Get Mystery Box with random crypto!

The Niles ናይል 🇪🇹

የቴሌግራም ቻናል አርማ nileabay — The Niles ናይል 🇪🇹 T
የቴሌግራም ቻናል አርማ nileabay — The Niles ናይል 🇪🇹
የሰርጥ አድራሻ: @nileabay
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 5.61K
የሰርጥ መግለጫ

news,article ,interview and analysis on nile and international issues .
በአባይ እና ከሃገራችን ጋር ተያያዥ በሆኑ አለምአቀፍ ጉዳዮች ዜና፣ሀተታ ፣ቃለ መጠይቅ እና ትንታኔ ያገኛሉ

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2022-07-08 23:10:30
አቤ እና አበበ

" ስሜ አቤ ነው ፤ ሆኖም ትምህርት ቤት ሳለሁ ግን ሁሉም የሚጠሩኝ አበበ እያሉ ነበር " ሺንዞ አቤ
~~~~~~~~~~~~~~~~~~
1.3K views20:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 21:25:47 የኢትዮጵያ እና የጂቡቲ መሪዎች በሶስት ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ በመምከር ውሳኔ አሳለፉ

የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር አብይ አህመድ እና የጂቡቲው ፕሬዝደንት ክቡር ኢስማኤል ዑማር ጌሌ ቀደም ብለው ያደረጉትን ውይይት ተከትሎ በኢፌዲሪ ፋይናንስ ሚኒስትር ክቡር አቶ አህመድ ሺዴ የሚመራ የልዑካን ቡድን ከሰኔ 29-30 ቀን 2014ዓ.ም ድረስ በጂቡቲ ይፋዊ ጉብኝት አካሂዷል፡፡

የልዑካን ቡድኑ ክቡር ፕሬዝደንት ኢስማኤል ዑማር ጌሌን አግኝቶ የክቡር ጠ/ሚኒስትራችንን መልዕክት ባስተላለፈበት ወቅት በጋራ ማንነት የተጋመደው እና ልዩ የሆነው የሁለቱ አገራት ሁሉን-አቀፍ ስትራቴጂያዊ ግንኙነት (Unique and Comprehensive Strategic Cooperation) ከመቼውም ጊዜ በላይ እያደገ የመጣ መሆኑን አውስቷል፡፡

በተለያዩ መሰረተ ልማቶች ትስስር ብቻ ከ10 ቢሊየን ዶላር በላይ በጋራ ኢንቨስት ያደረጉት ሁለቱ ወዳጅ አገራት ቀደም ብሎ በኮቪድ፣ ቀጥሎም በሌሎች የውጭ እና የውስጥ ሁኔታዎች ሲቆራረጥ የቆየውን የሁለትዮሽ ውይይት ከቀድሞው የበለጠ በማጠናከር የጋራ የምጣኔ-ሃብት ትስስሩን በአጭር ጊዜ ውስጥ በከፍተኛ ደረጃ ለመለወጥ በሁለቱም በኩል የታየውን ቁርጠኝነት አድንቀዋል፡፡

በመሆኑም የሁለቱን አገራት ታሪካዊ ፣ ተምሳሌታዊና ስትራቴጂያዊ ግንኙነት ከግምት ውስጥ በማስገባት የአገራት መሪዎች ቀደም ብለው በተወያዩት አግባብ መሰረት ሶስት ጉዳዮች ላይ ከስምምነት ተደርሷል።

የአትክልት እና ፍራፍሬ የዋጋ ተመንን በተመለከተ የሁለቱ አገራት መንግስታት በሚያቋቁሙት የጋራ ኮሚቴ አማካኝነት የጂቡቲን ነባራዊ አሁናዊ ገበያ እና የሰፊውን ህዝብ የኑሮ ሁኔታ ከግምት ውስጥ ያስገባ የዋጋ ማሻሻያ እስከሚደረግ ድረስ ለጂቡቲ ብቻ ቀድሞ በነበረው ዋጋ እንዲቀጥል ተወስኗል።

በተጨማሪም ለ40 ዓመታት ሲሰራበት የቆየው ወደ ጂቡቲ የሚላከውን የጫት ምርት ታሪፍ ከፍ ለማድረግ ቀደም ብለው መሪዎቹ በተስማሙት መሰረት ተግባራዊ የሚደረግ ሲሆን የጂቡቲ አስመጪዎች የጫት ምርት የውጪ ሽያጭ ውል ምዝገባ መፈፀም ሳይጠበቅባቸው ምርቱን ማስገባት እንዲችሉ እንዲሁም የባህር አገልግሎት ክፍያዎች (Maritime Charges) በሁለቱ አገራት መንግስታት የሚመለከታችው አካላት በጋራ ምክክር ተደርጎበት ውሳኔ ላይ እስኪደርስ ማስተካከያው ሳይደረግ በነበረው ዋጋ እንዲቀጥል ከስምምነት ተደርሷል።

የልዑካን ቡድኑ በክቡር ፕሬዝደንቱ ቤተ-መንግስት በመገኘት የክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩን መልዕክት ከማስተላለፉ በፊት የጂቡቲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክቡር አቶ ማህሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የንግድ እና ቱሪዝም ሚኒስትር ክቡር አቶ መሐመድ ዋርሳማ ዲሬህ፣

የንግድ ም/ቤት ሊቀ-መንበር ክቡር አቶ ዮሱፍ ሙሳ ደዋሌህ እንዲሁም የጂቡቲ ወደቦች እና ነጻ የንግድ ቀጠና ባለስልጣን ሊቀ-መንበር ክቡር አቶ አቡበከር ዑመር ሐዲን አግኝቶ በሁለቱ አገራት መካከል ስላለው የዲፕሎማሲ፣ ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ወደብ እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርጓል፡፡

የልዑካን ቡድኑ በቆይታው ወደ ኢትዮጵያ የሚገባው የተጣራ እና ድፍድፍ የምግብ ዘይት ምርቶች ዋነኛ አቅራቢ ድርጅት Golden Africa ተገኝቶ ጉብኝት እንዲሁም ከድርጅቱ ኃላፊዎች ጋር ውይይቶችን አድርጓል።
1.5K views18:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 21:25:35
የኢትዮጵያ እና የጂቡቲ መሪዎች በሶስት ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ በመምከር ውሳኔ አሳለፉ
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
1.4K views18:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-06 23:29:32
1.8K views20:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-06 23:23:13
የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሹን ከጅማ ዩንቨርሲቲ ጋር በተለያዩ ጉዳዮች አብሮ ለመስራት ስምምነት ተፈራረሙ
~~~~

የትብብር ስምምነቱን የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ክቡር አቶ ረሻድ ከማልና  የጅማ ዩንቨርሲቲ ፕሬዝደንት ዶ/ር ጀማል አባፊጣ ናቸው የፈረሙት ።

የስምምነቱ ዋና ዓለማ የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በግንባታ ፕሮጀክት አመራርና አስተዳደር ያገኘውን የተግባር ውጤት  ወደ ምርምር እና የእውቀት ተቋማት ለማስተላለፍ እንደሆነ ነው በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተገለጸው፡፡

በሥነ ስርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ   አቶ ረሻድ ከማል በ እንደገለጹት የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በግንባታ ፕሮጀክት አስተዳደርና አመራር  የላቀ ብቃት አሳይቷል ያሉ ሲሆን ይህንንም ውጤት  ወደ ትምህርት ተቋማት እንዲሸጋገር  እየሰራን ነው ብለዋል፡፡
ጅማ ዩንቨርሲቲ በሕክምናው እና በጥናትና ምርምር ውጤታማ ተቋም መሆኑን ጠቅሰው ከእንዲህ ዓይነት አንጋፋ እና ጠንካራ ዩንቨርሲቲ ጋር አብሮ መስራት ለኮርፖሬሽኑ ትልቅ አቅም እንደሚሆንም አመለክተዋል፡፡

የጅማ ዩንቨርሲቲ ፕሬዘዳንት ዶ/ር ጀማል አባፊጣ በበኩላቸው  በዘመናዊና በተለመደው(Conventional) የአሰራር ዘዴ ያገኘውን ውጤታማ የፕሮጀክት አስተዳደርና የማማከር ልምድ ለጅማ ዩነቨርሲቲ በቀጥታ ለማጋራትና በትብብር ለመስራት መወሰኑ  ዩንቨርሲቲውን እንደሚያግዝ  ተናግረዋል፡፡
1.7K viewsedited  20:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ