና ከክርስቲያኑ ኅብረተሰብም ጋር ተባብሮና ተከባብሮ እንዳይኖር የአሏህ ሕዝብ (Hizbu-Allah) እና የሰይጣን ሕዝብ (Hizbu Shaitan) በሚል ፈሊጥ እየከፋፈሉ የሕዝቡን አንድነት ለማናጋት መክረማቸው ብቻ ሳይሆን፣ በቅርቡ በአልሸባብ ዳግም ጥቃትም ሞክረዋል፣ የተሳካ ባይሆንም፡፡

     በዚህ ረገድ በውስጣችን ያሉትን አክራሪ ኃይሎች በገንዘብ በማጠናከርና በማደራጀት ይህንኑ የመከፋፈያ መርዝ እንዲረጩ፣ ሁከትና ሽብር እንዲፈጥሩ፣ ወኔ ሰላቢ የሆኑ ፕሮፓጋንዳዎችን እንዲያሠራጩ፣ ከፍተኛና አሰቃቂ የኃይል ዕርምጃዎችን በሰላማዊ ዜጎች ላይ እየወሰዱ ሕዝቡ እንዲሸማቀቅ ለማድረግ መኳተናቸውን መካድ አይቻልም፡፡ ይህ እኩይ የሆነ የእሾህን በሾህ ሴራ ሥልታቸው በፊትም የነበረና የቀጠለ ነው፡፡

       የግብፅ ፖለቲከኞች  የሚሉትን ሁሉ ቢሉ፣ የሚጮኹትንም ያህል ቢጮሁ፣ የኢትዮጵያ መንግሥትና ሕዝብ ማድረግ ያለባቸውን እያደረጉ የግድቡን ሥራ አጠናክረው በመቀጠላቸው የተደረሰበት ደረጃ ላይ መድረስ ተችሏል፡፡ ዋናው ሥራን በአግባቡና በትኩረት መሥራት እንጂ፣ የእነሱ ጩኸትና ማስፈራሪያ እንደማይበግረንና ሥራችንን የሚያስተጓጉል የገንዘብና የፀጥታ ችግር እንደሌለብን በተግባር ማሳየት በመቻላችን እንደ ሕዝብና አገር ልንኮራም ይገባል፡፡

      ለወደፊቱም ቢሆን በግብፅ ፖለቲከኞችና ሐሳዊ መሲህ ምሁራን ወሬ መፈታት የለብንም፡፡ የእነሱ ፕሮፓጋንዳ ሰለባ መሆንም አይገባም፡፡ ስለኃይል ማመንጫ ግድባችን ትክክለኛውንና ወቅታዊውን መረጃ የምናገኝበት ተቀዳሚ ምንጫችን የእኛው የራሳችን መንግሥትና የግድቡ ሥራ ብሔራዊ አስተባባሪው ተቋም መሆን አለበት፡፡ መንግሥትና በዘርፉ ያሉት አዋቂዎችና ሙያተኞች የሚሉንን መስማት ብቻ ይበቃናል፡፡

      በዚህ ረገድ ከብዙ ሥራዎቻችን በተሻለና ለብሔራዊ አጀንዳ ትኩረት የሚሰጡ የማኅበረሰብ አንቂዎችና በቂ የዕውቀት ባለቤቶች አሉን፡፡ ስለወሰን ተሻጋሪ ወንዞች በአጠቃላይና ስለዓባይ ወንዝ በተለይ ሊያስረዱን የሚችሉ እንደ ስለሺ በቀለ (ዶ/ር)፣ አቶ ፈቅ አህመድ ነጋሽ፣  ያዕቆብ አርሳኖ (ፕሮፌሰር)፣ መህመድ አልአሩሲ፣ ኡስታዝ ጀማል በሽር፣ ጌታቸው ወልዩና የአሁኑ ዘመን ከሚባሉትም እነ ሰላም ሙሉጌታ፣ ሱሌማን አብደላ፣ ስላአባት ማናዬ፣ ደጀኔ አሰፋ፣ እስሌማን ዓባይ (የዓባይ ልጅ) እና ሌሎችም ምሁራን ስለዓለም አቀፍ የውኃ ሕግጋትና ስለወሰን ተሻጋሪ ወንዞች ፖለቲካ በበቂ አሳማኝ ሁኔታ ሊነግሩን ይችላሉ፡፡

      ስለሆነም ስለዓባይ ጉዳይ መረጃ ለማግኘት ጆሮዋችንን የግብፅ ፕሮፓጋንዲስቶችና ቅጥረኞች አፍ ሥር መደቀን አያስፈልገንም፡፡ የግድቡን ግንባታ ያለማቋረጥ እያስኬድን ጎን ለጎን ደግሞ የብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦችና የሃይማኖት ልዩነቶቻችን ለግብፅ መሰሪዎች መጠቀሚያ እንዳይሆን መሥራት አለብን፡፡ በዚህ ረገድ የሚነሱ ጉዳዩችን በሙሉ በጥንቃቄ እንመርምር፡፡ አሁን ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ብሔራዊ አንድነታችንን አጠንክረንና እንደ አንድ ሰው ሆነን፣ በአንድ ልብ ሊደቀንብን የሚችለውን ተግዳሮት ለመወጣት እየተዘጋጀን ፍፃሜውን ማሳመር ይጠበቅብናል፡፡

     ለነገሩ እስካሁንም ከተፈጥሮ ሀብታችን ላለመጠቀማችን እንቅፋት የሆነችብን ግብፅ ብቻ አልነበረችም፡፡ ሌሎች ውጫዊ ተፅዕኖ አድራጊዎችና የራሳችንም ውስጣዊ የአቅም ውስንነት ነበረብን፡፡ የዓባይ ተፋሰስ አገሮችን በቅኝ ገዥነት ያስተዳድሩ የነበሩ አገሮች በውኃ ሀብቱ ግብፅ ብቻ ተጠቃሚ እንድትሆን በተለያዩ ጊዜያት ያደረጓቸው ስምምነቶች፣ እንዲሁም ከቅኝ አገዛዝ በኋላ የግብፅ መንግሥታት ኢትዮጵያ የዓባይን ወንዝ ለማልማት የገንዘብ ድጋፍና ዕርዳታ እንዳታገኝ ሲያደርጉ ልክ ነው ብለው ሳያመነቱ የተቀበሏቸው ዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅቶች በውጫዊ ተፅዕኖነት አድራጊነት ይጠቀሳሉ።

     እ.ኤ.አ. ከ1890 እስከ 1950 ድረስ የዓባይ ተፋሰስ አገሮች ቅኝ ገዥዎች (በዋናነት እንግሊዝ፣ ፈረንሣይና ጣሊያን) በዓባይ ውኃ አጠቃቀም ላይ ከስድስት ጊዜ በላይ ስምምነቶች አድርገዋል። ሁሉም ስምምነቶች ኢትዮጵያንና ሌሎች የራስጌ ተፋሰስ ሕዝቦችን ያገለሉና በዋናነት ግብፅን በተከታይነት ሱዳንን ተጠቃሚ ያደረጉ በመሆናቸው ይመሳሰላሉ።

     ከሁሉም በላይ ግን እ.ኤ.አ. በ1929 እና በ1959 ግብፅና ሱዳን የናይል ውኃን ብቸኛ ተጠቃሚ መሆናቸውን የደነገጉበትን የእርስ በርስ ስምምነት አድርገዋል። እ.ኤ.አ. በ1928 ኢትዮጵያን ወርሮ የነበረው የፋሺሽት ጣሊያን መንግሥት በዓባይ ወንዝ ላይ ምንም ዓይነት ልማት ላለማካሄድ ከእንግሊዝ ቅኝ ገዥዎች ጋር ተፈራርሟል። እነዚህ ድርጊቶች ሁሉ በታሪክ ጥቁር መመዝገብ ያለባቸው ናቸው፡፡

     እ.ኤ.አ. በ1959 ለናይል ውኃ ምንም ዓይነት አስተዋጽኦ የሌላቸው ሁለት አገሮች፣ 86 በመቶ የናይል ውኃ ባለቤት የሆነችውን ኢትዮጵያንና ሌሎቹን የራስጌ ተፋሰስ አገሮች ጭራሽ መኖራቸውን በመዘንጋት ስምምነት አድርገዋል። እስከ ዛሬ በዓባይ ውኃ ላለመልማታችን በሁለተኛነት ምክንያት የሆነው ደግሞ በወንዙ ላይ ልማትን በራስ ሀብት ለማከናወን የሚያስችል አቅም ማጣታችን መሆኑን፣ እንደ ትልቅ መመርያ መውሰድ ያስፈልጋል፣ ይገባልም፡፡

     እዚህ ላይ ይህ የዓባይ ትውልድ የሚኮራበት ቁም ነገር ያለውን ሀብት አሟጦ በራስ አቅም ግድቡን ለመገንባት በመነሳቱ ብቻ አይደለም፡፡ ይልቁንም ገና ከጅምሩ፣ ዓለም አቀፍ የድንበር ተሻጋሪ ወንዞች መርሆችን መሠረት የደረገውን የናይል ሁሉን አቀፍ የስምምነት ማዕቀፍ በማርቀቅና በመጨረሻም አብላጫው የተፋሰሱ ሕዝቦች እንዲቀበሉት በማድረግ ሰፊ የዲፕሎማሲ ሥራ በመሥራቱ መደላድሉን ምቹ አድርጎታል። ለኢትዮጵያ እጅግ ጠቃሚ የሚሆነው እ.ኤ.አ. በ2015 በግብፅ፣ በሱዳንና በኢትዮጵያ መካከል የተፈረመው «Declaration of Principles» በመባል የሚታወቀው ስምምነት ነው የሚባለውም በዚሁ መነሻ ነበር።

    ስምምነቱ በዓለም አቀፍ ሕግ ላይ የተመሠረተ፣ አሥር ዝርዝር ነጥቦችን የያዘና ሦስቱንም የተፋሰሱ አገሮችን ተጠቃሚ የሚያደርግ፣ እንዲሁም ታሪካዊና ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው። ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ሀብቷን እንዳትጠቀም ብዙ የውጭ ተፅዕኖዎች ተደርገውባታል፡፡ ያንን ሁሉ ጫና በጣጥሳ በአሸናፊነት ወጥታ እነሆ የግድቡ ግንባታ ሦስተኛውን ሙሌት አጠናቆ ኃይል ማመንጨት ደረጃ እንዲደርስ አንዱ እርሾ የተፋሰሱ አገሮች በፈራ ተባም ቢሆን የደረሱበት ስምምነት ነው።

     አንዲት ጠብታ ውኃ ለዓባይ ወንዝ የማታዋጣው ግብፅ በእኛ ሀብት ስትከብር ኖራ፣ ዛሬ በራሳችን ገንዘብ በሠራነው ግድብ ስካታብድ መታየቷ ግን አስገራሚ ብቻ ሳይሆን አሁንም ከተጣባት በሽታ አለመላቀቋን ያሳያል፡፡

ካይሮ በቅርቡ የእኛን ግድብ የውኃ ሙሌት ተከትሎ አስቸኳይ የፓርላማ ስብሰባ ጠርታ በ13 ሚኒስትሮች ላይ የሹም ሽር አድርጋለች፡፡ በፀረ ኢትዮጵያዊነት በከፍተኛ ደረጃ የተደራጀ የሚዲያና የማኅበራዊ ሚዲያ ሥልጠና ከመላው አፍሪካ ለተውጣጡ የሚዲያ ሰዎች በተለያዩ ቋንቋዎች በመስጠት፣ በኢትዮጵያ ላይ ሰፊ ዘመቻ ለመክፈት እንደ አዲስ እየሠራች መሆኗንም ነው ውስጥ አዋቂ መረጃዎች ያመለከቱት፡፡     
465 views18:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 21:14:59 የካይሮ ሴራ ቢበረታም ማምከኛው በእጃችን ላይ ነው

በንጉሥ ወዳጅነው

       ታላቁ የህዳሴ ግድብ የተገነባበት ረዥሙ ዓባይ ወንዝ ተዝቆ የማያልቅ ታሪክ፣ የተፈጥሮ ሀብትና ውበት፣ ፀጋና በረከት የሞላበት ነው። የእኛኑ ዓባይ ግብፆች የህልውናቸው መሠረት በመሆኑና በኃያልነቱ የተነሳ ‹‹ኢሲስ›› እና ‹‹ኦሲሪስ›› የሚባሉ አማልክት ፈጥረውለት ሲያመልኩት ኖረዋል። በዓለማችን 263 ያህል ወሰን ተሻጋሪ ወንዞች ቢኖሩም፣ ረዥም ርቀት በመጓዝና በርካታ አገሮችን በማቋረጥ ቀዳሚ የሆነው ዓባይ (ናይል) ወንዝ 6,650 ኪሎ ሜትር በመጓዝ 11 አገሮችን  የሚያካልል መሆኑም የሚስጥሩ መጀመርያ ነው፡፡

    ዓባይን ሦስት ወንዞች ተጣምረው ይፈጥሩታል። እነሱም ከብሩንዲ ሰንሰለታማ ተራሮች የሚመነጨው ነጭ ዓባይ፣ ከኢትዮጵያ የሚመነጨው ጥቁር ዓባይና የኢትዮጵያን ድንበር ተሻግሮ ሱዳን ሲደርስ ‹‹አትባራ›› በሚል ስያሜ የሚጠራው ‹‹ተከዜ ወንዝ›› ናቸው፡፡ እነዚህ ሦስት ወንዞች ካርቱም ላይ ከተገናኙ በኋላ ‹‹ናይል›› ይሰኛሉ።

     የሱዳንና የግብፅን በረሃዎችን ሰንጥቆና አቋርጦ ረዥሙ የናይል ጉዞ እስከ ሰሜናዊ ግብፅ በመዝለቅ በሜዲትራኒያን ባህር ዳርቻ ይጠናቀቃል። የናይል ወንዝ 86 በመቶ ያህሉ የውኃ ሀብት የሚሄደው ከኢትዮጵያ ነው። ከዚህ ውስጥ የዓባይ ወንዝ ብቻውን 53 በመቶ ይሸፍናል፣ የዓባይ ታላቅነት ቅኔም ሌላው መገለጫ ይኼኛው እውነታ ነው፡፡

      ያም ሆኖ ኢትዮጵያ የዓባይ ወንዝ መፈጠሪያ ሆና ለዘመናት በዓባይ የመጠራት እንጂ የመልማት ዕድሉ  አልነበራትም፡፡  ማንኛውም አገር ባሉት ወሰን ተሻጋሪ ወንዞች ሌሎች የተፋሰሱ አገሮችን በማይጎዳ መንገድ በውኃ ሀብቱ የመልማት ተፈጥሯዊና ሕጋዊ መብት እንዳለው ቢታወቅም፣ ለዘመናት ከሀብታችን ሳንጠቀም መቆየታችን ነው የሚያስቆጨው፡፡ 

      በእርግጥ ዓባይ ለግብፆች ብቸኛ የውኃ ምንጫቸው ነው፡፡ የከርሰ ምድር ውኃ ሊኖራቸው ቢችል እንኳ ስለእሱ ማሰብ አይፈልጉም፡፡ ዓይናቸው፣ ጆሮአቸውና ልባቸው ያለው ዓባይ ላይ ብቻ እንደሆነ የሚታወቅ ነው፡፡ ዓባይ ለግብፆች የዕለት ጉርሳቸውና የዓመት ልብሳቸው ነው፡፡ ሥጋታቸው፣ ቅዠታቸው፣ ጌጣቸው፣ ክብራቸው፣ ኩራታቸውና አጠቃላይ ህልውናቸው በዓባይ ውኃ ደኅንነት ላይ የተመሠረተ ነው፡፡

ሊዚህም ነው ትናንትም ሆነ ዛሬ ካይሮ የትኛውንም ወጥመድና ሴራ በመፈጸም እንኳንስ እንደ ታላቁ ህዳሴ ግድብ ያለውን ፕሮጀክት፣ የትኛውንም የውኃ ልማት ለማሰናከል ወደ ኋላ የማትለው፡፡ ትርፉ ትዝብት እንጂ በተቀየረ ዓለም አቀፋዊ ሁኔታ፣ እያደገ በመጣ የአገራችን ሕዝብና ምጣኔ ሀብት ብሎም የማደግ ፍላጎት በሰጥቶ መቀበል መርህ በጋራ ለመጠቀም ማሰቡ ነበር የሚበጃት፡፡ ሴራው የበረታን እንደሆን እንጂ ሊሰናከል እደማይችል በገቢር ታይቷል፡፡

      ገና ከጀማሬው አንስታ አገራችን የግድቡ ተልዕኮ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨትና ማለፍ መሆኑን፣ ግብፅን እንደማይጎዳ፣ እንዲያውም ለግብፅ እንደሚጠቅም፣ ወደ ግብፅ በሚሄደው ውኃ ላይ ጉልህ ተፅዕኖ እንደሌለውና ለተፋሰሱ አገሮች በአጠቃላይ ለሱዳንና ለግብፅ ደግሞ በተለይ አስረድታለች፡፡ ልዑካኖቻቸውን ተቀብላ፣ የእሷንም ልዑካን ልካ በጉዳዩ ላይ ግልጽ ውይይት አድርጋለች፡፡

በዓለም አቀፍና ከሦስቱ አገሮች በተውጣጡ የዘርፉ ሊቃውንት የግድቡን ፕሮጀክት አስመርምራለች፡፡ ምክረ ሐሳብ ተቀብላለች፡፡ የግድቡ ዲዛይን ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ መሆኑንም በዓለም አቀፍ የባለሙያዎች ቡድን አረጋግጣለች፡፡ በተለይ ዋናው የኃይል ማመንጫ ግድብ በጠንካራ አለት ላይ ያረፈ መሆኑን፣ የመሬት መንቀጥቀጥ እንደማያሠጋው፣ በብዙ ሺሕ ዓመታት አንድ ጊዜ ጎርፍ ቢከሰት እንኳ ማሳለፍ እንደሚችልና አስተማማኝ መሆኑንም በጥናት  አረጋግጣለች፡፡

     በሒደቱ የባለሙያዎች ቡድን ባቀረበው ምክረ ሐሳብ መሠረት ቀጣዩ ሥራ ምክረ ሐሳብን ተግባራዊ ለማድረግ የሦስቱን አገሮች (ኢትዮጵያ፣ ሱዳንና ግብፅ) ማዕቀፍ ማደራጀት ነበር፡፡ ሦስቱ አገሮች ተገናኝተውም መነጋገራቸው አይዘነጋም፡፡ ያም ሆኖ ግብፅ በማዕቀፉ አባላት ላይ ተቃውሞ ከመሰንዘር አልተቆጠበችም ነበር፡፡

    ኢትዮጵያና ሱዳን ከሦስታችንም አገሮች የተውጣጡ ባለሙያዎች ሥራውን መከታተል ይችላሉ ሲሉ፣ ግብፅ ግን ‹‹አይሆንም የዓለም አቀፍ ሙያተኞችም ካልገቡበት አሻፈረኝ›› እስከ ማለት ደርሳ እንደነበር አይዘነጋም፡፡ የአተገባበሩን የማዕቀፍ ኮሚቴ ለማቋቋም ሌላ ዓለም አቀፍ ኮሚቴ አያስፈልግም ብትባልም አይሆንም አለች፡፡ ይህንንም ‹‹እሺ›› ቢሏት ሌላ ተቃውሞ ማምጣቷ አይቀርም ነበር፣ ደግሞም አምጥታለች፡፡  ግብፅ በዓባይ ላይ የቀረበን ሐሳብ ከመቃወም ሌላ ሥራ የላትም እስኪባል ድረስ ስትጥል ስታነሳ ከረመች፡፡

ግድቡ ከተጀመረበት ባለፉት 11 ዓመታት ውስጥ ግብፅ የግድቡን ሥራ ለማወክና በጋራ ላለመሥራት ብዙ ርቀት ሄዳለች፡፡ አንዴ ‹‹የግድቡ ሆድ ሰፍቷልና ይጥበብ›› ስትል፣ ሌላ ጊዜ ‹‹የግድቡ ቁመት ይጠር›› ብላለች፡፡ ሌላ ጊዜ ግድቡ ቢደረመስ አደጋ ያስከትልብኛል ስትል፣ ሌላ ጊዜ የውኃ ድርሻዬን መጠን ይቀንስብኛለች እያለች ለስምምነት የሚደረጉ ጥረቶችን ሁሉ እያጓተተች፣ ቋሚ መንግሥት እስኪመሠረትና እስኪወስን ጠብቁኝ እያለች አስተጓጉላለች፡፡ ሁሉም አሉታዊ ጥረቶች ግን ፕሮጀክቱን ከዳር ከማድረስ አላወኩም፡፡

      ከሁሉ በላይ በምንገኝበት የዕውቀትና የመረጃ ዝመን ለሕዝቦቿም የተሳሳተ መረጃ በመስጠት ደክማለች፡፡ ዓባይ የግብፅ ብቻ ነው ትላቸዋለች፡፡ ለእኛም ጭምር የኢትዮጵያ መንግሥት የግድቡ ሥራ እየተገባደደ ነው የሚለውት ውሸት ነው፣ የግድቡ ሥራ ከፍተኛ የገንዘብ ችግር ገጥሞታል፣ ኢትዮጵያ ወጪውን መሸፈን አልቻለችም፣ ሕዝባዊ ተቃውሞም ተነስቶበታል፣ ወዘተ እያለች ወገኖቿን ለማጀገን እኛን ደግሞ ተስፋ ለማስቆረጥና ጥርጣሬ ውስጥ ለመክተት በሚዲያዎቿና በምሁራኖቿ አማካይነት ሰፊ ቅስቀሳ ስታካሂድ ኖራለች፡፡ 

     ‹የግድቡን አካባቢ በአውሮፕላን ልትመታ ትችላለች› እያስባለች የሥነ ልቦና ሰለባ ዘመቻ ታደርጋለች፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ እርስ በርሱና ከመንግሥት ጋር ያለውን ግንኙነት ለማሻከርና ለማቃቃር፣ በዚህም ምክንያት የግድቡን ሥራ ለማሰናከል ያልፈነቀለችው ድንጋይ አልነበረም፡፡ ለዚህም የተለያዩ ሥልቶችን ትጠቀማለች፡፡

    የመጀመርያ ሥልቷ የኢትዮጵያን ሕዝብ በብሔር እየከፋፈለች ማቆሚያ በሌለው የእርስ በርስ ሽኩቻ እንዲወጠር ማድረግ ነው፡፡ የትግራይን ሕዝብ በወያኔ አማካይነት ወደ የማያባራ ጦርነትና ከወገኑ ጋር የማጋጨት ሥራ ውስጥ ከተዋለች፡፡ ኦሮሞን በአማራ ላይ ለማስነሳት የተጀመረ የአፍራሽ ኃይሎች ሴራ ዛሬም ብልጭ ድርግም እያለ ቀጥሏል፡፡ በብሔር ብሔረሰቦች ካባ የተሸፈኑ ነፃ አውጭ ተብዬዎችና አማፅያንን በየቦታው እየደገፈች፣ ቀላል የማይባል ትርምስ ስፖንሰር ማድረጓ በመረጃ ተደጋግሞ የተረጋጋጠ ነው፡፡

      ኦሮሞ ኢትዮጵያዊነቱን እንደሚጠራጠር የሚያወሩና እንዲገነጠል የሚገፋፉ፣ በአማራው ላይ ጥላቻ እንዲያድርበት ከአፄ ምኒልክ ያለፈ ታሪክ ውስጥ መጥፎ መጥፎ የሚሉትን እየለቀሙ ዘረኝነትን የሚያራግቡ የፌስቡክ አርበኞች ይንቀሳቀሳሉ፡፡ ከእነዚህ ሴረኛ ዜጎች የጥፋት ድግስ በስተጀርባ የግብፅ እጅ አለበት፡፡ ማንኛውንም የግብፅ እንቅስቃሴ ግድቡን ለማሰናከል ከሚደረግ ዘመቻ ጋር አያይዘን ማየት አለብን፡፡ ከዚሁ ጋር አብሮ መታየት ያለበት የግብፅ መንግሥት በሽብርተኝነት የተፈረጁ ቡድኖችን በገንዘብ እያማለለ
440 views18:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 21:14:49
የካይሮ ሴራ ቢበረታም ማምከኛው በእጃችን ላይ ነው

በንጉሥ ወዳጅነው
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
436 views18:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 20:30:24 The Niles ናይል pinned a photo
17:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 20:30:11
"ዲፕሎማቶች የተሰጠንን ተልዕኮ በብቃት በመተግበር ሀገር በማዳን እንቅስቃሴ ውስጥ ኃላፊነታችን መወጣት ይገባናል።"
ክብርት አምባሳደር ብርቱካን አያኖ
_________________________________________________________
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሰራተኞችና ተጠሪ ተቋማት በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አድርገዋል።

በውይይቱ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት አምባሳደር ብርቱካን አያኖ ሁሉም ሰራተኞች ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የኢትዮጵያን እውነታ እንዲገነዘብ በማድረግ ለሀገራቸው ሁለተናዊ ተሳትፎ በማድረግ የበኩላቸውን ድርሻ መወጣት አለባቸው ብለዋል፡፡

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አምባሳደር ተስፋዬ ይልማ በበኩላቸው የኢትዮጵያ መንግስት ለሰላማዊ መፍትሄ ረጅም ርቀት መጓዙን ማስረጃዎችን በማቅረብ ያብራሩ ሲሆን፤ ለአሁኑ ግጭትም ህወሃት መንስኤ መሆኑን ጠቅሰዋል። መንግሥት በአፍሪካ ህብረት ማዕቀፍ ስር ለሚደረግ ድርድር ዝግጁ መሆኑንምጠቁመዋል

ለውይይቱ የመነሻ ጽሑፍ ያቀረቡት የውጭ ጉዳይ ኢንስቲቲዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ጃፋር በድሩ በበኩላቸው ህወሓት የጦርነት አማራጭ መርጦ ለሦስተኛ ጊዜ ግጭት መቀስቀሱን አብራርተዋል።

አቶ ጃፋር አሁንም መንግስት የዜጎችን ደህንነት እና የአገር ሉዓላዊነት ከማስጠበቅ ጎን ለጎን ለሰላማዊ መፍትሄ ቅድሚያ የሚሰጥ መሆኑን አብራርተዋል።

ተሳታፊዎቹም መንግስት የሰላም አማራጭ ቀዳሚ ማድረጉ ትክክል መሆኑን ገልጸው ፣ በዲፕሎማሲው ዘርፍ ለአገራቸው የሚችሉን ለማበርከት በትጋት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።
613 views17:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 20:09:51 በባህርዳር ከተማ የአልሙኒየም ፎርምወርክ ቴክኖሎጂ ለመጀመሪያ ጊዜ በመጠቀም ዘመናዊ የመኖሪያ ህንፃ ሊገነባ ነው

ለግንባታው የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን እና የአማራ ክልል ቤቶች ልማት ደርጅት የግንባታ ማመከር ውል ስምምነት ፈፅመዋል
~~~~~~

የአማራ ክልል ቤቶች ልማት ደርጅት በባህርዳር ከተማ በክልሉ ለመጀመሪያ ጊዜ አዲስ የሆነውን  የአልሙኒየም ፎርምወርክ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ለሚያስገነባው ዘመናዊ የመኖሪያ ሕንጻ ግንባታ ዛሬ ከፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ጋር የግንባታ አማካሪነት ውል ተፈራርመዋል።

ስምምነቱን የፈዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ክቡር አቶ ረሻድ ከማል እና የአማራ ቤቶች ልማት  ደርጅት ዋና ዳይሬክተር አቶ አበረ ሙጨ ተፈራርመዋል፡፡

በስምምነቱ መሰረት የአማራ ቤቶች ልማት ደርጅት የአልሙኒየም ፎርም ቴክኖሎጂ በመጠቀም ለሚያስገነባው የግንባታ ፕሮጀክት የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ሙሉ የማመከር ሥራ የሚያከናውን ይሆናል፡፡

የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ረሻድ ከማል  እንዳሉት ኮርፓሬሽኑ በቤት ልማት ኢንዱስትሪ ይበልጥ በግምባታ እና ማማከር ዘርፍ ግንባር ቀደም ለመሆን እየሰራ ይገኛል። ባለፉት አራት አመታት የለውጥ ስራዎችን በመተግበር በጊዜ ፣ በጥራት እና በብዛት ውጤታማ የሆኑ የቤት ግምባታዎችን ማከናወን መቻሉን ተናግረዋል።

ስኬታማ ተሞክሮውን በማስቀጠል የአማራ ቤቶች ልማት ደርጅት በሁሉም መስፈርቶች የተሻሉ  ዘመናዊ የመኖሪያ ቤት ፕሮጀክቶችን እንዲገነባ ኮርፖሬሽኑ ድጋፍ እንደሚያደርግ ነው ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ ረሻድ ተናግረዋል።


የአማራ ቤቶች ልማት ደርጅት ዋና ዳይሬክተር አቶ አበረ ሙጨ በበኩላቸው የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ለአማካሪ  መስፈርቶችን ያሟላና ውጤታማ የፕሮጀክት አስተዳደርና አመራር ልምድ ያካበተ ተቋም በመሆኑ አብሮ ለመስራት መምረጣቸውን ተናግረዋል ።፡

ኮርፖሬሽኑ በአዲስ አበባ ከተማ የአልሙኒየም ፎርምወርክ ቴክኖሎጂን በስፋት በመጠቀም በ18 ወራት ግዙፍ የመኖሪያ መንደር በመገንባት ያገኘው ተሞክሮ ለእኛም ኘሮጀክቶች ስኬታማነት ወሳኝ ነው ብለዋል።

በቀጣይም የአማራ ቤቶች ልማት ድርጅት ከፕሮጀክት ማመከር በዘለለ ከፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ጋር በትብብር እንደሚሰራም ተገልጿል።
696 views17:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 20:09:31
በባህርዳር ከተማ የአልሙኒየም ፎርምወርክ ቴክኖሎጂ ለመጀመሪያ ጊዜ በመጠቀም ዘመናዊ የመኖሪያ ህንፃ ሊገነባ ነው

ለግንባታው የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን እና የአማራ ክልል ቤቶች ልማት ደርጅት የግንባታ ማመከር ውል ስምምነት ፈፅመዋል
~~~~~~

የአማራ ክልል ቤቶች ልማት ደርጅት በባህርዳር ከተማ በክልሉ ለመጀመሪያ ጊዜ አዲስ የሆነውን  የአልሙኒየም ፎርምወርክ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ለሚያስገነባው ዘመናዊ የመኖሪያ ሕንጻ ግንባታ ዛሬ ከፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ጋር የግንባታ አማካሪነት ውል ተፈራርመዋል።
718 views17:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 19:57:00
111 ሕገ-ወጥ የዲጂታል ሚዲያዎች ላይ ክስ መመስቱን የፌደራል ፖሊስ አስታወቀ
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~

ሀሰተኛ መረጃዎችን በማሰራጨት ኢትዮጵያን የብጥብጥ ማዕከል ለማድረግ ሲሠሩ በነበሩ 111 ሕገ-ወጥ የዲጂታል ሚዲያዎች ላይ ክስ መመስረቱን የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡

በኮሚሽኑ የታክቲክ ወንጀሎች ምርመራ ምክትል ዋና መምሪያ ሃላፊ ረዳት ኮሚሽነር ብርሃኑ አበበ፤ ህዝብን ለአመጽ በማነሳሳት ድብቅ ዓላማቸውን ለማሳካት ሲንቀሳቀሱ እንደነበርም በምርመራ መረጋገጡን ገልጸዋል።

ከዚህ ጋር ተያይዞ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በተደራጁና የሽብር ወንጀሎች፣ በሙስና፣ በፋይናንስና ንግድ ነክ፣ በታክስና ጉሙሩክ ወንጀሎች ላይ ጥቆማዎችን መነሻ በማድረግ ምርመራዎች ተከናውነዋል ብለዋል።

ይሄውም በበጀት ዓመቱ 2 ሺህ 668 ጥቆማዎችን በመቀበል 1 ሺህ 438 መዝገቦችን መርምሮ ለፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ መላካቸውንም ገልጸዋል፡፡

ግለሰቦቹ ከ57 ሚሊየን ብር በላይ መዝረፋቸው በምርመራ በመረጋገጡ ክስ ተመስርቶባቸዋል ማለታቸውን ከኢዜአ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

The Niles
1.0K views16:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 21:30:21
እንዝመት ወደ ትዊተሩ ግንባር !!
ከ ethiopian truth

በኢትዮጵያ ላይ እየተካሄደ ያለውን የጠላቶቻችን የተቀናጀ የሃሰት ዘመቻ እውነትን በመግለፅ አብረን እንታገል ።

የቅጥረኛ ኘሮፓጋንዳስቶችን አፍራሽ ተግባር እንመክት ፤

ይህ ስለ አንዲት ሃገራችን ሲባል የሚደረግ ትግል ነው

ግቡ ወደ ትዊተሩ የትግል ግምባር ።

በተከታዪ ሊንክ የተዘጋጁ መልዕከሰቶችን ትዊት እናድርግ ጎበዝ

#ethiopian truth

https://ethiopiantruth.com/if-youre-an-african-respecting-the-au-is-respecting-yourself-respect-obasanjo/
1.3K views18:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ