Get Mystery Box with random crypto!

ማኅበረ ቅዱሳን (Mahibere Kidusan)

የቴሌግራም ቻናል አርማ mahiberekidusan — ማኅበረ ቅዱሳን (Mahibere Kidusan)
የቴሌግራም ቻናል አርማ mahiberekidusan — ማኅበረ ቅዱሳን (Mahibere Kidusan)
የሰርጥ አድራሻ: @mahiberekidusan
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.86K
የሰርጥ መግለጫ

🌷ይህ ቻናል የተከፈተው ለመላው የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ክርስትና እምነት ተከታይ ሲሆን ዋና አላማውም ምዕመናን በንስሐ ህይወት ተመላልሰው የእግዚአብሔርን መንግሥት እንድወርሱ የሚያስችል ትምህርት መስጠት ነው፡፡
🌷💚የቅዱሳን ገድላት
🌷💛ስንክሳር
🌷♥ ቅዱሳን ስዕላት
መንፈሳዊ ትምህርቶችና ጽሑፎች
🎤 ስብከቶች ............ይቀርቡበታል፡፡🌎

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-25 14:44:35 /2ኛ ኮርስ - ነገረ ሃይማኖት/

#በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ_አሜን

#የቀጠለ.......
__
#ዕፀ_በለስ
ይህቺ ዕፅ እግ
ዚአብሔር በገነት በምዕራብ በኩል የተከላት ሲሆን አዳምና ሔዋን እንዳይበሏት የከለከላቸው ብቸኛይቱ ዕፅ ነች፡፡
እንዳይበሏት ሲከለከሉ እንኳን ሔዋን ራሷ እንደ ተናገረችው ነፍጓቸው ወይም ተመቅኝቶዋቸው ሳይኾን፦

አንደኛ) ስለ ፍቅሩ ለፈጠረው ለእግዚአብሔር በፍቅር በመታዘዝ እንዲመልስ

ሁለተኛ) ፍጡርነቱን እንዲያውቅባት

ሦስተኛ) ነጻ ፈቃዱ እንዲገልጥባት የተሰጠችው ናት፡፡
ቸሩ እግዚአብሔር “ትሞታለህ” ሲለው እንኳን እግዚአብሔር ስለ ጥልቅ ፍቅሩ አዳምን የመከረው እንጂ ጠበኛ አምላክ ሆኖ የተናገረው አይደለም፤ እገድልሃለሁ አላለውምና፡፡

እዚህ ጋር መረዳት ያለብን ዕፀ በለስ በራሷ መልካም መሆኗን ነው፡፡
ፍሬዎቿም እንደዚሁ መልካም ናቸው፡፡ በውስጧ ሞትን የተሸከመች ወይም መርዝነት ያላት አይደለችም፡፡ ስለዚህ ዕፀ በለስ ልክ በዕፀ ሕይወት ላይ እንደተነጋገርነው የሕግ ምልክት ናት፡፡ በመሆኑም አዳም የሞት ሞትን የሞተው የሕግ ምልክት ኾና የተሰጠችውን ዕፅ ባለመታዘዙ ስለ በላት እንጂ ዕፀ በለስ የምትገድል ኾና አይደለም፡፡

በሌላ አገላለጽ አዳምን የጣለው አለመታዘዙ ነው። እንደ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ደግሞ ግድ የለሽነቱ ነው፡፡

በዕፀ በለስ ውስጥ ከዕውቀት በቀር ምንም የለም፡፡ ዕውቀት ሲባል ራሱ አዳምና ሔዋን ከክብር መዋረዳቸውን ማወቅን ነው እንጂ ሌላ አይደለም፡፡ አንዳንድ ሰዎች እንደሚሉት ዕፀ በለስ በጎ ዕውቀትን የምታሳውቅ ዛፍ ብትኾን ኖሮ ኃጢአት “ኃጢአት” ሳይሆን “የዕውቀት አስተማሪ” በተባለ ነበር፤ እባብ በእርሱ አንጻርም ዲያብሎስ ባልተወቀሰ “የሐሰት” ሳይሆን “የጥበብ አማካሪም” በተባለ ነበር፡፡
ነገር ግን አይደለም አዳምና ሔዋን መልካም የተባለው መታዘዝ፣ ክፉ የተባለውንም አለመታዘዝ ከመውደቃቸው በፊት ያውቁ ነበር፡፡

ዛሬ በዕፀ በለስ ምክንያት የመጣው ሞት በዕፀ መስቀል ምክንያት ተወግዶልናል፡፡
~~~~

ቀጣይ ትምህርታችን
የዕለት ረቡዕ ሥነ ፍጥረታት
#ወስብሐት ለእገዚአብሔር_ወለወላዲቱ_ድንግል_ወለመስቀሉ_ክቡር_ይቆየን!!

@mahiberekidusan
@mahiberekidusan
@mahiberekidusan

❹⓪
352 views𝐊𝐢𝐧𝐠𝐬𝐭𝐨𝐧 𝐄𝐭𝐡𝐢𝐨𝐩𝐢𝐚, 11:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 17:23:17 (2ኛ ኮርስ - ነገረ ሃይማኖት)

#በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ_አሜን

የቀጠለ.......
__
#በገነት_ውስጥ_ስለ_በቀሉት_ዕፅዋት
እግዚአብሔር አምላካ
ን በገነት ውስጥ (ለአዳም) ሦስት ዓይነት ዕፅዋትን ፈጥሮለታል፡፡
አንዱ - የሚመገበው
ሁለተኛው - የሚጠብቀው - ዕፀ በለስ
ሦስተኛው ደግሞ የሚታደስበት - ዕፀ ሕይወት ነው
እስኪ በጥቂቱም ቢኾን ስለ እነዚህ ዕፅዋት እና ስለ አዳም እንመልከት፡-


#እንዲመገባቸው_የተሰጡት_ዕፅዋት
ሰው ወዳጁ እግዚአብሔር በገነት ውስጥ ታላላቅና ታናናሽ ዕፅዋትን ያበቀለ ሲኾን ታናናሹ ብቻ ቅጠላቸው ዐሥራ ኹለት ዐሥራ ኹለት ክንድ ያክላል፡፡ እንደ ኮከብም ያበራል፡፡ ፍሬአቸውም ክብ ነው፡፡ ዛሬ እነዚህን ዕፅዋት የሚመገቡት በብሔር ብጹዓን ያሉ ጻድቃን ቅዱሳንና በገነት ያሉ አዕዋፍ ናቸው፡፡ የሚያመጣላቸውም ነፋስ ነው፤ ነፋሱ እንደ ዝናብ ያዘንብላቸዋል፡፡ ያን ተመግበውም ፈጣሪያቸውን ሲያመሰግኑ ይኖራሉ /ገድለ ዞሲማስ/፡፡



#ዕፀ_ሕይወት
አበው እንደሚነግሩን ዕፀ ሕይወት ጫፏ ከሰማይ ይደርሳል፡፡ ፍሬዋ እንደ ሮማን ፍሬ ተነባብሮ ከእግር እስከ ራሷ ምሉ ነው፡፡

ከዕፀ ሕይወት ፍሬ አንዲቱን ቆርጦ በአፉ ጎርሶ አላምጦ ሳይውጣት እንደ ቀድሞው ፍሬ ተክታ ትገኛለች። /ሕዝ.47፡12-13፣ ራእ.22፡2-3/፡፡

ከዕፀ ሕይወት አንዲቱን ፍሬ በበሏት ጊዜ ጣዕሙ ከአፍ፣ መዓዛው ከአፍንጫ ሳይለይ እስከ ሰባት ቀን ይቀመጣል (ኄኖ 7፥6-16)
ከዚህች ዕፅ የቀመሱ ሰዎች “እንዲህ ያለውስ ምግብ ያለ እግዚአብሔር ቸርነት ለፍጡር አይገባውም ነበር” እያሉ ያደንቃሉ፡፡ ቅጠሏ፣ አበባዋ፣ ፍሬዋ ያለ ደዌ ያለ ሕማም ነፍስን ከሥጋ ይለያል፡፡

እግዚአብሔር አምላካችን ዕፀ ሕይወትን ብላም አትብላም አላለውም፡፡ ይህ ለምን እንደ ኾነ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ሲመልስልን እንዲህ ይለናል፡-
“አዳም ቢፈልግ ኖሮ ይህን ዘለዓለማዊ ሕይወት የሚሰጠውን ዛፍ ከሌሎች ዛፎች ጋር አብሮ መብላት ይችል ነበር፤ በመኾኑም ስለ ዕፀ ሕይወት ብላም አትብላም አላለውም፡፡”
ከዚህ መረዳት እንደምንችለው የሰው ልጅ (አዳም) የራሱ የኾነ ነጻ ፈቃድ አለው፡፡ ይህ ነጻ ፈቃዱ እንኳንስ ዲያብሎስ እግዚአብሔርም ቢኾን ጣልቃ የሚገባበት አይደለም፤ ሰው ራሱ እንደ ውዴታው የሚያዘው እንጂ፡፡ በመኾኑም በዚህ ነጻ ፈቃዱ ከፈለገ ይህን ዕፀ ሕይወት በልቶ ለዘለዓለም መኖር ይችል ነበር፡፡ ውሳኔው ለራሱ ለአዳም የተተወውም ስለዚሁ ነው፡፡

መረዳት ያለብን ግን ዕፀ ሕይወት ሲባል ዕፁ በራሱ ሕይወትን የሚሰጥ ነው ለማለት አይደለም፡፡ ዕፁ የመታዘዝ ምልክት ነው፤ እግዚአብሔርን ቢታዘዝና እንደ ሕጉ ቢኖር ይህቺን ዕፅ በልቶ ይታደስ ነበር፡፡

ይታደስ ነበር ሲባል የሰው ልጅ በመዋቲነትና በኢመዋቲነት መካከል ኾኖ ተፈጥሮ ስለ ነበር ወደ ኢመዋቲነት ይሸጋገር ነበር ማለት ነው፡፡ በበደለ ጊዜ ይህቺን ዕፀ ሕይወት እንዳይበላ መከልከሉም ስለዚሁ ነው፡፡ ምክንያቱም ከበደሉ ሳይነጻ ይህቺን ዕፅ ቢበላ ኖሮ ለዘለዓለም እየበደለ ነበር የሚኖረው፡፡ በበደሉ ምክንያት የመጣበት ጉስቁልና ለዘለዓለም አብሮት ነበር የሚኖረው፡፡ እንደ ዲያቢሎስ አመፀኛና እርጉም ሁኖ ይቀር ነበር።

ሰው ወዳጁ እግዚአብሔር ግን መጀመሪያ ሞቱንና ጉስቁልናዉን አስወግዶ ወደ ቀድሞ ቦታው ወደ ገነት ወደ ቀድሞ ክብሩ ወደ ልጅነት ይመልሰው ዘንድ ከገነት እንዲወጣና ከዚህች ዕፅ እንዳይበላ አደረገው፡፡

ዛሬ ይህ ዕፀ ሕይወት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ሥጋውና ክቡር ደሙ ኾኖ ተሰጥቶናል /የሐሙስ ውዳሴ ማርያም/፡፡
~~~~

ቀጣይ ትምህርታችን
ስለ ዕፀ በለስ
#ወስብሐት ለእግዚአብሔር _ወለወላዲቱ_ድንግል_ወለመስቀሉ_ክቡር_ይቆየን!!

@mahiberekidusan
@mahiberekidusan
@mahiberekidusan
❸➒
379 views𝐊𝐢𝐧𝐠𝐬𝐭𝐨𝐧 𝐄𝐭𝐡𝐢𝐨𝐩𝐢𝐚, 14:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-23 10:47:33 (2ኛ ኮርስ - ነገረ ሃይማኖት)

#በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ_አሜን

የቀጠለ......
__
, ዓለማተ ማይ/ውሃ፦ ዓለማተ ውሀ በአራት የተከፈሉ
ሲሆኑ በዝርዝር እንያቸው
1ኛ, ሐኖስ፦ ሐኖስ ከኤረር በታች የሚገኝ ውሃ ነው በዚህ አለም ላይ ምንም ፍጥረት አይገኝም ውሃው እንዳይፈስ ባቢል የሚባል ንፋስ ተሸክሞታል። የሐኖስ ስፋቱ በምድር ልክ ነው። ሐኖስ ከምድር ዳርቻ ካለው ውሃ ጋር በጠፈር ይገናኛል።

2ኛ, ጠፈር፦ ጠፈር ከሐኖስ በታች ከውቅያኖስ በላይ ያለ የውሐ ዓለም ነው። ውሃውም የረጋ ነው። ይህንን የውሃ ዓለም የብርሃናት መመላለሻ የዓይን ማረፊያ አድርጎ ፈጥሮታል። በጠፈርም ምንም ሕይወት ያለው ፍጥረት የለም።


3ኛ,በምድር ዙሪያ ያለው ውቅያኖስ ነው። ውቅያኖስ በምድር ዙሪያ ሙሉ ነው ከውቅያኖስ በኋላ ደረቅ ምድር የለም ዝናብም የሚዘንበው ከውቅያኖስ ተቀድቶ ነው በዚህም አስደናቂ ፍጡራን ይኖራሉ እግዚአብሔር በሁለቱ ፍጥረታት ምድርን አጥሯል እነሱም ብሔሞትና ሌዋታን የሚባሉ የዘንዶ ዘሮች ላም መሰል ናቸው።

ብሔሞት እና ሌዋታን ዓለምን እንደ ቀለበት የጠመጠሙ ናቸው መንቀሳቀስ አይችሉም ከውሃ ውስጥ የተፈጠሩ ግን በየብስ ሚኖሩ የሐሙስ ፍጥረት ናቸው።

ብሔሞት፦ ግሩማን አራዊት/ የአራዊት ራስ/ የፍጥረት ቀንድ የሌዋታን ወንድም ነው።
ከአፉ ፋና፤ ከአፍንጫው ጢስ ይወጣል እጢስታው ብልጭታ ያመጣል።

ብሔሞት ዮርዳኖስን ጠጥቶ የማይጠግብ በቀን 1,000 ዝሆን መመገብ የሚችል ነው።
ግን በእግዚአብሔር ፍቃድ ማርና ወተት እየተመገቡ ይኖራሉ።

ሌዋታን፦ አንእስት የብሔሞት ጣምራ አብራው የተፈጠረች ናት
ብሔሞት በስተቀኝ ሌዋታን በስተግራ ተቀምጠዋል።

መገኛቸው በገነት በምስራቅ በኩል ባለ ዴንዳይን በሚባል ምድረ በዳ ነው። (ሄኖ 16፥14)
እነዚህን የተለዩ ፍጥረታት በቅድስና 10ኛው ደረጃ የደረሰ ሰው ማየት ይችላል።
አቡነ ዘርዓብሩክም ጥርሳቸውን ቆጥረው መምጣት ችለዋል።

እነዚህ እንሰሳት የእግዚአብሔር ፍጥረት አውራ ናቸው እግዚአብሔር አይቶም ይደሰትባቸዋል።


ከዚህ በተጨማሪም ካልህ የተባለ ፍጥረት ይገኛል።

ካልህ ከወገቡ በላይ የሰው መልክ ያለው ከወገቡ በታች ደግሞ የአራዊት መልክ ያለው ፍጡር ነው ወይም ደግሞ ከወገቡ በላይ የአራዊት ከወገቡ በታች የሰው መልክ ያለው ሊሆን ይችላል።


4ኛ, ከምድር በታች ምድርን የተሸከመው ውሃ ነው። ይህ ውሃ በእሳትና በመሬት ዓለማት መካከል ይገኛል። ከምድር በታች ባለው ውሃ ፍጥረታት አይኖሩም እስከ ምፅዓት ድረስ ምድርን ተሸክሞ ይኖራል።

, ዓለማተ ነፋስ/የነፋስ ዓለም፦ ዓለማተ ነፋስ በሁለት ይከፈላሉ።
1ኛ, ባቢል፦ ባቢል
ከጠፈር በላይ ያለውን የውሃ ዓለም ሐኖስን ተሸክሞ እስከ ምፅዓት ይኖራል። ባቢል አይንቀሳቀስም። ምክንያቱም ሐኖስ የተባለውን የውሃ ዓለም እንዳይፈስ ተሸክሟልና በዚህ ዓለም ፍጥረታት አይኖሩም።

2ኛ, ከምድር በታች ያለው እሳትን የተሸከመው ነፋሳ ነው ይህ ንፋስ እስከ ምፅዓት ድረስ ዓለመ እሳትን ተሸክሞ የኖራል። ይህ ዓለመ ነፋስ በ12 ይከፈላል። 4ቱ የምህረት ንፋሳት እና 8ቱ የማአት ንፋሳት ተብለው ይጠራሉ።
4ቱ የምህረት ነፋሳት በዝች አለም ፍጥረታትን ያገለግላሉ 8ቱ የማአት ንፋሳት እግዚአብሔር ሲቆጣ መሬትን የሚያገላብጡና በዕለተ ምፅዓት ዓለማትን ሁሉ የሚደመስሱ ናቸው።
~~~~

ቀጣይ ትምህርታችን
በገነት ስለ ነበሩት ጠቅላላ ዕፀ በለስ
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር_ወለወላዲቱ_ድንግል_ወለመስቀሉ_ክቡር_ይቆየን!!

@mahiberekidusan
@mahiberekidusan
@mahiberekidusan

❸➑
381 views𝐊𝐢𝐧𝐠𝐬𝐭𝐨𝐧 𝐄𝐭𝐡𝐢𝐨𝐩𝐢𝐚, 07:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 15:05:41 #በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ_ዘለዓለም_ሥላሴ_አሜን።

#እንኳን_ለእመቤታችን_ለቅድስት_ድንግል_ማርያም_ጾመ_ፍልሰታ የፍቺ በዓል ና ለእመቤታችን የትንሳኤና የዕርገት በሰላምና በጤና አደረሰን አደረሳችሁ!

በአጽናፈ ዓለም የምትኖሩ/የምትገኙ ውድ የክርስትና እምነት ተከታዮች የተዋህዶ ልጆች ክርስቲያናዊ ሰላምታችን በቅዱስ እግዚአብሔር ስም ይድረሳችሁ፡፡

#የእመቤታችን_ትንሣኤና_ዕርገት_

ነሐሴ 16 ቀን የእመቤታችን ድንግል ማርያም ሥጋዋ ያረገበት ዕለት ነው።
#እመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም በዚህ ምድር የኖረችው ስልሳ_አራት ዓመት ነው፡፡ እነዚህ ዓመታት ሲተነተኑ ሦስት ዓመት በወላጆቿ ሐናና ኢያቄም ቤት፣ ዐሥራ ሁለት ዓመት በቤተ መቅደስ፣ ሠላሣ ሦስት ዓመት ከሦስት ወር ከልጇ ከወዳጇ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር አሥራ አምስት ዓመት ከሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ጋር ነው፡፡
እመቤታችን እመ አምላክ በስዕለት የተወለደች ፣ በጸጋ የተሞላች፣ ባለሟልነትን የተጎናጸፈች፣አምላክን በአጭር ቁመት ፣በጠባብ ደረት የወሰነች፣የመለኮቱ እሳትነት ስጋዋን ሳያቃጥላት አምላክ ፈጣሪዋን ጸንሳ የወለደች ፣ በግብፅ በርሃ በስደት የተንከራተተች፣ በእውነቱ የህይወትን ምግብ አዝላ ስለእኛ የተራበች ፣የተጠማች፣ ከመዓር ከስኳር የሚጥም ጡቶቿን ያጠባችው ልጇ በቀራኒዮ ኮረብታ ተሰቅሎ ሲሞት መሪር እንባን ያለቀሰች፣ ለቅዱሳን ስደትን ለመባረክ ምሳሌ በመሆን የተጓዘች የተንገላታች ... ድንቅ ዘለዓለማዊ እናት ነች። አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በቅዳሜ አርጋኖን ሶስቱ ያልተከፈቱ ደጆች ይልና ። ያብራራል ። አንድም በድንግልና መጽነሷን፦ ድንግልናዋን ሳይለውጠው እግዚአብሔር ወልድ በግብረ መንፈስ ቅዱስ የመጸነሱ፤ በሁለተኛ ደረጃ ክርስቶስን በምትወልድበት ጊዜ የሴቶች ልማድ ሳያገኛት በጥበበ እግዚአብሔር መውለዷ፤ በሶስተኛ ደረጃ ደግሞ ከወለደችው በኋላ ማህተመ ድንግልናዋ አልተፈታም። እመቤታችን ዘላለማዊ ድንግል ናት። የስጋ ብቻ ያይደለ የሀሳብም ድንግል ናት።

አጠር ባለ አገላለጽ አምላክን ከመውለዷ በፊት፣ አምላክን በምትወልድበት ጊዜ እና አምላክን ከወለደች በኋላ ፍጹም ዘላለማዊ ድንግል መሆኗን ሊቁ ያስረዳል ። እመቤታችን ጥር 21 ቀን በ50 ዓ.ም ከዚህ አለም ድካም አርፋ ወደ ልጇ ተጠርታ ሄዳለች።

ወላድተ አምላክ ባረፈችበት ወቅት ቅዱሳን ሐዋርያት ክቡር ሥጋዋን ለማሳረፍ ወደ ጌቴ ሴማኒ ሲሔዱ አይሁድ "ቀድሞ ልጇ በሦስተኛው ቀን ሞትን ድል አድርጎ ተነሣ፤ በአርባኛውም ቀን ወደ ሰማይ ዐረገ፤ ተመልሶም ይህን ዓለምን ለማሳለፍ ይመጣል እያሉ በማስተማር ሕዝባችንን ወስደውብናል፡፡ አሁን ደግሞ ዝም ብለን ብንተዋት እርሷም እንደ ልጇ ተነሳች እያሉ በማስተማር ሊያውኩን አይደለምን? ኑ! ተሰብስበን በእሳት እናቃጥላት" ብለው ክፉ ምክር ተማከሩ፡፡

አይሁድም ከተማከሩ በኋላ ከመካከላቸውም ብርቱ ጉልበተኛ ሰው የሆነው #ታውፋንያ የተባለ ቅድስት ሥጋዋን ከሐዋርያት ነጥቆ ለማስቀረት ክቡር ሥጋዋ ያለበትን የአልጋ ሸንኮር ሲይዝ በመልአከ እግዚአብሔር እጁ ተቆርጣ ከአልጋው ላይ ተንጠልጥላ ቀረች፤ ከዚህ የጥፋቱ ሥራው ተምሮ እመቤታችንን በመለመኑ እመቤታችን የተቆረጠች እጁን መልሳለታለች፡፡

ከዚህ በኋላ መልአከ እግዚአብሔር የእመቤታችንን የተቀደሰ ሥጋዋን ጌታችን ይወደው የነበረ ተብሎ የተነገረለት ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስን ይዞ በገነት በዕፀ ሕይወት ሥር አስቀመጠው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስም የሆነውን ሁሉ ለወንድሞቹ ቅዱሳን ሐዋርያት ነገራቸው፡፡ እነሱም የእመቤታችን ሥጋ በክብር ለማሳረፍ ካላቸው ጉጉት የተነሣ ከነሐሴ 1 ቀን ጀምሮ ሱባኤ ገቡ፡፡

ከሁለተኛ ሱባኤ ቆይታቸው በኋላ በአሥራ አራተኛ ቀናቸው ጌታችን የእመቤታችንን ትኩስ ሥጋ ሰጣቸው፡፡ ሐዋርያትም በዝማሬና በታላቅ ምስጋና በጌቴ ሴማኔ ቀበሯት፡፡ ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊት ‹‹አቤቱ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ አንተና የመቅደስህ ታቦት› › ተብሎ ትንቢት የተናገረውን ሲተረጉሙት ‹‹ፈጣሪያችን እግዚአብሔር ሆይ፥ ወደ መንግሥተ ሰማያት የምታሳርፈው የመቅደስህ ታቦት የሆነችውን ድንግል ማርያምን ይዘህ ተነሥ›› ብለው ያመሰጥሩታል፡፡ /መዝ. 131፥8/፡፡

የእመቤታችንን ቅድስት ሥጋዋን ሐዋርያት ሲቀብሯት በሀገረ ስብከቱ ሕንድ የነበረው ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ ከሀገረ ስብከቱ በደመናሰረገላ ተጭኖ ሲመለስ እመቤታችን ስታርግ አገኛት። ለማረጓ ምልክት ይሆን ዘንድ ለምልክት እንዲሆነው ሰበኗን (የመግነዟን ጨርቅ) ተቀብሏት ይለያያሉ፡፡ ለወንድሞቹ ለቅዱሳን ሐዋርያት ያየውን ምስጢር/የተመለከተውን ድንቅ ተዓምር/የወላድተ አምላክን ዕርገት ነገራቸው፡፡

እመቤታችን ለበረከት የሰጠችውንም ሰበን አሳያቸውና አካፈላቸው ፤ ሐዋርያት ‹ ‹ዕርገቷን እንዴት እሱ ብቻ ተመልክቶ ለምን እኛ ይቀርብናል› › ብለው በዓመቱ ነሐሴ አንድ ቀን ሱባኤ ገቡ፡፡ ነሐሴ 16 ቀን የልባቸው መሻት ተፈጸመላቸው፡፡ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እመቤታችንን መንበር፣ ቅዱስ ጴጥሮስን ንፍቀ (ረዳት) ቄስ፣ ቀዳሚ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስን ገባሬ ሰናይ (ዋና ዲያቆን) አድርጎ ቀድሶ ሁሉንም አቆረባቸው፡፡

በንጽህና፣ በፍጹም እምነት ፣በትኅትና የያዙት በተስፋ የጠበቁት በአንድነት ወደ እግዚአብሔር ያቀረቡት ሱባኤም የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ዕርገቷን ለማየት አበቃቸው፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንም ይህን መሠረት አድርጋ ከነሐሴ 1-16 ጾመ ፍልሰታ በማለት ከሰባቱ አጽዋማት አንዱ አድርገን እንድንጠቀምበት ሥርዐት ሠራችልን፡፡

በቅዱሳን አበው በነቢያትና በሐዋርያት በቅዱሳን ሁሉ መሠረት ላይ የታነጽን ኦርቶዶክሳውያን የተዋሕዶ ልጆች በየዓመቱ ይህን ጾም በሱባኤ በማሳለፍ ከእመቤታችን ጸጋና በረከት ተሳታፊዎች እንሆናለን፤ ሆነናልም፡፡ ለቅዱሳን ሐዋርያት ትንሳኤዋን ፣ ዕርገቷን እንደገለጸችላቸው ለእኛም ምስጢርን ፣ እውቀትን ታድለን ። ትግለጽልን ። የአመት ሰው ይበለን። መልካም በዓል

ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከወላድተ አምላክ በረከት፣ረድኤት ፍቅር፣ምልጃና ጸሎት ተካፋዮች ያድርገን፡፡
አሜን!
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን
#ለወዳጅዎ_ዘመድ_ ፣_ለተዋህዶ_ልጆች #ሼር_ያድርጉ!
@mahiberekidusan
@mahiberekidusan
@mahiberekidusan
393 viewsKingston Ethiopia, 12:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-20 08:15:48 #በስመ-አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን

መንፈሳዊ ግጥም

#ደብረ_ታቦር

ከደብሮች ሁሉ ልቀሽ
እውነት ብርሃንን አጥልቀሽ
ተንቀሽ የነበርሽ ተራራ
አንቺ የምሥጢር ሥፍራ
የመለኮት ብርሃን በር
የሥሉስ ቅዱስ ምሥጢር
ልቆ የታየብሽ መንደር
ደብረ ታቦር!!!
ከአድማሳት ከፍ ከፍ ብሎ
የስምሽ ተረፈ ውሉ
የተዘከረው በዓለሙ
ምን ይሆን ወርቅ ሰሙ?
ምን አገኘሽ ያኔ ታቦር
እንዲያ ተከፍቶ የብርሃንሽ በር
የክብሩ ግርማ የዋጠሽ
እኮ ማን ነው የረገጠሽ?
ጌታሽ ነው አሉ ስሰማ
ከተራራሽ አናት ማማ
የብርሃን ጉንጉን ሸማ
ያጎናፀፈሽ በግርማ
ግሩም እኮ ነው!
ከተራሮች አንቺን መርጦ
ከነአባቱ ተገልጦ

ደጅሽን ሳይንቅ ማክበሩ
እንዴት እንዴት ይሆን ምሥጢሩ?
ይህንንም ደግሞ ዳዊት
ተናግሯል አሉ በትንቢት
ታቦር ወአርሞንኤም በሚል ቅኔ
በስሙ ተደሰቱ ያኔ
እያለ ዘመረ በክብር
የዚህችን ተራራ ምሥጢር
ያ ልበ አምላክ ዳዊት
የተናገረው ትንቢት
ለካ ይህ ኖሯል ግቡ
ደጅሽ በብርሃን ማበቡ
ኧረግ! አንቺስ ታድለሻል
የማይቻለውን ችለሻል
እሳተ መለኮትን ይዘሻል
ለመሆኑ እንዴት ቻልሽው ታቦር
ያን እውነተኛ ፍቅር?
ከመንበሩ የሳበው ንጉሥ
በብርሃን ሠረገላው ሲፈስ
መሠረትሽ ሳይናጋ
ባለበት ቆሞ የረጋ
ምን ይሆን ምሥጢሩ የፅናትሽ
በፊቱ ቆመሽ መታየትሽ?
ልብሱ ነጭ ሆኖ በረድ
አብም ከሰማይ ሲወርድ
ዙሪያው በክብር ደመና
ተመልቶ በብርሃን ፋና
ሙሴ ከመቃብሩ ተጠርቶ
ኤልያስ ከብሄረ ሕያዋን መጥቶ
በኢየሩሳሌም ስለሚሆነው
ሲወያዩ ላስተዋለው
ምን ይመስል ይሆን ገጹ?
የብርሃን መለኮት መገለጹ
ደግሞ የሐዋርያቱ
የእነዚያ የሦስቱ
ሲጋልቡ ርደው
እንደ ቄጤማ ወርደው
ከሰሩ የተነጠፉቱ
ምንድን ይሆን ምክንያቱ?
ጴጥሮሰማ ተሽብሮ
ናላው በድንጋጤ ዞሮ
ለእያንዳንዳችሁ በጋራ
ሦስት ዳሶችን እንስራ

ብሎ በዚያች የብርሃን እልፍኝ
የዘለዓለም ደስታን ሊያገኝ
አስቦ በቅጽበት መመኘቱ
ገርሞትም አይደል ክስተቱ
የብርሃን ፀዳል ድምቀቱ?
እኮ እንደምን አይገርመው
ሙሴና ኤልያስ ቆመው

ክብሩን ሲያውጁ እያዩ
ማነው የሙሴን አምላክ ሙሴ ባዩ?
ሲል ሙሴ ባሕር ከፋዩ
የኤልያስንስ ክብር ጌታ
አውርደውት ከሰው ተርታ
ኤልያስ ባዮቹ እነማን ናቸው?
ሲል ኤልያስ ገርሟቸው

ይህን ሲሰሙ ሐዋርያቱ
በድንጋጤ ሲመቱ
ደግሞ ወርዶ አባቱ
ልጄን ስሙት በማለቱ
በፍርሃት ማዕበል ሲንገላቱ
ይህ ሁሉ ምስጢር መታየቱ
በአንቺም አይደል ታቦር
መገለጹ የሦስትነት ምስጢር
ጥንትስ ታሪክሽ ተዘክሮ
መቼ ያልቅና ተነግሮ
እንዲያው ድንቅ
እንበል እንጂ ድንቅ ድንቅ!
የብርሃንሽ ሰንደቅ
ከአድማሳት ልቆ ሲደምቅ

ክብር እንበልሽ ክብር!ክብር!
አንቺ እውነተኛ የምስጢር በር
የሥሉስ ቅዱስ ነገር
የተገለጸብሽ መንደር
ደብረ ታቦር!!!
ያበራሽ ይብራ ስሙ ይግነን
ዛሬም ለእኛ ብርሃን ይሁነን
ገኖ ያግነን በፈቃዱ
በራ ይሁንልን መንገዱ
ክብሩም ከፍ ከፍ ወደ ላይ
ከሰማየ ሰማያት በላይ
እንዲሁም በምድር በቀላይ
የአምላካችን አዶናይ
ክብርሽ ዛሬም ነገ ይነገር
መሆንሽ እውነተኛ የብርሃን በር
የሥሉስ ቅዱስ ምስጢር
የተገለጠብሽ መንደር ደብረ ታቦር!!!

ልዑል አምላካችን ቅዱስ እግዚአብሔር በብርሃነ መለኮቱ ዘመናችንን ፣ ህይወታችንን ያብራልን። መልካም በዓል

ወስበሐት ለእግዚአብሔር።
@mahiberekidusan
@mahiberekidusan
@mahiberekidusan
464 viewsKingston Ethiopia, 05:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-19 12:34:37 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ ዘለዓለም ሥላሴ አሜን፡፡
#እንኳን-ለደብረ ታቦር በዓል በሰላም አደረሰን፡፡
#ደብረ-ታቦር/ቡሔ
ነሐሴ 13 ቀን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብርሀነ መለኮቱን የገለፀበት ዕለት ነው፡፡ በዚች ዕለት አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሶስቱን ደቀ መዛሙርቱን ጴጥሮስን፣ያዕቆብንና ዮሐንስን ይዞ ወደ ተራራ ላይ ወጡ መልኩም በፊታቸው ተለወጠና ብርሃነ መለኮቱን ገለጸባቸው ልብሱም እንደ በረዶ ነጭ ሆነ ሉቃ 9፥28 ማቴ 17 ፥1
እነሆ ሙሴን ከመቃብር ኤልያስን ከብሔረ ህያዋን ጠቅሶ አምጥቶ አሳያቸው፡፡ ጴጥሮስም ይህንን አይቶ ጌታችንን እንድህ አለው፡፡አቤቱ ጌታ ሆይ በዚህ መኖር መልካም ነው ሶስት ሰቀላዎችንም እንስራ አንዱን ለአንተ አንዱን ለሙሴ አንዱን ለኤልያስ አለው፡፡ይህንንም በተናገረ ጊዜ ጌታችን በሰው እጅ የተሰራ ማደሪያ የማይሻ መሆኑን ለጴጥሮስ ያሳየው ዘንድ እነሆ ደመና ጋረዳቸው የጌታችንን ጌትነቱን የሚገልፅ በሐዋርያትም ልቡና እምነትን የሚያጸና እንድህ የሚል ቃል ከደመና ውስጥ መጣ ይህ የምወደው በእርሱ ደስ የሚለኝ ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት ሙሴና ኤልያስም ከእርሱ ጋር ሲነጋገሩት ትንቢታቸውንም በቸርነቱ አረጋግጦ ወደ ተራራ ላይ በመውጣቱ ነቢያት እና ሐዋርያት ደስ አላቸው፡፡ በአጠቃላይ ይህ ዕለት ጌታችን መድኃኒታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ መለኮቱን የገለጠበት ሙሴና ኤልያስን ለሶስቱ ምስጢረ ሐዋርያት ያሳየበት እርሱም ሁለመናው ነጭ ልብስ መልኩ እንደመብረቅ ሆኖ የታየበት ዕለት ነው ፡፡ በቤተክርስቲያናችን አስተምህሮ ይህ በዓል ከጌታችን አበይት በዓላት አንዱ እንደሆነ ታስተምራለች፡፡ ምዕመናንም በዓሉን በድምቀት ያከብሩታል፡፡ ዳቦ በመጋገር ምሳሌውም እረኞች በተራራው ላይ ብርሀኑን እያዩ በወጡበት አልተመለሱም ነበረና ቤተሰቦቻቸው ዳቦ ይዘው የመሄዳቸው ምሳሌ ነው ጅራፉ የነጎድጓድ ችቦ የሚበራው ወይም ደመራው የብርሃነ መለኮቱ ምሳሌ ነው፡፡ እናት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሁሉንም በምሳሌ ሰንዳ አስቀምጣለች፡፡ ለአባቶቻችን ምስጢሩን የገለጸ ለእኛም ይግለጽል፡፡ ስለ ሁሉም ነገር የቸርነቱን ስራ ይስራልን፡፡ ከበዓሉ በረከት ከቅዱሳን ምልጃና ጸሎት ከመላዕክት ጠባቂነት ከቅድስት ድንግል ማርያም እናትነትና ምልጃ ይክፈለን፡፡ "አድህነኒ እግዚኦ እስመ ኃልቀ ኄር ወውህዴ ኃይማኖት እመእጓለ እመህያው" መዝ 11፥1 አቤቱ ደግ ሰው አልቋልና አድነኝ፤ ከሰው ዘንድም መተማመን ጎድሏልና ።
#ሼር-ያድርጉ
#መልካም-በዓል-
#ወስብሐት-ለእግዚአብሔር ወለወላድቱ ድንግል ወለመስ ቀሉ ክቡር አሜን፡፡

@mahiberekidusan
@mahiberekidusan
@mahiberekidusan
446 viewsKingston Ethiopia, edited  09:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-19 10:27:02 እንኳን አደረሰን አደረሳችሁ ​ነሐሴ 13/12/2014 ዓ.ም
ደብረ ታቦር
በዕለቱ ቅዳሴ ሰዓት የሚነበቡ መልዕክታት፣ወንጌልና ምስባክ።

ዲያቆን፦ ዕብ 11÷23-30
ንፍቅ ዲያቆን፦ 2 ጴጥ 1÷15-ፍ.ም
ንፍቅ ካህን፦ ግብረ ሐዋርያት፦ 7÷44-51

ምስባክ ፦ መዝ 88፥12-14
ታቦር ወአርሞንዔም በስመ ዚአከ ይትፌስሁ ወይሴብሑ ለስምከ
መዝራዕትከ ምስለ ኀይል

ትርጉም ፦
ታቦር እና አርሞንዔም በስምህ ደስ ይላቸዋል
ስምህንም ይመሰግናሉ
ክንድክ ከኃይልክ ጋር ነው

ወንጌል ፦ ሉቃ 9÷28-38
ቅዳሴ ፦ ዘእግዝእትነ

@mahiberekidusan
@mahiberekidusan
@mahiberekidusan
832 viewsKingston Ethiopia, 07:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-16 16:55:28 ′ 2ኛ ኮርስ - ነገረ ሃይማኖት ′

#በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ_አሜን

የቀጠለ.......
__
ሃያው ዓለማት በ6 ቀን ከተፈጠሩት ጋር የተፈጠሩ
ቸው።

እነዚህ ሀያው ዓለማትን በአይነታቸው በ4 እንከ
ፍላቸዋለን

እነሱም፦
, ዓለማተ እሳት 9
, ዓለማተ ምድር 5
, ዓለማተ ውሃ 4
, ዓለማተ ነፋስ 2 ናቸው።

1
️⃣, ዓለማተ እሳት፦ ዘጠኝ ሲሆኑ በዝርዝር እንመልከታቸው

1ኛ, መ
በረ መንግስት ወይም መንበረ ጸባኦት፦ አጋአስት ዓለም ስላሴ የክቡር ዙፋናቸውን የዘረጉበት የመጀመሪያው ሰማይ ነው። ይህንንም አለም በአራት ተንቀሳቃሽ ፍጥረታት አምሳል የተፈጠሩ ኪሩቤል የተሰኙ መላአክት በአራት ማአዘን እርስ በርስ ሳይተያዩ በመቆም ዙፋኑን ተሸክመውታል።

አንደኛው ኪሩብ ገፀ ብእሲ/ሰብ ይባላል። የሰው መልክ ያለው ሲሆን ለሰው ልጆች በሙሉ የሚፀልይ ነው።

ሁለተኛው ኪሩብ ገፀ አንበሳ ይባላል። የአንበሳ መልክ ሲኖረው የሚጸልየው ለአራዊት ነው።

ሦስተኛው ኪሩብ ገፀ ላህም ይባላል። የላም መልክ ሲኖረው የሚጸልየው ለእንሰሳ ነው።

አራተኛው ኪሩብ ገፀ ንስር ይባላል። የንስር መልክ ሲኖረው የሚጸልየው ለአእዋፋት በሙሉ ነው።

ሱራፌል የተሰኙ 24 ካህናተ ሰማያት ይህን መንበረ ጸባኦት ዝንተ አለም ያለ እረፍት ያጥናሉ፤ ይሰግዳሉ ምስጋናም እረፍታቸው ነው።


2ኛ, ሰማይ ውዱድ፦ ሰማይ ውዱድ ማለት የተስማማ ሰማይ ማለት ሲሆን መላአክት የምስጋና መስዋኢት ይሰውበታል። ቅዱሳን መላእክትም ለአገልግሎት ወደዚህ ሰማይ ይመጣሉ ሱራፌልም ይገኙበታል።

3ኛ, ጸርሀ አርያም፦ ጸርሀ አርያም ማለት የሰማይ አዳራሽ ሲሆን በዚህ ሰማይ መላእክት አገልግሎት የሚከፋፈሉበት ነው። እረቂቅ የወርቅ ከበሮና እረቂቅ የወርቅ መቋሚያ ይዘው ከፊሉ በቅዳሴ ከፊሉ በስግደት ከፊሉ በልመና ከፊሉ በምስጋና ለማገልገል የሚከፋፈሉበት ነው።

ልክ በሶስት ክፍል እንደምትሠራ ቤተ ክርስቲያን መንበረ መንግስት እንደ መቅደስ ሰማይ ውዱድ ቅድስት ጸርሀ አርያም እንደ ቅኔ ማህሌት ሁነው በአምላካዊ ፍቃድ ተፈጥረዋል። ነገር ግን መንበረ መንግስት ሰማይ ውዱድና ጸርሀ አርያም ከላይ ወደ ታች ሲሆን እኩል ስፋትም አላቸው።

4ኛ, እየሩሳሌም ሰማያዊት፦ እየሩሳሌም ሰማያዊት ከላይ እንደ ተማርነው ለሳጥናኤል መኖሪያ የተፈጠረች ናት ነገር ግን በትእምቱ ምክኒያት ሊኖርባት አልቻለም።

ሳጥናኤል ከወደቀ በኋላ ለአዳም ተሰታው ነበር አዳምም በሳጥናኤል አሳሳችነት ኃጢያትን ሲሰራ ከእየሩሳሌም ሰማያዊት ወጥቷል ነገር ግን ጽድቅ የሰራ የሰው ልጅ በሙሉ በዳግም ምፅዓት ለዛልአለም ይወርሳታል። 12 የበር ደረጃዎች ሲኖሯት የ12ቱ ሐዋሪያት ስም ተጽፎባታል።

5ኛ, ኢዮር፦ ኢዮር ከሱስቱ ዓለመ መላእክት አንዷ ስትሄን ከላይ እንደ ተማርነው የኪሩብ የሱራፊ እና የሚካኤል ነገድ ይኖሩባታል።

6ኛ, ራማ፦ ራማ ልክ እንደ ኢዮር በሦስት ከተማ የተከፈለች ሲሆን የገብርኤል የሩፋኤል እና የሱርኤል ነገድ የኖሩበታል።

7ኛ, ኤረር፦ ኤረር ልክ እንደ ኢዮርና ራማ ሶስት ከተማ ሲኖሯት የሳድካኤል፣ የሰላታኤል እና አናንኤል ነገድ ይኖሩባታል።

8ኛ, ኮሬብ፦ ኮሬብ ምድርን ያጠረ የእሳት ዓለም ነው። ዙሪያውን በነፋስ ታጥሯል ከውቅያኖስ ቀጥሎ ይገኛል። ከምድር በታች ካለው እሳት ጋር በጠፈር ይገናኛል። በኮሬብ ስጋዊም ደማዊም ፍጥረት አይኖርም።

9ኛ, ከምድር በታች ሁኖ ውሀን የተሸከመ እሳት ነው። ይህ ዓለመ እሳት ስፋቱ ምድርን ያክላል ምድርን በውሀ ላይ አፅንቷታል ውሀን ደግሞ በእሳት ላይ አፅንቶታል። ይህ ውሀ የፀናበት እሳተ ዓለም እሳት ይባላል። ውሃን ብቻ ተሸክሞ ሊኖር የተፈጠረ ፍጥረት ነው። በዚህ አለመ እሳት ምንም አይነት ፍጥረት አይኖርም።


, ዓለማተ መሬት፦ አምስት ሲሆኑ በዝርዝር እንያቸው

1ኛ, ብሔር
ብጹአን፦ ብሔረ ብፁዓን ከብሔረ ሕያዋን ከፍ ብላ የምትገኝ ሲሆን በዝች ምድር ሰዎች ይኖራሉ ሰዎችም ያገባሉ ይጋባሉ ልጆችም ይወልዳሉ። ባልና ሚስት በግብር የሚተዋወቁት 3 ጊዜ ብቻ ነው የሚወልዱት ልጅም 3 ብቻ ነው ከ3 ከፍም ዝቅም አይልም የመጀመሪያው ወንድ ልጅ ለአገልግሎት ሁለቱ ሴቲቱና ወንዱ ዘር ለመተካት ይሆናሉ። በዝች ቦታ የሚኖሩ የተነጠቁት በነብዩ ኤርሚያስ ዘመን ነው ከሄዱት መካከል ማቴዎስ ወንጌላዊ እና ቅዱስ ዞሲማስ መጥቀስ ይቻላል።

2ኛ, ብሔረ ሕያዋን፦ ብሔረ ሕያዋን እስከ ምፅዓት ቀን ድረስ የማይሞቱ ሰዎችና እነሱን ሚጠብቁ መላእክት መኖሪያ ናት።

ብሔረ ሕያዋን እንደ ገዳም ናት በዚህ ሚኖሩ ሰዎች አያገቡም አይጋቡም አይወልድምም

በዚች ምድር ሳሉ አግብተው ኑረው ኋላ በመልካም ስራቸው የተነሳ ተነጥቀው ወደ ላይ በመውጣት ይኖሩባታል። ሄኖክ፣ ካላገቡ ኤሊያስ፣ ከ12ቱ ሐዋሪያት 11ዱ ሲሞቱ ዮሐንስ ብቻ ሳይሞት ተነጥቆ በብሔረ ሕያዋን ይኖራል።

3ኛ, ገነት፦ ገነት ከምንኖርባት ምድር በቀኝ ወይም በምስራቅ በኩል ትገኛለች የሲኦል ተቃራኒም ናት ከዚች ምድርም ትሻላለች ኃጢያት የለባትም መላእክት፣ የጻድቃን ነፍሳት፣ እጽዋት እና አእዋፋት ይኖራሉ። የጻድቃን ነፍሳት ከገነት እስከ ዳግም ምፅዓት ይቆያሉ ከዛ በኋለ ወደ መንግስተ ሰማያት/እየሩሳሌም ሰማያዊት ይሄዳሉ።

4ኛ, የምንኖርባት መሬት ወይም ምድር ናት እች ምድር ከሲኦል ትሻላለች ጻድቃንና የኃጥአን ሰው መላእክት እንሰሳትና አጋንትም ጭምር ይኖራሉ።

ምድር ሰማይ በተፈጠረበት ቀን እሁድ ስትፈጠር ለሰዎች ወደ ሲኦልና ገነት መሸጋገሪያ ናት መላእክትም ሰውንና ቤተ ክርስቲያንን ለመጠበቅ ከሰማያት ይወርዳሉ አንድ ሰው ለሊትና ቀን የሚጠብቁት ከናቱ ማህጸን ከተፈጠረ ጀምሮ ሁለት መላእክት ይመደቡለታል። አጋንንት ደግሞ ሰውን ኃጢያት እያሰሩት ይኖራሉ።

5ኛ, ሲኦል/በርባኖስ ወይም እንጦሮጦስ ይባላል። ሲኦል ከገነት በተቃራኒ ከምድር በግራ በምእራብ በኩል ትገኛለች።

በዝች ጽድቅ በማይነገርባት ቦታ እጽዋትም ሆነ ውሃ ባይኖርባትም የመሬት አካልነት አላት እሳት የሚነድባት ጨለማ ናት እሳት ሲነድ ጨለማ ሊገፈፍ ባሕርይው ቢሆንም በሲኦል ግን እንዲህ አይደለም።
~~~~

ቀጣይ ትምህርታችን
ዓለማተ ማይ
#ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላድቱ ድንግል -ወለመስቀሉ_ክቡር_ይቆየን!!

@mahiberekidusan


❸➐
1.2K viewsKingston Ethiopia, 13:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-15 20:56:40 የቅዳሜ ውዳሴ ማርያም አንድምታ
ሊቀ ጉባኤ ጌታሁን

#ለወዳጅዎ-ለተዋህዶ ልጆች_ሼር ያድርጉ!
@mahiberekidusan
@mahiberekidusan
@mahiberekidusan
816 viewsKingston Ethiopia, 17:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-15 20:44:12 የአርብ ውዳሴ ማርያም አንድምታ ትርጓሜ
#ሼር-በማድረግ ኦርቶዶክሳዊ ግዴታዎን ይወጡ።
@mahibetekidusan
@mahiberekidusan
@mahiberekidusan
799 viewsKingston Ethiopia, 17:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ