Get Mystery Box with random crypto!

ማኅበረ ቅዱሳን (Mahibere Kidusan)

የቴሌግራም ቻናል አርማ mahiberekidusan — ማኅበረ ቅዱሳን (Mahibere Kidusan)
የቴሌግራም ቻናል አርማ mahiberekidusan — ማኅበረ ቅዱሳን (Mahibere Kidusan)
የሰርጥ አድራሻ: @mahiberekidusan
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.86K
የሰርጥ መግለጫ

🌷ይህ ቻናል የተከፈተው ለመላው የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ክርስትና እምነት ተከታይ ሲሆን ዋና አላማውም ምዕመናን በንስሐ ህይወት ተመላልሰው የእግዚአብሔርን መንግሥት እንድወርሱ የሚያስችል ትምህርት መስጠት ነው፡፡
🌷💚የቅዱሳን ገድላት
🌷💛ስንክሳር
🌷♥ ቅዱሳን ስዕላት
መንፈሳዊ ትምህርቶችና ጽሑፎች
🎤 ስብከቶች ............ይቀርቡበታል፡፡🌎

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2022-06-02 21:29:01 ​​​​#የቀጠለ

የጌታችን ዕርገት ምሳሌ እና ትንቢት አለው፡፡ ምሳሌው እንደምን ነው ቢሉ የቅዱስ ዮናስ በዓሣ አንበሪ ሆድ ሦስት ቀን አድሮ በሦስተኛው ቀን መውጣቱ ለትንሣኤው ምሳሌ እንደሆነ ሁሉ እንዲሁ የቅዱስ ኤልያስ ዕርገትም ለጌታችን ዕርገት ምሳሌ ነው፡፡ ልዩነቱ ግን ቅዱስ ኤልያስ በመላእክት እርዳታ በፈቃደ እግዚአብሔር ያረገ ሲሆን ጌታችን ግን በፈቃዱ በራሱ ኃይል ዐርጓል፡፡

ትንቢቱም ቅዱስ ዳዊት ‹‹ ወደ ሰማይ ላረገው ለእግዚአብሔር ዘምሩ ›› መዝ 67(68)፡33 ብሎ የተናገረው ነው፡፡ በተጨማሪም ‹‹ወደ ላይ ዐረግህ ምርኮን ማረክህ ስጦታንም ለሰዎች ሰጠህ›› (መዝ 67፡18) የሚል እናገኛለን፡፡ በመጨረሻም የጌታችን ታላቁ የዕርገት መልእክት ‹‹ኃይልን እስክታገኙ በኢየሩሳሌም ጽኑ›› የሚለው ታላቅ መልእክት ነው፡፡

ጌታችን በኢሩሳሌም እንደተወለደ እንዳደገ እንዳስተማረ እንደተሰቀለ በቤተ ክርስቲያንም በቤተልሔም ሥጋው ደሙ የሚዘጋጅባት ቃሉ የሚነገርባት በቤተ መቅደስ ሥጋው የሚቆረስበት ደሙ የሚፈስባት ቦታ ናትና ኢየረሳሌም የቤተ ክርስቲያን ምሳሌ ናት፡፡ ስለሆነም ቅዱስን የእግዚአብሔር መንፈስ እንዲሁም ጸጋ ለማግኘት በቤተ ክርስቲያን መጽናት እንደሚገባ በአጭር ዐረፍተ ነገር ያስተማረው ታላቅ በዓል ነው፡፡

የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዕርገቱን ከትንሣኤው አከታትሎ ወዲያውኑ አላደረገም ፣ ምክንያቱም ፈጽመው ክፋትን የተመሉ አይሁድና በኋላም የሚነሣ የረከሱ መናፍቃን ዕርገቱ ምትሐት ናት ብለው እንዳያስቡ ነው፡፡ ጌታችንም በረቀቀ ጥበቡ የደቀ መዛሙርቱን ተሸብሮ የነበረ ልቡናቸውን እያጽናና መነሣቱንም እያስረዳቸው ከትንሣኤው በኋላ አርባ ቀን ኖረ፡፡

ይህ የዕርገት በዓል ከጌታችን ዓበይት (ታላላቅ) በዓላት መካከል አንዱና ዋነኛው ነው፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የጌታችንን የዕርገት በዓል ሁለት ጊዜ ታከብራለች፡፡ ይኸውም በመጀመሪያ ጌታችን ያረገበትን ጥንተ በዓሉን ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ የቀመር በዓል ነው፡፡

ዓመታዊ በዓላት ዓዋድያት (Movable Feasts) እና ዓዋድያት ያልሆኑ (Immovable Feasts) ተብለው በሁለት ሊከፈሉ ይችላሉ፡፡ ዓዋድያት (Movable Feasts) የሚባሉት በቅዱስ ዲሜጥሮስ ቀመር መሠረት መባጃ ሐመርን ተከትለው ወደፊት ወደኋላ በመመላለስ በየዓመቱ በተለያየ ቀንና ወር የሚውሉት ናቸው፡፡ እነዚህም እንደ ስቅለት፣ ሕመማት፣ ትንሣኤ፣ ደብረ ዘይት ፣ ሆሣዕና ፣ ዕርገትና ጰራቅሊጦስ የመሳሰሉት ናቸው፡፡

ዋድያት ያልሆኑ (Immovable Feasts) የሚባሉት ደግሞ ሁልጊዜም በወር ውስጥ በሚገኝ በታወቀ ቀን ብቻ በቋሚነት የሚውሉት ናቸው፡፡ እነዚህም እንደ ፅንሰት (ትስብእት) ፣ ልደት ፣ ጥምቀት ፣ ደብረ ታቦር ፣ ቃና ዘገሊላ ፣ ዘመን መለወጫ ፣ መስቀል ፣ 33ቱ የእመቤታችን በዓላት ፣ የመላእክት ፣ የሰማዕታትና የቅዱሳን በዓላት ናቸው፡፡

የጌታችን ዓበይትና ንዑሳት በዓላት፡- ለመጀመሪያ ጊዜ የጌታችንን በዓላት ማክበር የጀመሩት የከበሩ ሐዋርያት ናቸው፡፡ ሠለስቱ ምእት ደግሞ ከ325 ዓ.ም ጀምረው በዓላቱ በቀኖና በሕግ እንዲከበሩ አዘዋል፡፡ ለዚኽም በፍትሐ ነገሥቱ ላይ የተጻፈውን በማስረጃነት ማየት እንችላለን፡፡ ‹‹እግዚአብሔር የጠመመውን እያቀናላቸው፣ የጎደለውን እየሞላላቸው የጌታን በዓላት ማክበር እንዲገባ 318 ሊቃውንት በጉባኤ ኒቅያ በእግዚአብሔር አጋዥነት የጌታችንን በዓላት ያከብሩ ዘንድ፣ ተአምራቱን ይገልጹ ዘንድ፣ ምስጋናውንም ይናገሩ ዘንድ አዘዙ ተናገሩ›› እንዲል፡፡ (ፍትሐ ነገሥት ትርጓሜ፣ ገጽ 260)

የጌታችን ዓበይት በዓላት ዘጠኝ ናቸው፡፡ እነዚህም፡- ፅንሰት (ትስብእት)፣ ልደት፣ ጥምቀት፣ ደብረ ታቦር፣ ሆሣዕና፣ ስቅለት፣ ትንሣኤ፣ ዕርገትና ጰራቅሊጦስ ናቸው፡፡

የጌታችን ንዑሳት በዓላት የሚባሉትም ዘጠኝ ሲሆኑ እነርሱም ስብከት ፣ ብርሃን ፣ ኖላዊ ፣ በዓለ ጌና ፣ ግዝረት፣ ልደተ ስምዖን ፣ ቃና ዘገሊላ ፣ ደብረ ዘይትና መስቀል ናቸው፡፡ የጌታችን የከበረ የዕረገቱ ረድኤት በረከት ይደርብን!

በምሥራቅ በኩል ወደ ሰማየ ሰማያት ላረገ አምላካችን ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ምስጋና ይሁን ከቸር አባቱ ከአብ ሕይወት ከሆነ ከመንፈስ ቅዱስም ጋራ ለዘለዓለሙ አሜን!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር አሜን

ስንክሳር ዘወርሃ ግንቦት

#ሼር
@mahiberekidusan
@mahiberekidusan
@mahibetekidusan
810 viewsKingston Ethiopia, 18:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-02 21:26:23 #​​​​እንኳን- ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የዕርገት በዓል በሰላም አደረሰን!!!

‹‹በምሥራቅ በኩል ወደ ሰማየ ሰማያት ለወጣ ለእግዚአብሔር ዘምሩ፡፡›› መዝ 67(68)፡33፡፡

‹‹ አምላክ በእልልታ፣ እግዚአብሔር በመለከት ድምፅ ዐረገ፡፡ ዘምሩ፣ ለአምላካችን ዘምሩ ፤ ዘምሩ ፣ ለንጉሣችን ዘምሩ፡፡ እግዚአብሔር ለምድር ሁሉ ንጉሥ ነውና ፤ በማስተዋል ዘምሩ፡፡ እግዚአብሔር በአሕዛብ ላይ ነገሠ ፤ እግዚአብሔር በቅድስናው ዙፋን ይቀመጣል፡፡ ›› መዝ 47፡5-8፡፡

‹‹ ነሆም አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ እልክላችኋለሁ ፤ እናንተ ግን ከላይ ኃይል እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ከተማ ቆዩ፡፡ እስከ ቢታንያም አወጣቸው እጆቹንም አንሥቶ ባረካቸው፡፡ ሲባርካቸውም ከእነርሱ ተለየ ወደ ሰማይም ዐረገ፡፡ እነርሱም ሰገዱለትና በብዙ ደስታ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ፣ ዘወትርም እግዚአብሔርን እያመሰገኑና እየባረኩ በመቅደስ ኖሩ፡፡ ›› ሉቃ 23፡50-53፡፡

‹‹ #ዕርገት ›› የሚለው ቃል ዐረገ ከሚለው የግእዝ ግስ የወጣ ሲሆን ‹‹ ከፍ ከፍ አለ ፣ ወደ ሰማይ ወጣ ›› ማለት ነው፡፡ ለምሳሌ ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በአንቀጸ ብርሃን ላይ ‹‹ በስምሽ በመለመን በመማጸን የሰው ልጆችን ጸሎት ያሳርጋሉ ›› እንዲል፡፡ እንዲሁም በእሁድ ውዳሴ ማርያም ላይ ‹‹ራሱን የተወደደ መሥዋዕት አድርጎ ያሳረገ›› እንዳለ፡፡

በተጨማሪም በራእይ 8፡4 ላይ ‹‹የዕጣኑም ጢስ ከቅዱሳን ጸሎት ጋር በመልአኩ እጅ በእግዚአብሔር ፊት ወጣ›› በማለት ዐረገ የሚለውን ቃል በአማርኛ ‹‹ወጣ›› በማለት ይገልጸዋል፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዕለተ ዓርብ ሞቶ ድኅነትን ከፈፀመ በኋላ በሦስተኛው ቀን የሞትን መውጊያ ሰብሮ ተነሣ፡፡ ከዚህ በኋላ በሞቱ ቀቢጸ ተስፋ ይዟቸው የነበረውን ሐዋርያትና አርድዕትን በተደጋጋሚ ትንሣኤዉን በመግለጥ ያጽናናቸው ነበር፡፡ ጌታችን ከሞት ከተነሣ ከኋላ ለአሥራ ሁለቱ ሐዋርያት ኪዳንንና ትምሕርተ ሕቡዓትን በዝርዝር አስተምሯቸዋል፡፡

መድኃኔዓለም ክርስቶስ ሞትን ድል አድርጎ ከተነሣ ጀምሮ እስከ 40 ቀን ድረስ ሐዋርያትን ፣ አርድዕትን በጠቅላላው 120ውን ቤተሰብ ሲያጽናና ቆይቶ ለቅዱስ ጴጥሮስ የፕርትክና (ታላቅ አባት የመሆን) ሥልጣንን ከሰጠው በኋላ 120ውን ቤተሰብ ወደ ደብረ ዘይት ይዞአቸው ወጣ፡፡ በዚያም ሳሉ ‹‹ኃይልን እስክትለብሱ ድርስ በኢየሩሳሌም ጸንታችሁ ቆዩ›› የሚለውን ታላቁን የዕርገት መልእክት አስተላልፎ ከምድር ከፍ አለ፡፡

በመላእክት ምስጋና ‹‹በምስጋና ወደ ሰማይ ዐረገ›› እንዲል ወደ ሰማይ ዐረገ፡፡ ከዐይናቸዉም ተሰወረ፣ ሐዋርያትም ወደላይ አንጋጠው አንገታቸውን አቅንተው ይመለከቱ ነበር፡፡ ሐዋ 1፡2፡፡ በዚህ ጊዜ ሁለቱ ብርሃናውያን መላእክት እንዲህ ሲሉ ተናገሯቸው ‹‹የገሊላ ሰዎች ሆይ! ወደ ሰማይ እየተመለከታችሁ ለምን ቆማችኋል? ይህ ከእናንተ ወደ ሰማይ የወጣው ኢየሱስ ወደ ሰማይ ሲሄድ እንዳያችሁ እንዲሁ ይመጣል፡፡››

ይህ ታላቅ የተስፋ ቃል የመላእክት ንግግር ከቅዱስ ዳዊት ትንቢት ጋር የተዛመደ ሲሆን የጌታችን ምጽአት በምሥራቅ በኩል እንደሚፈጸም ያሳያል፡፡ ሁለቱ መላእክት በንግግራቸው በዚህ ሲሄድ እንዳያችሁት በግርማ ደግሞ በዚህ ይመጣል ብለው ነበር፡፡ ቅዱስ ዳዊት ‹‹በምሥራቅ በኩል ወደ ሰማየ ሰማያት ለወጣ ለእግዚአብሔር ዘምሩ ›› መዝ 67(68)፡33 በማለት ይናገራል፡፡ በመሆኑም ጌታችን ያረገው በምሥራቅ ነው ፤ ደግሞ ለፍርድ የሚመጣው በምሥራቅ ነው ማለት ነው፡፡

#ይቀጥላል
#ሼር
@mahiberekidusan
@mahiberekidusan
@mahiberekidusan
586 viewsKingston Ethiopia, 18:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-31 12:23:45 የመጀመሪያ ኮርስ -ነገረ ክርስትና
የቀጠለ.......
#በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ አሃዱ አምላክ ዘለዓለም ሥላሴ አሜን።


#ምዕራፍ-፫ የግቢ ጉባኤያት ቦታ በቤተ ክርስቲያን መዋቅር
የቤተ ክርስቲያን መዋቅር ማለት ከጠቅላይ ቤተክህነት እስከ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን በልዩ ልዩ አደረጃጀት ቤተ ክርስቲያን ልጆችን የምታስተምርበት የተዘረጋ መዋቅር ነው።
በዚህ መዋቅር አሰራር መሰረት የከፍተኛ ት/ት ተቋማት ማለትም ግቢ ጉባኤያት በዚህም መዋቅር ውስጥ አገልግሎትን ለማግኘት አስቸጋሪ ስለሆነ እነርሱን ተጠቃሚ ሊያደርግ ሚችል በመሆን በሰንበት ት/ት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ስር ማህበረ ቅዱሳን በሚል ሌላ መዋቅር ተሰርቶላቸው መንፈሳዊይ አገልግሎታቸውን ይፈፅማሉ።

ሲኖዶስ ማለት አጠቃላይ የሐገራቱ ሊቃነ ጳጳሳት በአመት ሁለት ጊዜ ተሰብስበው ለቤተክርስቲያን ለህዝቦች የሚያስፈልግ ሃይማኖታዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ጉዳዮችን በመወሰን ያስተላልፋሉ።

ማህበረ ቅዱሳን ማለት የቅዱሳን፣ የሰማዕታት፣ የፃድቃን፣ ስራቸው ገድላቸው የሚዘከርበት ስለሆነ ማህበረ ቅዱሳን ተብሏል። ስሙንም አቡነ ገብርኤል ሰጥተውታል።

#የማህበረ_ቅዱሳን_አመሰራረት
የማህበረ ቅዱሳን የአመሰራረት ታሪክ መነሻው በ1970ቹ መጨረሻ ነው። ዘመኑም እግዚአብሔር የለሽ ትውልድ የበዛበት ጊዜ ነበረ። ይህም ወቅት በተለይም በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሚገኙ ተማሪዎች ዘንድ ቃለ እግዚአብሔርን መስማትም ሆነ መናገር ፈፅሞ የተከለከለ ነበር። ወጣቱ በዚህ ሁኔታ ላይ በነበረበት ጊዜ እግዚአብሔር የሰራውን ስራ መለስ ብለን በአንክሮ ስንመለከት እፁብ ድንቅ ነው። በክህደት አስተሳሰብ በፍልስፍና ማኢበል ቤተ ክረስቲያን መርከቧ በተናወፀበት ጊዜ/በተፈተነችበት ጊዜ እግዚአብሔር ታላቅን ስራ አደረገ።
በብፁዕ አባታችን አቡነ ጎርጎሪዎስ ... የሽዋ አገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አማካኝነት "እናንተን እግዚአብሔር ወደ ቤቱ የጠራችሁ በዚህ መንገድ እንድታገለግሉ ነው።" በማለት የእግዚአብሔርን ድንቅ ስራ አስቀምጠውታል።
ማህበሩ፦ በ1984 ዓ.ም ግንቦት ወር በሰንበት ትምህርት ቤቶች መደራጃ መምሪያ ስር ሁኖ ተደራጅቶ ቢቆይም መሪና ተዋረድ የተሰራለትና የጀመረው በ1986 ዓ.ም ስብሰባውን አድርጎ አባላቱን መርጧል።
አሁን 450 የግቢ ጉባኤያት ብዛት ደርሰዋል።

#ማህበረ_ቅዱሳን_ያለው_አወቃቀር
-->ስራ አስፈፃሚ
-->ስራ አመራር/ዋና ማዕከል/አዲስ አበባ
-->ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት/ባህር ዳር
-->ማዕከል
-->ወረዳ ማዕከል እና ግቢ ጉባኤያት

#የማህበረ_ቅዱሳን_አላማ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን እምነትና ስራአት ተጠብቆ ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲተላለፍ ለማድረግ ይቻል ዘንድ ቅዱስ ሲኖድዎስ በሚያወጣው መመሪያ መሰረት የዘመኑን ትውልድ በሀይማኖት በምግባር ማፅናት።
የቤተ ክርስቲያን ተልዕኮ ማስፈፀም
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ የሚማሩ ኦርቶዶክሳዊያን ወጣቶችን በማህበሩ ስር ረደራጅቶ የቤተ ክርስቲያን ተተኪ ትውልድን መፍጠር
ሰንበት ትምህርት ቤቶችንና የተለያዩ ማህበራትን ማደራጀት

#የማህበሩ_ተግዳሮቶች፦ የገንዘብ እጥረት፣ የአባላት ዝለት/ስንፍና፣ የትሀድሶ መናፍቃን ዘመቻ፣ የአህዛብ እንቅስቃሴ፣ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚገኙ የገንዘብ ጥመኞች፣ የወቅቱ ፖለቲካ ተፅዕኖ።

#መደረግ_ያለባቸው_ነገሮች፦ ችግሮችን ለማለፍና ቤተክርስቲያንን ለማጠንከር
~>ስልታዊ እቅድ ነድፎ መንቀሳቀስ
~>ጠንካራ የስብከት አገልግሎቶችን ማስፋፋት
~>የአብነት ትምህርት ቤቶችን ማስፋፋት
~>ወደ ቤተክርስቲያን የማይመጡ ተማሪዋችን ችግር መፍትሔ መስጠት
~>የቤተ ክርስቲያንና የአስተዳደርን በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መጠበቅ
~~~~~~~~
ቀጣይ ትምህርታችን
መንፈሳዊ አገልግሎት
#ወስብሐት _ለእግዚአብሔር_ወለወላዲቱ_ድንግል_ወለመስቀሉ_ክቡር_ይቆየን!!
#ሼር
@mahiberekidusan
@mahiberekidusan
@mahiberekidusan
842 viewsKingston Ethiopia, 09:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-29 21:00:07 የመጀመሪያ ኮርስ -ነገረ ክርስትና
የቀጠለ......
#በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ_አሜን


#ግሎባላይዜሽን
ከሀገራዊ ተፅዕኖ የሚያሳስበው መንፈሳዊነትን ማዳከም ላይ ነው። በስልጣኔ ሰበብ መዝናናት፣ ሀጢያትን ማላመድ፣ ቸልተኝነት፣ እግዚአብሔርን የማይፈራ ትውልድ መፍጠር፣ የነውር ተግባራትን እንደስልጣኔ የሚመለከት ትውልድን መፍጠር፣ በእግዚአብሔር ቃል ሳይሆን በራስ መተማመን በራስ አስተሳሰብ ብቻ የሚመራ ትውልድ መፍጠሩ ለመንፈሳዊነት መዳከም ትልቁን ድርሻ ይወስዳል።
በግሎባላይዜሽን ላይ አብሮ የሚካተተው ትውልድ አጥርቶ ሊመለከተው ያልቻለው ነገር ቢኖር ዘመናዊነትን ከዘመናዊነት ጋር አለመለየት ሲሆን ይህም ገሎባላይዜሽን በይበልጥ ክርስትና ላይ ተፅዕኖ እንዲያሳድር አድርጎታል።
ለኦርቶዳክሳዊያን ክርስቲያኖች መዘመን ለጊዜ እሳቤ ሳይሆን ለማንነት ጥበቃ ነው። የዘመናዊ ሳይንስ ውጤት አጠቃቀም ከዚህ አላማ በሚስማማ መሆን ይገባዋል።
አንድ ኦርቶዶክሳውያን ዘመናዊነትን በዘመኑ መዋደድ ሳይሆን ዘመኑን መዋጀት ነው።
ይህም ሲባል፦
ሐዋሪያት በሰበሰቧት በአንዲት ቤተ ክርስቲያን የሚያምኑ እና እችን ቤተ ክርስቲያን የሚከተል ሰው በዚህ አለም ሲኖር (በማሰብ፣ በመናገር፣ በማድረግ) ሲመለሱበት የሚገባውን ደንበር ምልክት በማስመር ነው።

የመስመሩን ምልክት በተገቢው አኗኗር እንዲኖሩ ማድረግ ነው።

በምግባር በሀይማኖት እንዲኖሩ ማድረግ ስለሆነም ዘመናዊነት ማለት በጊዜ እሳቤ እየተመላለሱ ሀይማኖትን፣ ባህልን፣ ትውፊትን መለወጥ ማለት አይደለም። ይህስ ዘመናዊነት ሳይሆን ዘማዊነት ነው።
~~~~~~~~
ቀጣይ ትምህርታችን
ምዕራፍ-3 የግቢ ጉባኤያት ቦታ መዋቅር
#ወስብሀት_ለእግዚአብሔር_ወለወላዲቱ_ድንግል_ወለመስቀሉ_ክቡር_ይቆየን!!
#ሼር-በማድረግ ለምዕመናን ያዳርሱ
@mahiberekidusan
644 viewsKingston Ethiopia, 18:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-28 08:38:53 የመጀመሪያ ኮርስ -ነገረ ክርስትና
የቀጠለ........
#በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ_አሜን


#በቅድመ_ግቢ_ህይወት፦ ተማሪዎች ወደ ኮሌጅ ወደ ዩኒቨርሲቲ ከመግባታቸው በፊት የተለያየ ህይወት እንደሚኖራቸው አያጠራጥርም።
ለአብነት ያህልም በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ላይ ሲያገለግሉና ሲሳተፉ የነበሩ በካሀናት አሰልጣኝነት ስልጠና የወሰዱ፣ በሰርክ ጉባኤ ሲማሩ የነበሩ ነገር ግን የሰንበት ትምህርት ቤት አባል ያልሆኑ ሌሎች ደግሞ ለበአለ ጥምቀት፣ ለቀብር ከመሆድአቸው በቀር ወደ ቤተክርስቲያን ቀርበው ማያውቁ አሉ። ሀይማኖታቸውን ቢጠይቃቸውም ያማያብራሩ አሉ።

#በብሔር፦ ሀገራችን የብዙ ብዙ ብሔረሰቦች መኖሪያ መሆኗ ገቢዎችንም በዚህ ስብጥር እንዲያሸበርቁ አድርጓቸዋል። ተማሪዎች በአንድ ግቢ ውስጥ ሁነው ከነሱ ውጭ ስለሆኑ ብሔረሰቦች የማወቅ እድል ብቻ ሳይሆን የመተዋወቅና በአንድነት በፍቅር የመኖር እድል ማግኘታቸው የኑሮአቸውን ውበት ያደምቀዋል። (ዮሐ 15፥1-5 እኔ የወይን ግንድ ነኝ እናንተም ቅርንጫፎች ናችሁ)

#በባህል፦ ከላይ የተለያየ ብሔር እንዳሉ ተመልክተናል እያንዳንዱ ብሔረሰብ ደግሞ የራሱ የሆነ ነገር ሊኖረው እንደሚችል የታመነ ነው። ኢትዮጵያ የክርስቲያን ደሴት በመሆኗ እና ባህሏ ከቅዱሳን መፅሐፍትና ከቅዱሳን ኑሮ የተቀዳ ቢሆንም ከአካባቢ አካባቢ፣ ከብሔረሰብ ብሔረሰብ የሚለያይ ነገር አይጠፋም።
ይሁን እንጂ አንድ ተማሪ ከብሔረሰቡ እና ከአካባቢው ያመጣውን ባህል ግቢ ውስጥ እንደፈጠረው ስናስብ እንሳሳታለን።
ይህ የባሀል ስብጥር ጎጅ የሚሆንበትን በሁለት መንገድ ከፍለን እናየዋለን፦

ሀ/ #የኔ_ባህል_ከሌላው_ይበልጣል ብለን መሰብ የሌላውን መናቅና መጥላት ስንጀምር

ለ/ #በባህላችን ታርቀን ለክርስትና ህይወት እንዳንታዘዝ ስናማፅ እና ከፅድቅ ህይወት ስንከለከል ነው።
ከእነዚህ ሁለት ወጥመዶች ካመለጥን የህብረተሰብና የባህል ስብጥር በአንድ የአትክልት ቦታ እንደሚጎበኙ አንድነት እንዳላቸው አበቦች የሚያስጌጠን፣ የሚያስውበን አምላካዊ ስጦታ መንፈሳዊ አንድነት ነው። (መክ 12፥1 የጭንቀት ቀን ሳይመጣ በጕብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስብ...)

#በጠባይ፦ ሰው በመልክ።፣ በቁመት፣ በገፅ እንደሚለያይ በጠባይም ይለያያል። ከባህሪው ስንል ከአራቱ ባህርያተ ስጋ እና ከሶስቱ ባህርያተ ነብስ ነው በእነዚህም እድሚያቸው የተለያየ ፀባይ ይኖራቸዋል። ይህ የፀባይ ስብጥር መኖሩ አይቀሬ ነው።

#በእውቀት፦ ይህ ደግሞ ሰው በቁመቱ እነደሚበላለጥ ሁሉ በእውቀቱ በሚያደርገው ጥረት እንዲሁም ሊያውቀው በሚፈልገው ት/ት ይለያያል። ከዚህም የተነሳ ለያንዳንዱ ትምህርትም የተለያየ የሆነ አስተሳሰብ ይፈጥርበታል። መምህሩ የትምህርት ጓደኞቹም እንዲሁ ይህ ስብጥርም ከፍላጎትና ከፀጋ ልዩነት መሆኑን ካልተገነዘብን መናናቅም መጣላትም ስለሚፈጥር በእውቀት በሚማሩት ትምህርት አይነት መሰባጠሩን ጥቅም በውል መረዳት እና መገንዘብ ያስፈልጋል።

#በገንዘብ_አቅም፦ አገራችን ውስጥ ያሉት ባለፀጎች ከሌሎች አገራት ባለፀጎች ጋር የሚወዳደሩ ሊሆኑ ይችላሉ።
ይሁን እንጅ በአገራችን እይታ ባለ ፀጎች አሉ፣ ድሆዎችም አሉ፣ መካከለኛ ኑዋሪዎችም አሉ። እኛ ተማሪዎችም የነዚህ ሰዎች ልጆች ነነ። በመሆኑም የተለያየ አኗኗር ለምደው የመጡ መሆናቸው የታወቀ ነው። ወላጆችም የቀደመ አኗኗራቸውን በመገንዘብ የሚያደርጉት ክትትል ይለያያል። የደብተርና የብዕር/የስክርቢቶ መግዣ የለለውና በግሉ መመገብ እሰከ ሚችል ድረስ አቅም ያላቸው ተማሪዎች አሉ። ይህንም ስብጥር ከተጠቀሙበት ልዩ ጥቅም አለው።

ሀ/ ከሌላው ጋር በፍቅር መኖር የጎደለውን በመሙላት የሚረዳዱበትና ከተዋወቁበት ጊዜ አንስቶ አንዱ ከሌላው እውነተኛ ወንድምነት የሚመሰርቱበት በመሆኑ ነው።

ለ/ ሰው እንደ ጎረቤቱ ሳይሆን እንደ ቤቱ መኖር እንደሚችል ትልቅ ልምድና ልበ ሙሉነት የሚያዳብርበት ጊዜ ነው። (በቃኝ ከማለት ጋር እግዚአብሔርን ማምለክ ታላቅ ክብር ነው)። ወደ አለም የመጣሁት ነገር የለም የምወስደውም ነገር የለም 1ኛ ጢሞ 6፥6-8
''ሀይልን በሚሰጠኝ በክርስቶስ ሁሉን እችላለሁ ፊል 4፥11"

#በቦታ፦ ግቢ ውስጥ አዲሱ ስብጥራችን ከለመድነው በተለየ ሁኔታ የቦታ ስብጥር አለ።
በግቢ ውስጥ የቤተ መፅሐፍት፣ የኳስ ሜዳ ለሌሎችም የተለያየ ቦታዎች በህይወታችን ላይ ድርሻ አላቸው።
የቤተ መፅሐፍትን ፀጥታ የለመደና የኳስ ሜዳ የድጋፍ ጭሆትን የለመደ ሰው አንድ ቦታ ማውራት ይቸገራሉ። እንደ መዝናኛ ቦታ ደግሞ ዳማ፣ የጠረፔዛ ቴንስ፣ ፑል የሚያዘወትር ሰው አለ በሌሎችም ቦታዎች እንዲሁ ሌላው ደግሞ በእነዚህ የመሳሰሉ ጎጅ ቦታዎችና ሁኔታዎች መጠበቅ ይገባል። "ወንድሞቻችን ሆይ እውነትን ሁሉ፣ ቅንነትን ሁሉ፣ ፅድቅንም ሁሉ፣ ንፁህነትንም ሁሉ፣ ፍቅርንም ሁሉ፣ በጎነትይም ሁሉ ምስጋናንም ቢሆን አነዚህን ሁሉ አስቡ (ፊል 4፥8-9)
የግቢ ጉባኤ አባላት ባልሆነው ነገር መልካም ወሬ በለለበት ቦታ ከመገኘት መጠበቅ ይኖርባችኋል ሲል ነው።


ቀጣይ ትምህርታችን
#ግሎባላይዜሽን
#ወስብሀት_ለእግዚአብሔር_ወለወላዲቱ_ድንግል_ወለመስቀሉ_ክቡር_ይቆየን!!
#ሼር-በማድረግ ቃሉን ለምዕመናን ያዳርሱ
@mahiberekidusan
684 viewsKingston Ethiopia, 05:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-25 09:27:18 የመጀመሪያ ኮርስ -ነገረ ክርስትና

የቀጠለ........
#በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ_አሜን

_________
#አዲስ_ነገር_በከፍተኛ_ተቋም_ውስጥ
አንድ ተማሪ ወደ ግቢ ሲገባ ብዙ አዲስ ነገሮች ይገጥሙታል። እነዚህንም እንደሚከተለው እንመለከታለን፦

ጓደኝነት፦ አንድ ሰው ወደ ሌላ አካባቢ በሚሄድበት ጊዜ የማያውቃቸው አዳዲስ ሰዎች ወደ ህይወቱ ይመጣሉ።
አንዳንድ ጊዜ ሰዎችን ወደህይወታችን ስናመጣ ጥንቃቄ ልናደርግ ይገባል። ስለዚህ አዲሱ ጓደኝነት እንደ ጓደኝነት ከመመስረታችን በፊት መደረግ ያለባቸውን ጥንቃቄዎች መርሳት አይገባም።
ከነዚህም መካከል፦
ሀ/ በይሉንታ ላለመጠመድ መዘጋጀት ያስፈልጋል።
ለ/ ከዘረኝነት መንፈስ መውጣት።
ሐ/ ለሥጋዊ ጥቅማቸው የሚፈልጉን ሰዋች እንደሆኑና እንዳልሆኑ ማረጋገጥ።
ጓደኝነት ማለት ጠቅላላ አድርገን ስንተረጉመው ጓደኝነት ማለት ነው። ይህም ማለት ምስጢርን አዋቂ እንዲሁም ምስጢርን ጠባቂ ነው። በደስታ ብቻ ሳይሆን በችግርም መከራ ጊዜ መሸሸጊያ የሚሆን ነው።

ሀላፊነት፦ ሐላፊነት ማለት ስለ አንድ ነገር ባለቤት ሁኖ ለጉዳዩ ተጠያቂ መሆን ማለት ነው። ስለሆነም ተማሪዎች ወደ ግቢ ሲገቡ እራስን የመምራትና ሀላፊነት የመውሰድ ግዴታ አለባቸው።
ነፃነት ያለ ሐላፊነት ፍፃሜዋ አያምርም / ነፃነት ያለ ባርነት መኖር ማለት ነው። ይኸውም በሌሎች ክፉ አስተሳሰብ እና ምክር ሳይገደዱ መኖር ነው። ስለሆነም እንደ ቤተ ክርስቲያንና አስተምህሮ በሐላፊነት እራስን መምራት ይገባል።

የቤተሰብ_ናፍቆት፦ አንድ ሰው ከቤተሰቡ እንደተለየ ቤተሰቡና አካባቢው ይናፍቀዋል። እንኳን ሰው ይቅርና እንሰሳትም ከመንጋ ሲለዩ ይነፋፈቃሉ። ናፍቆት እንደ ሰዋዊ ባህሪይ በሁሉም ላይ ያለ ነው። (የሐዋርያት ስራ 15፥38) ስለዚህ አንድ ሰው በየትም አካባቢ ቢጓዝ እራሱን እንደ ቤተ ክርስቲያን አካል አድርጎ/ቆጥሮ ሊያይ ይገባል።
ይህንን የሚረሳ ከሆነ ግን የቤተሰብ ናፍቆት በትምህርቱ ላይ ተፅዕኖ ያሳድርበታል።

#ስብጥር
በትምህርት ቤት ውስጥ የተማሪዎች እድሜ ተቀራራቢ ቢሆንም በተማሪዎች መካከል ግን ስብጥር አለ። ተማሪዎችን የሚጎዳው ስብጥር መኖሩ ሳይሆን ስብጥሩን አለማገናዘቡ ነው። ይሄንም እንደሚከተለው እናያለን፦
1/ በቅድመ ግቢ ህይወት
2/ በብሔር
3/ በባህል
4/ በፀባይ /በጠባይ
5/ በእውቀት
6/ በገንዘብ አቅም
7/ በቦታ


ቀጣይ ትምህርታችን
1/ በቅድመ_ግቢ_ህይወት
#ወስብሀት_ለእግዚአብሔር_ወለወላዲቱ_ድንግል_ወለመስቀሉ_ክቡር_ይቆየን!!
#ሼር-ያድርጉ
@mahiberekidusan
840 viewsKingston Ethiopia, 06:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-21 15:45:15 የመጀመሪያ ኮርስ -ነገረ ክርስትና

የቀጠለ.......
#በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ_አሜን



#የሐይማኖትእና_የሳይንስ_ልዮነት
1,#መነሻቸው፦ የሐይማኖት መነሻ እግዚአብሔር ነው። ሰው ተቀባይ ሲሆን እግዚአብሔር ደግሞ ሰጭ ነው (የዮሐ መልዕክት 1፥3 ፤ የዮሐ ወንጌል 17፥8)
~>የሳይንስ መነሻው/ምንጩ የሰው ልጅ ነው

2,#ከአለም_አንፃር፦ የሐይማኖት አላማው/ግቡ ሰውን ከእግዚአብሔር ጋር ማገናኘት ነው
~>የሳይንስ አላማው የሰውን ኑሮ ማሻሻል ነው

3,#ከትኩረት_አቅጣጫ_አንፃር፦ የሐይማኖት ትኩረቱ ስለ አድራጊው፣ ስለ አስገኝው፣ ስለ ፈጣሪው ነው
~>የሳይንስ ትኩረቱ ስለ ተደራጊው፣ ስለ ተፈጥሮው ነው

4,#ከተጠቃሽነት_አንፃር፦ ሐይማኖት የሚጠቅሰው የሚጠቅሰው የእግዚአብሔርን ቃል ነው
ሳይንስ ደግሞ የሚጠቅሰው የቀደሙትን ምርምር ነው።

#ሐይማኖትእናፍልስፍና
#ፍልስፍና ማለት በሰዋሰዋዊ ትርጓሜ ጥበብ፣ እውቀት፣ ምርምር ማለት ነው

#ፈላስፋ ማለት የጥበብ፣ የእውቀት፣ የምርምር ሰው ማለት ነው
ፍልስፍናን/አለማዊ እውቀትን በአግባቡ ካልተጠቀሙበት ከፍተኛ ጉዳት ያስከትላል።
#እነዚህም፦ 1, በስጋዊ መራቀቅን እንጅ መንፈሳዊነትን አያሳድግም።
2, በስጋዊ እውቀትና ጥበብ ብቻ እንዲመኩ ያደርጋል።
3, የሰዋችን ህይወት ዘላለማዊነት ወደ ጊዜያዊነት ዝቅ ያደርጋል።
4, ወደ ክህደት ትምህርት ይወስዳል (ግኖስቲክ)
➭➭➭➭➭➭➭➭➭➭➭➮➮➭➮➮➮

ቀጣይ ትምህርታችን #አዲስ_ነገር_በከፍተኛ_ተቋም_ውስጥ

#ወስብሀት_ለእግዚአብሔር_ወለወላዲቱ_ድንግል_ወለመስቀሉ_ክቡር_ይቆየን!!
#ሼር-ያድርጉ
@mahiberekidusan
780 viewsKingston Ethiopia, 12:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 19:33:57 የመጀመሪያ ኮርስ -ነገረ ክርስትና


#በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ_አሜን)።


#መንፈሳዊነትእናእውቀት
~>እውቀት ማለት አንድን ነገር መረዳት መገንዘብ ማለት ነው።

እንደ ቅድስት ቤተክርስቲያን አስተምህሮ መሠረት 3 አይነት የእውቀት ደረጃዎች አሉ ።
#እነሱም፦ 1,#አለማዊ_እውቀት
2,#መንፈሳዊ_እውቀት (ስርዓተ አብ)
3,#እርኩስ_እውቀት (በጥንቆላ)

እውቀት ከማስተዋልጋር ሊውል ይገባል ማስተዋል ከጥበብ ጋር ሊውል ይገባል።
አቤቱ ማስተዋልና ጥበብን ስጠን (ጠቢቡ ሰለሞን)

#ጥበብ ማለት እግዚአብሔር ነው (ቅዱስ እስጢፋኖስ)
~>የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፋራት ነው (ጠቢቡ ሰለሞን)
~>እግዛብሔርን መፍራት ጥበብ ነው (ፃድቁ እዮብ)
~>የጥበብ መጨረሻው እግዚአብሔርን መፍራት ነው (መጽሐፈ መለኮት)
~>እውቀትን የለመንፈሳዊነት ገንዘብ ማድረግ ፍፃሜው በጎ ምላሽ አይሆንም። (ፍፃሜው አያምርም)

~>እውቀት ብርሀን ነው። ብርሀንም ለማየት ይጠቀሙበታል ለመታየት አይጠቀሙበትም። እውቀትን እንዲሁ ለማየት እንጅ ለመታየት አግባብ አይደለም።

#መንፈሳዊነትእናምርምር
~>የመንፈሳዊነት መሠረት እንዲሁም የምግባር እና የትሩፋት መሰረታቸው ሐይማኖት ነው።

~ ሐይማኖት በተፈጣሪ እና በፈጣሪ መካከል ያለ ግንኙነት ነው።

#ሳይንስ ማለት ከላቲን ቃል የተገኘ ሲሆን ትርጓሜውም በልምድ የተገኘ እውቀት ማለት ነው።
➥➥➥➥➥➥➥➥➥➥➥➥➥➥➥➥➥➥➥➥➥➥
ቀጣይ ትምህርታችን #የሐይማኖትእናየሳይንስ_ልዩነት

#ወስብሀት_ለእግዚአብሔር_ወለወላዲቱ_ድንግል_ወለመስቀሉ_ክቡር_ይቆየን!!
#ሼር- ያድርጉ
@mahiberekidusan
697 viewsKingston Ethiopia, 16:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-19 09:45:43 የመጀመሪያ ኮርስ -ነገረ ክርስትና

የቀጠለ.......
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን።
ክርስቶስ ተንስአ እሙታን
በዓቢይ ኃይል ወስልጣን
አሰሮ ለሰይጣን
አጋዞ ለአዳም
ሰላም
እምይእዜሰ
ኮነ
ፍስሐ ወሰላም።
ከባለፈው የቀጠለ ኮርስ ነው ። እንድትከታተሉ በትህትና እንጋብዛለን ።
_____
#ምዕራፍ-፪ መንፈሳዊ ህይወት በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት

#መንፈሳዊ_ህይወት
#መንፈሳዊነት ማለት ከመንፈስና ከውሀ ተወልዶ በልጅነት ያገኛትን ፀጋ እያሳደጉ የተቀበሉትን ስመ ክርስትና በመግባር መግለፅ ማለት ነው። ገላ 5፥1

#መንፈስ የማይጨበጥ፣ የማይዳሰስ ረቂቅ ነገር ነው
#መንፈሳዊ ማለት ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ በማህፀነ ዮርዳኖስ ሲወለድ ነው
~>አንድ ሰው መንፈሳዊ ለመባል 3 መሰረታዊ ነጥቦችን ሊያሟላ ይገባል
1,#መታመን 2,#ተስፋ 3,#ፍቅር

መንፈሳዊያን እና መንፈሳያን ያላቸው ልዩነት
#መንፈሳዊነት #መንፈሳያን
~>ይነበባሉ ~>ይታያሉ
~>ይቀመሳሉ ~>ይላሳሉ
~>ይደመጣሉ ~>ይለፈልፋሉ
~>ያስተውላሉ ~>ይቸኩላሉ
~>ይጠግባሉ ~>ይቁለጨለጫሉ
~>ይመዘናሉ ~>ይፈሳሉ
~>ያርማሉ ~>ይተቻሉ
~>ጠላቶቻቸውን ~>ወዳጆቻቸውን
ወዳጃቸው ጠላቶቻቸው
ለማድረግ ለማድረግ
አንድ ሺ እድል አንድ ሺ እድል
ይሰጣሉ ይከፍታሉ
~>ይኖራሉ ~>ያኗኑራሉ
~>ይሰጣሉ ~> ያሳያሉ
~>ከመፍረድ በፊት ~>ከፈረዱ በኋላ
ይመክራሉ ይመክራሉ

➥በአጠቃላይ መንፈሳዊነት ማለት በክርስቶስ ክርስቲያን በወልድ መወለድን በመንፈስ ቅዱስ መንፈሳዊያን የሆነ ነው

#የመንፈሳዊያን_መገለጫ
አንዱ እና ዋነኛው መልካም ምግባር ነው
#ለምሳሌ፦ባልንጀራህን እንደራስህ መውደድ ትህትና፣ ትግስት፣ መቻቻል፣ ፅኑ ተጋድሎና የመሳሰሉት ናቸው።
~~~~
#ወስብሀት_ለእግዚአብሔር_ወለወላዲቱ_ድንግል_ወለመስቀሉ_ክቡር_ይቆየን

ቀጣይ ትምህርታችን #መንፈሳዊነትናእናእውቀት
#ሼር-ያድርጉ
@mahiberekidusan
729 viewsKingston Ethiopia, 06:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-01 18:45:23 ዳግማይትንሳኤ ማለት ዳግም መነሳት (ሁለተኛ መነሳት)

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ በተነሳ በስምንተኛው ቀን በዕለተ እሁድ ደቀ መዛረሙርቱ አይሁድን ፈርተው በተሰበሰቡበት ዝግ ቤቶ "ሰላም ለእናንተ ይሁን "ብሎ ዳግም ስለ ተገለጠ #ዳግማይ\ትንሳኤ ተብሏል ።
ሁለተኛለምንተገለጠ?

ለሐዋርያው ቶማስ ትንሳኤውን ለማሳመን

የጌታችን ትንሳኤ ቶማስ ስለ ተጠራጠረ ጌታችን ቶማስ በተገኘበት ዝግ ቤት ተገልጦ ለቶማስ ና ወደኔ የተቸነከረውን እጄና ጉኔን ዳስስ ብሎታል

ቶማስም የተቸነከረው እጁን አይቶ የተወጋውን ጉኑ በእጁ ዳስሶ የጌታችን ትንሳኤ አምኗል ።ሃገረ ስብከቱም በሕንድ ስለ ነበረ ተጋድሎውም የፈጸመው እንዲሁም ሰማዕትነት የተቀበለው በሕንድ ነው ።ያቺ የጌታችንን ጎን የነካች (የዳሰሰች)እጅ ሳትበሰብስ ከታቦት ጋር በመንበሩ ላይ ተቀምጣለች ።እስካሁን ድረስ የሕንድ ሊቀ ጳጳስ ሲሾም በዛች እጅ ተመርጦና ተባርኮ እንደሚሾም አንዳንድ ሊቃውንት ይናገራሉ

ሰንበትን ሊያጸናልን

የአይሁድ ሰንበት፣እግዚአብሔር 22 ፍጥረታትን ፈጥሮ ያረፈባትና እረፉባት ብሎ ያዘዘን ሰንበት ቀዳም(ቅዳሜ)ናት ።በሐዲስ ኪዳንም ጌታችን የተጸነሰባት ፣ከሙታን መካከል የተነሳባት፣አንዲሁም ደግሞ ለማጽናት ሁለተኛ የተገለጠባት(ዳግማይ ትንሳኤ)፣መንፈስ ቅዱስ የወረደባትና ሐዋርያት ከመጀመርያዋቹ ክርስቲያኖች ጋር በኅብረት ሆነው መንፈሳዊ ስራዋች የሚሰሩባት ቀን ዕለተ እሁድ ነበረች ።ቤተ ክርስቲያናችን ለቅዳሜ ቀዳሚት ሰንበት ለእሁድ ደግሞ ሰንበተ ክርስቲያን እያለች ለሁለቱም ቀናት እኩል ታከብራቸዋለች ።ጌታችንም ይቺ ቀን እረፍትነቷን ለማጽናት ሁለተኛ የተገለጠባት ቀን ናት ።እረፍት ስንልም ስራችንን ትተን ቁጭ ብለን (ተኝተን)የምናሳልፈው ማለት አይደለም ።እንደውም ከማንም ቀን በላይ አብዝተን መንፈሳዊ ስራዎች የምንሰራባቸው ቀናት ናቸው እንጂ

ምትሐት አለመሆኑ ለማስረዳት

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ምትሐት እንዳልሆነና ቀድሞ የተዋሃደው ስጋና መለኮት ፣ፍጹም ሰው ፍጹም አምላክ መሆኑ ለማስረዳት ለሁለተኛ ጊዜ ተገልጦላቸዋል ።በዝግ ቤት መግባቱ ደግሞ መለኮት እንዳልተለየውና ስጋ ብቻው እንዳልሆነ ለማስረዳት ነው ።
"ብጹዓን እለ እንዘ ኢይሬእዩ የአምኑ"
(ዮሐ20:29)

የተሣተውን ፤ የተረሳው፤ የተገደፈውን፤ የነጠፈውን በቀና መንፈስ አቃንታቹ አንብቡት
ስለ ማይነገር ስጦታው እግዚአብሔር ይመስገን

@mahiberekidusan
@mahiberekidusan
@mahiberekidusan
1.0K viewsKingston Ethiopia, 15:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ