Get Mystery Box with random crypto!

LEYU NEWS

የቴሌግራም ቻናል አርማ leyu_news — LEYU NEWS L
የቴሌግራም ቻናል አርማ leyu_news — LEYU NEWS
የሰርጥ አድራሻ: @leyu_news
ምድቦች: ቴሌግራም
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 527
የሰርጥ መግለጫ

#ልዩ_መረጃ  |  #ቀዳሚ_ምርጫዎ
➠ ፈጣን እና ተዐማኒ መረጃ
➠ወቅታዊ መረጃዎች
➠ልዩ ልዩ ዘገባዎች
➠ የስፓርት እና መዝናኛ ዜናዎች
➠ጠቃሚ ጥቆማዎች ይደርሶታል።
አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን።
         PROMOTION
➥   
🎬  "ተመራጭ የዜና ምንጭ"
News & Media Channel®

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 34

2023-03-28 20:40:50 አስቸኳይ የፓስፖርት አገልግሎት ለጊዜው መቋረጡ ተገለጸ
በኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና መሥሪያ ቤት እንዲሁም በ11ዱ የክልል ቅርንጫፍ ፅኅፈት ቤቶች ሲሰጥ የነበረው “አስቸኳይ” የፓስፖርት አገልግሎት ለጊዜው መቋረጡ ተገለጸ፡፡

አገልግሎቱ የተቋረጠው ከአቅም በላይ የባለ ጉዳይ ፍሰት ከመፈጠሩ ጋር ተያይዞ መጠነ ሰፊ የሠነድ ማጭበርበሮች በመስተዋላቸው መሆኑን ነው የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ያስታወቀው፡፡

በተጨማሪም ተገልጋዮች ሊገለገሉ ሌሊት በሚመጡበት ወቅት በተለያዩ ኅገ-ወጥ ግለሰቦች የሚደርስባቸው እንግልትና ጉዳት በአገልግሎት አሰጣጥ እና በተገልጋዩ ላይ ተግዳሮት በመፍጠሩ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡

ስለሆነም የማስተናገድ አቅምና ሌሎች ክፍተቶች እስከሚስተካከሉ ድረስ ይሰጥ የነበረው የ“አስቸኳይ”ፓስፖርት አገልግሎት ለጊዜው መቋረጡ ተገልጿል፡፡

ቀድሞ ይሰራበት በነበረው አሰራር መሰረት አስቸኳይ ጉዞ ያላቸው አገልግሎት ጠያቂዎች ማስረጃዎቻቸውን አቅርበው በዋና መስሪያ ቤቱ ብቻ ከመጋቢት 20 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ የሚስተናገዱ መሆኑ ተጠቅሷል፡፡

ተገልጋዮች ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ  ከኅገ ወጥ ደላሎች እንዲጠነቀቁም ነው አገልግሎቱ ያሳሰበው፡፡

የመደበኛ ፓስፖርት ተገልጋዮች ቀድሞ በነበረው ሒደት መስተናገድ እንደሚቀጥሉም የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት መረጃ ያመላክታል።

@Leyu_News
@Leyu_News
1.6K views17:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-28 19:14:04 ጀግኖችን አለማክበር ሌሎች ጀግኖች እንዳይወጡ እንቅፋት ነውና አፈናው ይቁም!

በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከእናት ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ

በየትኛውም መመዘኛ ሰብዓዊ መብቶች ለድርድር የማይቀርቡ ተፈጥሯዊ መብቶች መሆናቸው በዓለም አቀፍ ሕግጋት የተደነገገ ሲሆን በሀገራችን ሕገ መንግሥት ውስጥም ተካቶ ይገኛል፡፡ ይኹን እንጂ በሀገራችን የሰብዓዊ መብት ጥሰት በተለይ ላለፋት ሃምሳ ዓመታት ከጊዜ ወደ ጊዜ በከፋ ኹኔታ እየተፈጸመ የሚገኝ ሲሆን ከዚሁ እኩይ ልማድ መላቀቅ ባለመቻሏ በህመም የሚሰቃዩ ዜጎችን ሕክምና እስከመከልከል የደረሰ ዜጎቿን በጭካኔ አለንጋ የምትገርፍ ሀገር ሆናለች።

በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የተቀሰቀሰውን ጦርነት ተከትሎ ሀገር የሕልውና አደጋ ውስጥ በገባችበት ወቅት መንግሥት ያቀረበላቸውን ጥሪ ተቀብለው በሙያቸው ለማገልገል የሕይወት ዋጋ ሊያስከፍል የሚችለውን ተልእኮ ተቀብለው ዋጋ ከከፈሉ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች አንዱ የሆኑት ብርጋዴር ጄኔራል ተፈራ ማሞ በከፍተኛ ሕመም እየተሰቃዩ መሆኑን ከቤተሰባቸው ጭምር መረጃ አግኝተናል፡፡ ሕክምና ካላገኙ ሕይወታቸው ጭምር አደጋ ላይ ሊወድቅ እንደሚችል መገንዘብም ችለናል። ጀኔራሉ ሕመማቸው በጦርነቱ ወቅት በጥይት በመመታታቸው ከደረሰ ተደጋጋሚ ጉዳትና ለሀገር ቅድሚያ በመስጠት በውል ሊታከሙት ካለመቻላቸው ጋር የተያያዘ መሆኑንና በሀኪሞች ቦርድ ምክርና ምሥክር መሠረት የግዴታ የውጭ ሕክምና ማድረግ እንዳለባቸው ቢረዱም መታከም እንዳይችሉ በመንግሥት መከልከላቸውን ገልጸዋል።

እኒህና መሰል ለሀገር መጽናት በሕይወታቸው ተወራርደው ዋጋ የከፈሉ የሀገር ባለውለታ ጀግኖችን  በሚገባቸው ልክ ክብር መስጠት ባይቻል እንኳን በደረሰባቸው ጉዳት ከሚያሰቃያቸው ሕመም ለማገገም በራሳቸው ወጪ ሕክምና እንዳያገኙ መከልከል ሀገር ተቆርቋሪ እንድታጣ የሚያደርግ፣ “ነግ በኔ” የሚያስብል፣ ጀግኖች በከፈሉት ዋጋ እንዲኮሩ ሳይሆን እንዲያፍሩበትና “ምን ባጠፋ ነው?” እያሉ እንዲሸማቀቁ የሚያደርግ ስሑት አካሄድ ነውና በጊዜ ሊታረም ይገባል።

በሌላ በኩል ለሀገር ሊከፈል የሚገባ የመጨረሻ የሆነውን የሕይወት መስዋዕትነት ለከፈሉና እየከፈሉ ላሉ የሀገር ባለውለታዎችና ቤተሰቦቻቸው የሚገባቸውን ያህል ክብር ባይቸራቸው ቢያንስ ግን ዋጋ በከፈሉላት ሀገር በሕይወት የመኖርን ያህል መንግሥት ሊያከብረውና ሊያስከብረው የሚገባ ሰብዓዊ መብት ሊነፈጉ አይገባም። ጀግኖቻችንን በገፋን ቁጥር ኢትዮጵያችን ጀግኖቿን እያጣች መጭውም ትውልድ አርዓያ ሰቡን እያጣ ጠላትን ከወራሪ የሚመክት ተቆርቋሪ ትውልድ ማፍራት እንዴት ይቻላል?!

ስለሆነም መንግሥት ከዚህ ድርጊቱ ተቆጥቦ ብ/ጄ ተፈራ ማሞ ሕክምና እንዲያገኙ እንዲፈቅድ ፓርቲያችን በአጽንዖት ይጠይቃል። በሌላ በኩል እኒህን መሠል ዋጋ የከፈሉ ጀግኖችና ቤተሰቦቻቸው ከያሉበት እየተፈለጉ የሚዲያ ትኩረት እንዲሰጣቸው፣ መንግሥት በቂ የሆነ መዋቅራዊ እገዛ እንዲያደርግላቸው እና ሕዝብም ጀግኖቹን በብርታታቸው ጊዜ ብቻ ሳይሆን በችግራቸውና በድካማቸው ጊዜም አለኋችሁ እንዲላቸው ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡

ፈጣሪ ሀገራችን ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ይጠብቅ

እናት ፓርቲ
መጋቢት 19 ቀን 2015 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

@Leyu_News
@Leyu_News
1.6K views16:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-28 19:13:46
1.4K views16:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-28 19:06:15
በህገወጥ ከተሾሙት አባቶች ዉስጥ 17 የቀድሞ አባቶች ይቅርታ የጠየቁ ሲሆን ቀሪ 6 የቀድሞ አባቶች በህመም ምክንያት አልተገኙም ተባለ

ከቤተክርስቲያን በውግዘት የተለዩ 17 የቀድሞ አባቶች ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በተገኙበት በተደረሰው ስምምነት መሰረት 10ሩን የስምምነት ነጥቦች መቀበልላቸውን የሚገልጽ ደብዳቤ ለቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ለብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ዶ/ር አስገብተዋል።

ደብዳቤውን ያስገቡት 17 ሲሆኑ አንዱ ወደ ጸበል መሄዳቸውን ገልጸው ደብዳቤአቸውን በተወካይ አስገብተዋል። በጥቅሉ ደብዳቤ ያስገቡት 18 ሲሆኑ ቀሪዎቹ 6 የቀድሞ አባቶች በህመም ምክንያት እንዳልተገኙ በዛሬው ዕለት የተገኙት የቀድሞ አባቶች ገልጸው በቅርብ ጊዜ ቀሪዎቹ ግለሰቦች ማመልከቻቸውን ይዘው እንደሚመጡ ገልጸዋል።

ምንጭ፡ የ/ኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

@Leyu_News
@Leyu_News
1.5K views16:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-28 12:36:37 አቶ ክርስቲያን ታደለ "ስልጣን በመልቀቅ የመፍትሄው አካል አይሆኑም ወይ? ብለው ለጠየቁት ጥያቄ ጠ/ሚንስተሩ የሰጡት ምላሽ?

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የሰጡት ምላሽ፦

"ስልጣን ብትለቅ የተባለው በጣም ጥሩ ጥያቄ ነው ፤ ግን ጥሩ የሚሆነው ስልጣን ብንለቅ ነበረ ምክንያቱም መንግስት ማለት አስፈፃሚ ብቻ ማለት አይደለም። ህግ አውጪ መንግስት ነው፣ ህግ ተርጓሚ መንግስት ነው ፣ አስፈፃሚ መንግስት ነው እኛ እዚህ ያለን ሰዎች የመንግስት ባለስልጣኖች ነን።

ይልቁኑንም የተከበሩ አቶ ክርስቲያን ደግሞ የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ናቸው የአንድ ሚኒስትር አለቃ ናቸው እና በጋራ ብንለቅ ቢሆን ምክንያቱም እርሶም እንደሚገነዘቡት የሁሉ ችግር ምንጭ እና ባለቤት እኔ ብቻ ልሆን አልችልም። ኃላፊነት ከወሰድንም በጋራ ቢሆን ጥሩ ይሆናል ብዬ አስባለሁ።

ነገር ግን ይሄን ጥያቄ እሳቸው ቢያነሱትም እሳቸው ላይም ይነሳ ነበር በውጭ ያሉ እንደሳቸው ፓርላማ አሸንፈው መግባት ያልቻሉ ሰዎች ለምንድነው እኚህ ሰውዬ የቋሚ ኮሚቴ ኃላፊነት ላይ የተቀመጡት አይለቁም እንዴ ? እያሉ ከዚህ ቀደም በሚዲያ እንደምትሰሙት ብዙ ይተቻሉ፤ እርሶ ምርጫ አሸንፈው ነው የገቡት እዚህ ተቀምጠው የህዝቡን ጥያቄ ማንሳትዎ ተገቢ ነው ብዬ ማስበው መቆጣጠሩም የሚያደርጉት ጥረትም።

ግን ከስልጣን ጋር ተያይዞ ያለውን ጉዳይ በአንድ ቀላል ምላሴ ለማስረዳት በደቡብ ህንድ ጦጣን የማጥመድ ቴክኒክ አለ ጦጣን እንደምታውቁት ቁንጥንጥ ናት፣ ቅብዝብዝ ናት  ለአደን አትመችም እና በደቡብ ህንድ ያሉ አዳኞች ጦጣን ለማጥመድ የኮኮናት ፍሬ በጦጣ እጅ ልክ በቀጭኑ ይቀዱና ከውሥጥ ሩዝ ያስቀምጣሉ ሲቀዱት የጦጣ እጅ ቀጭን ስለሆነ በዚያ ልክ ይቀዱትና ውስጥ ግን ሰፋ አድርገው ሩዝ ያስቀምጣሉ፤ሊይዟት ስለማይችሉ ጦጣ ሩዝ አየሁ ብላ እጇን ሰዳ ካፈሰች በኃላ ልውጣ ስትል የተሰራው ለቀጭኑ ስለሆነ ከጨበጠች በኃላ አይለቃትም።

ይቺ ጦጣ የሰው ሩዝ ነው የያዝኩት የማይገባኝን ሩዝ ነው የያዝኩት ይዤው ከቆየሁ ልያዝ እችላለሁ በትኜው ልሂድ አትልም እንደጨበጠች ትታገላለች በዚህ ጊዜ ያን የኮከናት ፍሬ መውሰድ ስለማትችል አዳኙ መጥቶ ይይዛታል። ጦጣዋን ያደናት የያዛት ምንድነው ያላችሁ እንደሆነ ሃሳቧ ነው እንጂ ወጥመዱ አይደለም፤ እዛው በትና በትለቅ ትወጣለች በሀሳብ ግን ሩዝ አፍሼ ካልወጣሁ ስላለች ሀሳቧ አጥምዶ ያስቀራታል እዛው።

ዶሮ ብታልም ጥሬዋን እንደሚባለው ቁጭ ብለው የሚያልሙ ሰዎች አሉ ሁል ጊዜ በዚያ መንገድ ጥሩ አይሆንም።

ሁለተኛ ቢጨበጥ ጥሩ የሚሆነው ስልጣንን በሚመለከት በእኔ እና በተከበሩ አቶ ብናልፍ መካከል የሚደረግ ድርድር የለም። የስልጣን ባለቤት ህዝብ ነው፤ስልጣን ሰጪም ነፋጊም ህዝብ ነው፤እኔ ና አቶ ብናልፍ ማድረግ ያለብን የተሻለ ሃሳብ ይዘን ህዝባችን ጋር መቅረብ እና የኔን ሃሳብ ምረጥልኝ ብለን በሰጪው ነው የምንመረጠው እንጂ በምክር ቤት ውስጥ ስጠኝ ልቀቅልኝ በሚል አይሆንም።

ሰጪው ጋር ሃሳብ የተሻለ ይዞ መቅረብ ታስፈልጋል፤ ስለዚህ ስልጣን በኮሮጆ እንጂ በመናጀ አይያዝም እና ሶስት ዓመት ይቅራል ለምርጫ በውጭም አሉ ይሄ የኦሮሞ መንግሥት ይሄ የኦሮሞ መንግስት እያሉ የሚዘፍኑ ዘፋኞች አሉ እነሱን ጨምሮ ሰብሰብ ብሎ ሃሳብ አጠናክሮ ለኢትዮጵያ ህዝብ ማቅረብ ነው እኛ ለኢትዮጵያ ህዝብ እንደተባለድ የተገባውን ቃል ካልመለስን የኢትዮጵያ ህዝብ በእኛ አስተዳደር ካልረካ በምርጫ ከጣለን በተደጋጋሚ እንዳልነው በደስታ እናስረክባለን። ፓርቲዎች መዘጋጀት ያለባቸው ሃሳብ ይዘው መምጣት ነው፤ አሁን ሃሳብ የለም፤ ሰብሰብ ብሎ ሃሳብ ይዞ ያን ወደ ህዝብ አቅርቦ ለመመረጥ እና ለማሸነፍ የሚደረግ ጥረት ለሁላችን የሚጠቅመን ይሆናል" ብለዋል።

 @Leyu_News
@Leyu_News
1.9K views09:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-28 11:56:47
ላለፉት ሀምሳ አመት ሶስት አይነት  ፖለቲካዎች በኢትዮጵያ ነበሩ፤
የመተላለፍ ፣የሴራ እና የጉልበት ፖለቲካ  ናቸው።

ሰላም እንደ ጦርነት ጀግንነት ይፈልጋል። እኛ እሱ ላይ እየሰራን ነው።

*ክልል ከተኮነ በኋላ ሳምንት አይቆይም ደስታው

*ሙስናን  በአቅማችን እየተዋጋን ነው።

*አንዳንድ ሚዲያዎች ያልሞተን ሰው ሞተ እያሉ የሟርት ስራ እየሰሩ ነው።

*ኢትዮጵያን  እያፈረሳቹ ነው ተብሎ  ለተጠየቀው ጥያቄ የአመቱ ምርጥ ቀልድ ብየዋለው

ጠ/ ሚ ዐብይ አህመድ

@Leyu_News
@Leyu_News
1.8K viewsedited  08:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-28 10:37:30 የተከበሩ አቶ ክርስቲያን ታደለ ዛሬ መጋቢት 19 ቀን 2015 ዓ.ም እየተካሄደ ባለው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 11ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ  ያቀረቡት ጥያቄ፤
**
አመሰግናለሁ የተከበሩ አፈጉባዔ፤

አመሰግናለሁ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስቴር፤

ጥያቄዬን ከማቅረቤ በፊት ስለጥያቄዬ ትንሽ ማለት እፈልጋለሁ። ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር በዚህ ምክር ቤት እና በተለያዩ መድረኮች ስለእርስዎና ስለሚመሩት የአስፈፃሚ መንግስት ተጠየቅ ሲቀርብብዎ ለተጠየቁ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ ጠያቂዎችን የሚያጥላላ አስተያየት ሲያራምዱ፤ አለፍ ሲልም ተጠየቅ የቀረበብዎት የወጡበት ብሔርን በመጥላት እንደሆነ አድርገው ምላሽ መስጠትዎ የቅርብ ትዝታ ነው። ክቡር ጠቅላይ ሚኒስቴር ቀጥዬ የማቀርብልዎ ጥያቄ ራስዎንና መንግስትዎን የሚመለከት እንጂ ሌላ ማንንም የማይመለከት መሆኑን ማረጋገጥ እፈልጋለሁ። እኔም ጥያቄውን የማቀርብልዎት በብሔር አይደለም። ምላሽ ሲሰጡም የመንግስት ግልበጣ ለማድረግ የተሼረበ ሴራ ነው የሚል እንደማይሆን ተስፋ አደርጋለሁ። ጥያቄዬ የሚከተለው ነው።

የዜጎችን ደኅንነት እና የአገርን ሉዓላዊነት መጠበቅ ዝቅተኛ የመንግስት ኃላፊነት ሆኖ ሳለ ዜጎች በማንነታቸው ምክንያት በመንግስት የፀጥታ ኃይሎች ይገደላሉ፤ ይፈናቀላሉ፤ ቤታቸው ይፈርሳል፤ ንብረታቸውም ይወድማል። የአገር ሉዓላዊነትን በሚዳፈር መልኩ የጎረቤት አገራት ሰራዊቶች በኢትዮጵያ ሰሜን ምዕራብና ደቡብ ምዕራብ ወሰኖች በርካታ ኪሎሜትሮችን ዘልቀው በመግባት ወረራ ፈጽመዋል። አሁን ላይ ባለው ተጨባጭ ሁኔታ የዜጎች ደኅንነትና የአገር ሉዓላዊነት ዋነኛ የስጋት ምንጭ ሆኖ የምናየው ራሱ መንግስትን ነው። እርስዎ  በአፍዎ «ኢትዮጵያ አትፈርስም» ቢሉንም በተግባር ግን ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነት በመንግስትዎ እየተናዱ ነው። የበርካታ አገራት መሪዎቸ መሰል ኃላፊነትን በወጉ ያለመወጣት ጉድለት ሲያሳዩ ሕዝብን ይቅርታ ጠይቀው ሥልጣናቸውን ሲለቁ ይታያል። በአገራችንም የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ኃይለማርያም ደሳለኝ ተመሳሳይ ሕዝባዊ ተጠየቅ ሲቀርብባቸው ሥልጣን መልቀቃቸው ይታወሳል።

እርስዎስ ሥልጣንዎን በመልቀቅ የመፍትሔው አካል ለመሆን አላሰቡም ወይ?  በሰብአዊነት ላይ በተፈፀሙ እንዲሁም የማንነት ተኮር የዘር ማጥፋት፣ የዘር ማጽዳትና የማንነት ማሳሳት ወንጀሎች ተጠያቂ ለመሆን ምን ያህል ዝግጁ ነዎት?

አመሰግናለሁ!

@Leyu_News
@Leyu_News
1.8K views07:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-28 10:37:12
1.6K views07:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-28 09:45:11
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተገኙበት ስብሰባውን እያካሄደ ነው!

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 11ኛ መደበኛ ስብሰባው የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) በተገኙበት መካሄድ ጀምሯል።የምክር ቤቱ አባላት ጥያቄዎችን እየቀረቡ ሲሆን፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለቀረቡላቸው ጠያቄዎች ምላሽ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።

እስካሁንም ከኦነግ ከሸኔ፣ ከአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ፣ ከሰሜኑ የሰላም ስምምነት፣ ከዜጎች መፈናቀልና ግድያ፣ ወደ አዲስ አበባ እንዳይገቡ ስለተከለከሉ ዜጎች፣ አርሶ አደሩ ምርቱን ለመሸጥ ከመቸገሩ ጋር በተያያዘ፣ ወደ አዲስ አበባ ምርት እንዳይገባ ከመከልከሉ ጋር፣ ከክልሎች የርስ በርስ መናበብ አለመቻል፣ የሱዳን ወታደሮች ወረው የያዙትን የኢትዮጵያ መሬትና ያወደሟቸውን ንብረቶች የተመለከቱ ጥያቄዎች ቀርበዋል።አሁንም የምክር ቤቱ አባላት ጥያቄዎችን በማቅረብ ላይ ናቸው።

@Leyu_News
@Leyu_News
1.8K views06:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-28 09:01:10
ሁሉም አብራሪዎች በአለም አቀፍ በረራዎች ላይ እንግሊዘኛ እንዲናገሩ ይጠበቅባቸዋል። ስለዚህም እንግሊዘኛ የሰማይ ቋንቋ እንደሆነ ይቆጠራል።

ፊደል ፖስት

@Leyu_News
@Leyu_News
1.7K views06:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ