Get Mystery Box with random crypto!

ISLAM IS UNIVERSITY

የቴሌግራም ቻናል አርማ islamisuniverstiy_public_group — ISLAM IS UNIVERSITY I
የቴሌግራም ቻናል አርማ islamisuniverstiy_public_group — ISLAM IS UNIVERSITY
የሰርጥ አድራሻ: @islamisuniverstiy_public_group
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 22.95K
የሰርጥ መግለጫ

⭐️ሰው የሚገነዘብ አእምሮና የሚያፈቅር ልቦና ባለቤት ነው።እነዚህ ሁለቱ ካልተመጣጠኑ ስብእናው አደጋ ውስጥ ነው።የሚያገናዝበው አዕምሮው፣የሚያፈቅረው ልቡ፣የሚንቀሳቀሰው አካሉናወደ ሰማይ የሚወነጨፈው መንፈሱ በውህደት ካልተንቀሳቀሱ ሰውየው ላይ ችግር አለ ማለት ነው
📨የፍቅር እና የጥላቻ ስሜቱ፣የፍላጎት እናየፍርሃት መንፈሱ በአዕምሮ ብስለት ካልተገራ አስቸጋሪ ነው
አስተያየት👇
T.me/Aisuu_bot

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2023-05-01 06:33:45
አስገራሚና አስተማሪ ገጠመኝ...

አንድ ሰውዬ በኬኒያ ሀገር ለመታከም ወደ መንግስት ሆስፒታል አቅንቷ 'X-ray' ከተነሳ በኋላ ፣ በጥሩ ጤንነት ላይ ያለች በረሮ ልቡ ውስጥ እንዳለች ይነገረዋል ።

ወደ ሲንጋፖር ሄዶም መታከም እንዳለበት ይነግሩታል ።
ታማሚውም ወደ ሲንጋፖር ሄዶ ሲታይ ፣ የታየው በረሮ ልቡ ውስጥ ሳይሆን 'X-ray' ከሚያነሳው ማሽን ውስጥ የተገኘ መሆኑን ያስረዱታል ።

ብዙ ግዜ የምንያበትን ነገር ሳናፀዳ አሊያም የምንመለከትበት መስታወት ሳነነፃ የሌላውን እድፍ ለመናገር እንሮጣለን ፣ እድፉ እኛ ምንለው ነገር ሳይሆን አስተሳሰባችን ወይም የምናይበት መነፅር ነው !
2.8K views03:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-30 06:40:22
በሀገረ ግብፅ አንዲት እናት የ5 አመት ልጇን አርዳ ሬሳውን አብስላ ከፊሉን እንደበላች በፖሊስ ተይዛ ለዐቃቤ ህግ ተላልፋ ስትሰጥ "ለዘልዓለም እንዳይለየኝ አካሉን ለመብላት ሞከርኩ" በማለት መናገሯን አልጀዚራ ዘግቧል።

"ዲን መያዝ ፍም የመጨበጥ ያህል ከባድ ይሆናል" ተብሎ በረሱል (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) አንደበት የተገለፀው ዘመን ይህ ነው እንዴ?!" በማለት አንድ ወጣት አላህን አብዝተው የሚፈሩትን ዓሊም ጠየቀ

ዓሊሙም በአርምሞ እየተመለከቱት "ያ ዘመንማ ካለፈ ቆይቷል። አሁን ያለንበት ዘመን "አንድ ሰው ሙስሊም ሆኖ ያነጋል። ካፊር ሆኖ ያመሻል። በጥቂት ዱንያዊ ጥቅም ዲኑን ይሸጣል" እንዲህ በረሱል አንደበት የተገለፀበት ዘመን ላይ ነን አሉት።
2.5K views03:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-29 07:25:52 አረቦች አይደሉም ግና መግባቢያ ቋንቋቸው አረብኛ እንዲሆንላቸው ታግለዋል። በክርስቲያን ግዛት ውስጥ ያሉ አናሳ ቁጥሮች ግና በኢስላማዊ ህግ በሸሪዓ ድንጋጌ መዳኘትን የጠየቁ በሒጃባቸው የፀኑ፣ ሰላታቸውን የማያዛንፉ ቋሚዎችና ጿሚዎች ናቸው።


በቁጥር ጥቂት ተፅዕኖ ፈጣሪነታቸው ግን ግዙፍ ነው። የክርስቲያኖች ቁጥር ከ80 ሚሊዮን በላይ በሆነባት ሀገር ውስጥ የሚኖሩ ከ15 ሚሊዮን የማይበልጡ ጀግኖች

የስፔንን ወረራ በመጋፈጥ የዘመቻውን መሪ የገደሉ!
ሀገራቸው ለአሜሪካዊያን በ20 ሚሊዮን ዶላር ተሽጦባቸው እጃቸውን ያልሰጡ!
ለተከታታይ 40 ዓመታት የአሜሪካን ወረራ ተቋቁመው እስልምናን መንካት ቀይ መስመር መሆኑን ያስተማሩ ፅኑዎች።

በ1972 ፊሊፒን የካቶሊክ ክርስቲያን ሀገር እንድትሆን ፕሬዝዳንት ፈርዲናንድ ማርኮስ ለቫቲካን ሊቀ ጳጳስ ቃል በገባላቸው መሠረት ሙስሊሞች ላይ ብዙ እልቂቶችን ፈፀመ። የግፍ በትሩ በየከተማው ተቀጣጥሎ መንደሮችን ዘልቆ በየቤቱ ደረሰ።

  ይህን ግፍ ለማስቆም የሞሮ ብሄራዊ ነፃ አውጪ የሙጃሂዶች ግንባር ወታደራዊ ጂሃድን አወጀ። ከ150,000 በላይ ሙስሊሞች ሸሂድነትን ተጎናፅፈው አፀደ ገላቸው ከጂሃዱ ሜዳ ስር አረፈ። በርካቶች ቆሰሉ። ብዙዎችም ሀገር ለቀው ተሰደዱ።

ከበርካታ የትግል አመታት በኋላ ድልን ተጎናፀፉ
   ኢስላማዊ እሴቶቻቸውን አያከብርምና ዓለማዊ አገዛዝን ውድቅ አደረጉ። ኢስላማዊ ህግ በሀገራቸው ተፈጻሚነትን ያገኝ ዘንድ ራሳቸውን በራስ ማስተዳደር ጀመሩ። የላኢላሀ ኢለላህ ዓርማ የሰፈረበትን ባንዲራ አውለበለቡ። ግና በውስጣዊ ሽኩቻ ነፃነታቸውን ዳግም አጡ።

እንደ አውሮፓውያን የዘመን ቀመር በ2019 በተካሄደው ህዝባዊ ውሳኔ የራስ ገዝነታቸው ፀድቆ ሸሪዓ በስርዓተ ትምህርታቸው ላይ እንዲካተት ተወሰነ። በርካቶች ተገረሙ። አብዛኛው ነዋሪዎቿ ክርስቲያኖች በሆኑባት ከተማ የመስቀል ዓርማ በመንደሮቿና በአካባቢዎቿ በተተከለባት ሀገር ህዝበ ክርስቲያኑ በሙስሊሞች ህግ ለመዳኘት መወሰኑ እጅጉኑ አስደነቀ። "በእስልምና ውስጥ ፍትህና ፍቅር አጊንተናል" ሲሉ ነዋሪዎቿ ምስክርነታቸውን ሰጡ። ሸሪዓ ከህጋቸው ጋር እንዲካተት ታወጀ።

ይህ በዓለም ላይ እስልምና በከፍተኛ ደረጃ የተስፋፋበት ሀገረ ፊሊፒን ናት።
644 views04:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-29 07:25:22
አረቦች አይደሉም ግና መግባቢያ ቋንቋቸው አረብኛ እንዲሆንላቸው ታግለዋል። በክርስቲያን ግዛት ውስጥ ያሉ አናሳ ቁጥሮች ግና በኢስላማዊ ህግ በሸሪዓ ድንጋጌ መዳኘትን የጠየቁ በሒጃባቸው የፀኑ፣ ሰላታቸውን የማያዛንፉ ቋሚዎችና ጿሚዎች ናቸው።

በቁጥር ጥቂት ተፅዕኖ ፈጣሪነታቸው ግን ግዙፍ ነው። የክርስቲያኖች ቁጥር ከ80 ሚሊዮን በላይ በሆነባት ሀገር ውስጥ የሚኖሩ ከ15 ሚሊዮን የማይበልጡ ጀግኖች
561 views04:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-29 07:21:58
እንደ አውሮፓውያን የዘመን ቀመር ከ1816 - 1824 በአልጄሪያ ቆንስላ ተመድቦ የነበረው ትውልደ አሜሪካዊው ዊልያም ሻለር እንዲህ ይላል፡-

"በአልጄሪያ ባሳለፍኳቸው ተከታታይ ስምንት ዓመታት የአልጄሪያዊያንን ሙስሊም ሴቶች ቅርፅና መልክ በህይወቴ ተመልክቼ አላውቅም። ኒቃብ ባህላቸው አይደለም በሙስሊም ሴቶች ልብ ላይ የታተመ ሀይማኖታዊ መመርያ ነው"
451 views04:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-29 07:20:48
በታላቁ ሱልጣን ሱለይማን አልቃኑኒ የአመራርነት ዘመን በፈረንሳይ ውስጥ ሴቶች እርቃናቸው እየጨፈሩ ነው የሚል ዜና ኸሊፋው ዘንድ ደረሰ። በንዴት በግኖ ደብዳቤን ወደ ፈረንሳዩ ንጉስ ላከ፡፡

"በሀገራችሁ ያሉ ሀፍረት የሌላቸው ሴቶች እርቃናቸውን ከወንዶች ጋር ተቃቅፈው እየጨፈሩ መሆኑን ሰምቻለሁ። ሀገራችሁ ከእኛ ድንበር ጎን ስላለች ይህ ጋጠወጥ ስነምግባር ወደእኛም ሊዛመት ይችላልና መልዕክቴ እንደደረሰህ ይህን እርኩስ ተግባር አስቁም። አለዚያ እኔው ዘምቼ ለማስቆም ጦሬን ሰብቄ ወደናንተው ሀገር እመጣለሁ"
ከዚህ ደብዳቤ በኋላ በሀገረ ፈረንሳይ ጭፈራው ለመቶ ዓመታት ሙሉ በምስጢርና በድብቅ ይከወን እንደነበረ የኦስትሪያው ታሪክ ጸሐፊ ሀመር ዘግቧል፡፡
430 views04:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-29 07:18:46
ደስታውንና ሐዘኑን በእግር ኳስ ተጫዋቾች ጫማ ስር ያደረገ በእርግጥም ከሰረ። ለኳስ የሚያነባ ዓይን የሙስሊሞችን ቅዱስ ሥፍራ ነጻ ሊያወጣ ክብራቸውንም ሊያስመልስ ፈፅሞ አይቻለውም


ትራምፕ እየሩሳሌምን የጽዮናዊት ዋና ከተማ መሆኗን ለማወጅ ሲነሳ በምስሉ ላይ የሚታየው ህፃን በጽዮናዊው ወታደር ፊት በጀግንነትና በኩራት ቆሞ ይታያል

የህፃኑ ሁኔታ የነገን ምስል ያሳያል። እየሩሳሌምን ነፃ የማውጣት ተስፋ የኡማው እጣ ፈንታ እኔ ነኝ ይላል።

ከታች ያለው ምስል በአለም ዋንጫ ማጣሪያ በግብፅ እና በኮንጎ መካከል በነበረው ግጥሚያ ኮንጎ በግብፅ እግር ኳስ ቡድን ላይ ጎል በማስቆጠሩ ወጣቱ እያለቀሰ ይታያል

ይህን ወጣት ሴቶች ሲያዩት ስለወደፊታቸው ሊሰጉ ስለደህንነታቸው ሊፈሩ ይገባቸዋል።

ኻሊድ አርራሺድ እንዲህ ይላል
"ይህ ትውልድ አቅሳን ነፃ እንዲያወጣ ትፈልጋላችሁን?! በፍፁም እንደውም የጠላቶች መሻገርያ ድልድይ፣ ልጓሟቸውን ይዘው የሚጎትቷቸው ባርያ ይሆናሉ። እንደነዚህ ዓይነቶቹ የኢስላምን ምሽጎች ለጠላት አሳልፈው ይሰጣሉ። የመስጂደል አቅሳን ቁልፍ ያስረክባሉ። እስልምና በልባችን ውስጥ ከሞተ የታል ጥንታዊ ኩራታችን የታለ ያ ውብ ኃያልነታችን?! ዋ በዲኔ ላይ ቁጭቴ! ዋ በወንድነቴ ላይ ቁጭቴ! በታላቁ አላህ እምላለሁ የትኛውም ህብረተሰብ በዚህ ሁኔታ ላይ ካደገ ለኢስላም ሊደነግጥ በፍፁም አይቻለውም። አይሁዶችና የመስቀል አምላኪዎች ማንነታችንን በመግፈፍ ላይ ተሳክቶላቸዋል። ዲን የለ ክብር የለ"
422 views04:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-29 07:16:19 በያዘው ፎጣ መኪናዬን እየጠራረገ
"የመኪናህን መስታወት ላፅዳውን?" በማለት ጠየቀ። ድንቡሽቡሽ ፊቱ ችግር ያቆራመደው ይመስላል። በእጁ የጨበጠው ፎጣ መድረስ የሚፈልግበት ዓላማ እንዳለው ያሳብቃል። አንገቴን በመነቅነቅ በእሺታ ተስማማሁ።
  ስራውን በትጋት መስራቱ ስላስደሰተኝ 20 ዶላር ከኪሴ አወጣሁና ልሰጠው እጄን ዘረጋሁ። ብሯን በአግራሞት እያያት "ከአሜሪካ ነው እንዴ የመጣኸው?" ሲል ጠየቀኝ
"አዎ" አልኩት
"ከገንዘብ ይልቅ ክፍያዬ ስለ ዩኒቨርሲቲዎቻቸው ብትነግረኝስ?" አለኝ

  ለዕውቀት ያለው ጉጉት ስላስገረመኝ ተቀምጠን እንድናወራ የመኪናዬን በር እየከፈትኩለት
"ስንት አመትህ ነው?" በማለት ጠየቅኩት
"አስራ ስድስት" አለኝ
"የሁለተኛ ደረጃ የሀይስኩል ተማሪ ነሀ?!"
"በብዙ የትምህርት ዓይነቶች ጥሩ ውጤት ስላመጣሁ ሁለት ክፍሎችን ከፍ አድርገውኛል" አለ።
"እዚህ ፅዳት ስራ ላይ የተሰማራኸው ለምንድነው?" ስለው ትክዝ አለና
"አባቴ የሁለት ዓመት ልጅ እያለሁ ነበር ከዚህ አለም በሞት የተለየው። እናቴ የሰው ቤት ምግብ አብስላ ተሰቃይታ አሳደገችን። እሷን ለማገዝ መኪና አጥቤ በማገኛት ገቢ ራሴንና እህቴን አስተምራለሁ። በተረፈኝ ብርም እማን እኻድምበታለው" አለና ሳግ እየተናነቀው ንግግሩን አቋርጦ "የአሜሪካ ዩኒቨርስቲዎች በአካዳሚክ ትምህርታቸው ጥሩ ውጤት ላመጡ ተማሪዎች ስኮላርሺፕ እንደሚሰጡ ሰምቻለሁ ልትረዳኝ ትችላለህ?" አለኝ።
  "እሺ ግን መጀመርያ እንሂድና ምሳ እንብላ" አልኩት
"የመኪናውን የኋላ መስታወት ካጸዳሁልህ እሺ" አለኝና ተስማማን። ወደ ሬስቶራንቱ ዘልቀን ቦታችንን ይዘን ተቀመጥን። ከእናቱና ከእህቱ ጋር ለመመገብ ድርሻው ቴካዌ እንዲደረግለት ጠየቀ። የአነጋገሩ ለዛ እርጋታውና ቅልጥፍናው አግራሞትን ጫረብኝ።

  የምችለውን ሁሉ ልሞክርለት ቃል ገብቼ የትምህርት ሰነዶቹን ተቀብዬው ተሰነባበትን። ከስድስት ወራት በኋላ ስኮላሩ ተቀባይነትን አገኘ። እንኳን ደስ አለህ በማለት አበሰርኩት።
"በአላህ እምላለሁ ቤታችን በደስታ ለቅሶ ተውጦ እንባን እያረገፍን ነው" አለኝ።

ከሁለት ዓመታት በኋላ ስሙ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ትንሹ ኤክስፐርት ሆኖ በኒውዮርክ ታይምስ መጽሔት ላይ ታትሞ ወጣ። በጣም ተደሰትኩ። ባለቤቴ ለእናቱና ለእህቱ በድብቅ ቪዛ አሰርታ አሜሪካ አስመጣቻቸው። ወጣቱ እናቱንና እህቱን በድንገት ሲያያቸው መናገርም ማልቀስም ተስኖት በድንጋጤም በደስታም ፈጠጠ።
አንድ ቀን ከቤተሰቤ ጋር ቤት ውስጥ ተቀምጠን መኪናዬን ሲያጥብ በመስኮት በኩል ተመለከትኩት
"ምን እያደረግክ ነው?" ስልም ጠየቅኩት
"የነበርኩበትን እንዳልረሳ አንተም ያደረክልኝን ውለታ እንዳልዘነጋ ነው" አለኝ

ስሙ ፈሪድ ዐብዱልዐሊ ይሰኛል ፍልስጤማዊ ወጣት ነው አሁን በአሜሪካ harvard (ሃርቫርድ) ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ካሉ ምርጥና ታዋቂ ፕሮፌሰሮች መካከል አንዱ ነው።

መልካምነት የተሰበሩ ልቦችን ጠግኖ ለስኬት ያበቃልና መልካም እንሁን።
419 views04:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-29 07:15:53
በያዘው ፎጣ መኪናዬን እየጠራረገ
"የመኪናህን መስታወት ላፅዳውን?" በማለት ጠየቀ። ድንቡሽቡሽ ፊቱ ችግር ያቆራመደው ይመስላል። በእጁ የጨበጠው ፎጣ መድረስ የሚፈልግበት ዓላማ እንዳለው ያሳብቃል። አንገቴን በመነቅነቅ በእሺታ ተስማማሁ።
  ስራውን በትጋት መስራቱ ስላስደሰተኝ 20 ዶላር ከኪሴ አወጣሁና ልሰጠው እጄን ዘረጋሁ። ብሯን በአግራሞት እያያት "ከአሜሪካ ነው እንዴ የመጣኸው?" ሲል ጠየቀኝ
"አዎ" አልኩት
"ከገንዘብ ይልቅ ክፍያዬ ስለ ዩኒቨርሲቲዎቻቸው ብትነግረኝስ?" አለኝ
420 views04:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-29 07:13:59
እናቱን ሊዘይር ወደ መቃብር ሥፍራው አቀና
ቀብሯን ታቅፎ እንደተጋደመ ከጎኗ ሞቶ ተገኘ
422 views04:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ