Get Mystery Box with random crypto!

Muktarovich Ousmanova

የሰርጥ አድራሻ: @muktarovichousmanova
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 63.61K
የሰርጥ መግለጫ

Ethiopia forever

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 144

2022-09-03 21:39:12
ሰበር
-
የህወሓት ቀጣይ እስትራቴጅና የመጨረሻ ግብ ብሎ ያስቀመጣቸው ሚስጢራዊ ሰነዶች በጃችን ገብቷል።

በሰነዱ ላይ የሚከተሉት ዋናዋና ነገሮች ይገኙበታል።

(1)
ህወሓት ሰላም እንደማይፈልግና አማራን እንዴት እንደጥላት ፈርጆ ሲያበቃ አሁን ወዳጅ መስሎ ለመበተን እየሰራ እንዳለ፣

(2)
በተጨባጭ መሳርያ የሚያቀርቡለት ሃይሎች(ሀገሮች) መኖራቸውን ማመኑን፣

(3)
በሀገራችን የተለያዩ ክልሎች የሚንቀሳቀሱ አማፂያንና ሽብርተኞችን እንዴት እንደሚደግፍ ያመነበትን፣

(4)
የእርዳታ ድርጅቶችን እንዴት አግባብቶ የእርዳታ ቁሳቁስ እንዳይነፍጉት እያደረገ እንዳለና እንደሚያደርግ አስቀምጧል።

(5) የትግራይ ወጣቶችን የማይቀርና የመጨረሻ ድል ነው እያለ እያምታታና እያታለለ ለጦርነት አሰልፎ እንደሚማግድ፣

የአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት ምንም ትርጉም ስለሌለው መንግስት ሰላም አይፈልጉም ብሎ እያሳጣን ስለሆነ ከዚህ ወቀሳ ለማምለጥ እንጂ ዋናው ግባቸው በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ አኩራፊዎችን በማበራከት መንግስትን መገልበጥ እንጂ በድርድር ሰላም ይመጣል ብለው እንደማያምኑ ከተገለፁት ዋናዋናዎቹ ናቸው።

ሱሌማን አብደላ
14.7K views18:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-03 21:25:52
ጥቆማ
ስለ ወቅታዊው የግንባር ዜናዎችንና መረጃዎችን በፍጥነት የሚያደርስ ቻናል ልጠቁማችሁ። መረጃ በጊዜ፣ በታማኝነት፣ የሚባልና የማይባልን የሚለይ ቻናል።
ተቀላቀሉት ቻናሉ ይሄ ነው
https://t.me/+z7Kc0EjprgFlYmU8
15.0K views18:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-03 21:11:04 ሰቆጣ…

ከሁለት አቅጣጫ ከአላማጣ በመረዋ እና በኮረም ሀሙሲት አድርጎ ወደ ሰቆጣ ለመግባት የሞከረው የህውሃት ወራሪ ሀይል ከሰዓት በኋላ እስካሁን ከጥምር ጦሩ ጋር ውጊያ ላይ መሆኑ ታውቋል።
ጦርነቱ ከሰቆጣ 10 ኪሜ ወለህ በሚባል ቦታ ሲካሄድ እንደነበረረ ተሰምቷል።ከሰቆጣ ምዕራብ አቅጣጫ ወደ አምደወርቅ እና እብናት የመጓዝ እቅድ ይዘው እንደተነሱ ለማወቅ ተችሏል።

መረጃ በፍጥነት ለማግኘት ወደዚህ ይግቡ t.me/wasulife
t.me/wasulife

የቪዲዮና ድምፅ መረጃዎችን ለማግኘት የዩቲዩብ ቻናላችንን Subscribe ያድርጉ
https://www.youtube.com/channel/UCrdWHrcXNEhMfbp1ucgxd1g
16.3K views18:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-03 16:13:54
ወጉማ ተይዟልኮ! ይልቅስ ሄደህ አስከሬን ቁጠር በለው!

ትናንት ብሉምበርግ የሚባል ሚዲያ ለትህነግ ተስፋ የሚሆን አንድ ዜና ሰርቶ ነበር። ኢትዮጵያ በሰላም አስከባሪነት የላከቻቸው የትግራይ ተወላጅ መኮንኖች ወደ ኢትዮጵያ አንመለስም ብለው ወደ ሱዳን አቅንተው ነበር። 528 ናቸው። ሁሉም ሰሞኑን ውጊያ በተደረገበት አካባቢ ስልጠና እየሰጡ ነበር። ብሉምበርግ ታዲያ ከትህነግ በተሰጠው የውሸት መረጃ መሰረት እነዚህ መኮንኖች የሚመሩት የትህነግ ታጣቂ ሁመራን ሊይዝ እንደሆነ አድርጎ አውርቶ ነበር። ውሸት ቁርሳቸው፣ ምሳቸው፣ ራታቸውም ነው።

እውነታው ሌላ ሆነ። ጥምር ጦሩ ገና በመጀመርያው ቀን የት ልግባ አስባላቸው። በሁለት ቀን ሁሉም ምሽግ ተሰባብሮ የተረፉት ወደ ሱዳን እግሬ አውጭኝ ሲሉ አብዛኛውን ጥይትና ቀሪውን የተከዜ ውሃ በላው።

ተበታትኖ የሚገኘውን የትህነግ ኃይል ጥምር ጦሩ የማፅዳት ስራ እየሰራ ይገኛል። እንደምንም ወደ ሱዳን የተሻገረው የትህነግ ታጣቂ አሻባ የተባለ ቦታ ላይ የሱዳን ወታደሮች መሳሪያህን አራግፍ እያለው ነው። ሱደን የከረመው የትህነግ ኃይል ሲፎክር ስለከረመ አሁን እግሬ አውጭኝ ሲል ሱዳኖቹ እንዴት ይታዘቡታል?

ከሱዳን አቅጣጫ የመጣው የትህነግ ኃይል ሁመራን እይዛለሁ ብሎ አስወርቶ በጥምር ጦሩ አሳሩን ሲበላ ከፍተኛ አዛዦቹን ጭምር አጥቷል። በዚህ ውጊያ ኮ/ል መኮነን ኃይሉ የተባለ የትህነግ ክ/ጦር አዛዥን ጨምሮ በሺህ የሚቆጥር ሬሳውን ጭኖ ለመሸሽ ሞክሯል። በርካታ ታጣቂ ሲሮጥ ተከዜ ሲወስደው፣ በውጊያ የሞቱበትን ግን በጀልባ እየጫነ ወደ ሱዳን ለመሻገር ጥሯል። ነፍስ ያለውን ወንዝ ላይ ጨምሮ ሙት ተሸክሞ ይሄዳል። ትህነግ በብሉምበርግ ያሰራው ደግሞ በጀግኖቻችን መስዋዕነት ህልም ሆኖ ቀርቷል። ወግ ብቻ!

https://t.me/GetachewShiferaw
21.6K views13:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-03 16:03:00
የጦርነት ሎጅክ….

የመጀመሪያዉ የዓለም ጦርነት በአዉሮፓ ጦርነቶችን ሁሉ ለማስቆም የተደረገ ጦርነት ነበር ይባላል። ግን የብዙ ሚሊዮን ሰዎችን ህይወት ቀጥፎ፣ ዓለምን ለሌሎች በርካታ ጦርነቶች ዳርጎ አለፈ። በዓለም ላይ በፍፁም በጦርነት ጥሩ ነገር ተገኝቶ አያዉቅም። ነገር ግን አንዱ ጠብ-መንጃ ስያነሳ ሌላኛዉ ዝም ብሎ ማየት አይቻልም። ጠበብ-መንጃ ያነሳዉ ጠብ-መንጃዉን እንድያስቀምጥ ጠብ-መንጃ የተነሳበት ጠብ-መንጃ ማንሳት የግድ ይሆናል። በዓለም ላይ ከጦርነት የከፋ ነገር ብኖር ጦርነትን አለመመከት ብቻ ይሆናል። ብቸኛ የጦርነት ጄስትፍከሽን ይሄ ብቻ ይሆናል።
(ዶክተር ብርሃኑ ሌንጂሶ)
20.2K views13:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-03 15:55:33
የኢትዮጵያን የባንክ አገልግሎት ዘርፍ ለውጭ ኢንቨስተሮች ክፍት የሚያደርገው ፖሊሲ በስራ ላይ እንዲውል የሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔ አሳለፈ። ምክር ቤቱ ውሳኔውን ያሳለፈው ዛሬ ቅዳሜ ነሐሴ 28፤ 2014 ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ ነው።

የመንግስት ፖሊሲው ተግባራዊ እንዲሆን የወሰነው በአራት ምክንያቶች እንደሆነ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ፖሊሲው ስራ ላይ እንዲውል ካስፈለገበት ምክንያቶች አንዱ የፋይናንስ ዘርፉን ተወዳዳሪነት፣ ወጤታማነትና ቀልጣፋነት በመጨመር፤ በቂ የፋይናንስ አቅርቦት እንዲኖር እና የውጭ ምንዛሬ አቅርቦት እንዲሳለጥ ለማድረግ መሆኑን ጽህፈት ቤቱ ገልጿል።

አዲሱ ፖሊሲ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ከዓለም አቀፍ ገበያ ጋር ያለውን ትስስር “ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር” ያስችላል ተብሎ ታምኖበታል። ፖሊሲው ከዚህ በተጨማሪ “የስራ እድል ፈጠራ እንዲጎለብት” እንዲሁም “ኢኮኖሚያዊ ውጤታማነትን እና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን ለማረጋገጥ” የሚያስችል መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት መግለጫ ጠቁሟል። የባንክ ዘርፍን ለውጭ ኢንቨስተሮች ክፍት ማድረግ “የዘርፉን አገልግሎቶች በእውቀት እና በቴክኖሎጂ ለመደገፍ” የሚያግዝ መሆኑንም የጽህፈት ቤቱ መግለጫ አክሏል።

ጠ/ አብይ አህመድ ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ ባንክ ለውጭ ኢንቨስተሮች ክፍት ስለማድረግ ተናግረው ነበር፣ ባለፈው የካቲት 15፤ 2014 በፓርላማ ተገኝተው በሰጡት ማብራሪያ፤ የውጭ ሀገር ባንኮችን ወደ ኢትዮጵያ ለማስገባት “የፖሊሲ ማሻሻያ ለማድረግ ቅድመ ዝግጅት” እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

ጠ/ሩ ማብራሪያቸው “ተጨማሪ ሀብት፣ ተጨማሪ የውጭ ምንዛሬ ማግኘት ስላለብን [የውጭ] ባንኮች እናመጣለን። የሀገር ውስጥ ባንኮች ዝግጅት ማድረግ ይኖርባቸዋል” ሲሉ አሳስበው ነበር። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
20.4K views12:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-03 13:34:00
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 13ኛ መደበኛ ስብሰባ የባንክ ዘርፍን ለውጭ ኢንቨስተሮች ክፍት ለማድረግ በቀረበ ረቂቅ ፖሊሲ ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ፡፡

#PMOEthiopia
ዝርዝሩን ቴሌግራም
https://t.me/MuktarovichOusmanova
20.6K views10:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-03 12:49:25
በምዕራብ ግንባር የወገን ጦር በጠላት ላይ እያሰመዘገባቸዉ ያሉ ድሎች ቀጥለዋል የጠላት ሀይል ሲጠቀምበት የነበረው ግዴማ መስመር ያለ ምሽግ ልዩ ቦታው ጀንጅሪት እየተባለ የሚጠራው በወገን ሀይል ከጥዋቱ 4:30 አካባቢ በቁጥጥር ስር የዋለ መሆኑ ጅንጅሪት አካባቢ ተበታትኖ የሚገኘውን የጠላት ሀይል የወገን ሀይል የማፅዳት ስራ እየሰራ የሚገኝ ሲሆን እየሸሸ የሚሄደውን የጠላት ሀይል አሻባ ላይ የሱዳን ወታደሮች መሳሪያቸውን እንዲያራግፉ እያደረገ ይገኛል።(ጅንጅሪት ወደ ሃሻባ የጀልባ መሻገሪው አካባቢ ቦታ ነው በዚህ ውጊያ ኮ/ል መኮነን ሀይሉ የተባለ ክ/ጦር አዛዥ አዛዥን ጨምሮ በሺዎች የሚቆጥር ሬሳ ቡድኑ ጥሎ እየሸሸ መሆኑን፤ የቻለውን ቁስለኛ ደግሞ ዝሃና ወደ ተባለ የሱዳን ከተማ ለመውሰድ ጥረት እያደረገ ነው፤
Natnael Mekonnen
21.0K views09:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-03 11:45:37
በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ከወሰዳቸው 60 ኮርሶች ራጂ አሸናፊ ሁሉንም A+ በማምጣቱ የአሜሪካው MIT ዩኒቨርሲቲ የዶክትሬት ትምህርቱን እንዲማር ጥሪ ባደረገለት መሰረት ወደ አሜሪካ መልካም የትምህርት ዘመን ይሁንልህ ወንድማችን....

ምንጭ ፦ የወንጌል ድምፅ
21.3K views08:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-03 11:31:12
የኢትዮጵያ ጥምር ጦር በህወሀት ላይ እያሳረፈበት ያለው ጡጫ ከባድ ስለሆነ የተባበሩት መንግስታት በኢትዮጰያ ጉዳይ ካልተሰበሰብኩ ብሏል።

ሲታሰር ወደኔ ሲፈታ ወደ እሱ

እንደተባለው ነው።

ኢትዮጵያውያን ሁሉ የፖለቲካ ልዩነት ወደ ጎን በማድረግ ለሀገር በጋራ እንቁም
21.8K views08:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ