Get Mystery Box with random crypto!

ISLAM IS UNIVERSITY

የቴሌግራም ቻናል አርማ islamisuniverstiy_public_group — ISLAM IS UNIVERSITY I
የቴሌግራም ቻናል አርማ islamisuniverstiy_public_group — ISLAM IS UNIVERSITY
የሰርጥ አድራሻ: @islamisuniverstiy_public_group
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 22.95K
የሰርጥ መግለጫ

⭐️ሰው የሚገነዘብ አእምሮና የሚያፈቅር ልቦና ባለቤት ነው።እነዚህ ሁለቱ ካልተመጣጠኑ ስብእናው አደጋ ውስጥ ነው።የሚያገናዝበው አዕምሮው፣የሚያፈቅረው ልቡ፣የሚንቀሳቀሰው አካሉናወደ ሰማይ የሚወነጨፈው መንፈሱ በውህደት ካልተንቀሳቀሱ ሰውየው ላይ ችግር አለ ማለት ነው
📨የፍቅር እና የጥላቻ ስሜቱ፣የፍላጎት እናየፍርሃት መንፈሱ በአዕምሮ ብስለት ካልተገራ አስቸጋሪ ነው
አስተያየት👇
T.me/Aisuu_bot

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-07-25 06:37:59
ከድህነቱ የተነሳ ትምህርቱን ሊገፋበት ይቅርና የሚላስ የሚቀመስ እንኳ በቅጡ አጣ። የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን አቋርጦ ለ24 አመታት ኤርፖርት ውስጥ በጽዳት ሰራተኝነት እያገለገለ ኑሮውን ይገፋ ጀመረ። ትውልደ ናይጄሪያዊ ነው። ሙሐመድ አቡበከር ይሰኛል። በማታ ፈረቃ ትምህርቱ ላይ እየተጋ ቀን ቀን ሽንት ቤት እያፀዳ በመጨረሻም አውሮፕላን አብራሪ ካፒቴን ሆኖ ተመረቀ።

እምነትና ቆራጥነት የጠንካሮች መሳርያ ናት


Join
t.me/IslamisUniverstiy_public_group
  t.me/IslamisUniverstiy_public_group
1.0K viewsedited  03:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-22 05:45:50 እያለቀስክም ቢሆን የበሩ መከፈት ቢዘገይ እንኳን አትዘን፡፡ ዋናው ሳትሰለች በሩ ላይ ቆመህ መገኘትህ ነው፡፡ በሀይልና በተደጋጋሚ የተንኳኳ በር መከፈቱ ግድ ነው፡፡ እስልምናህን የምትወድ ከሆነ አላህ ይከፍትልሀልና ተስፋ አትቁረጥ፡፡ አላህ ይሰጥሀል፡፡ ውስጥህ ያለውንም ተስፋ ያድሳል፡፡ አል-ፈታሕ ብለህ በስሙ ጥራው፡፡ በርግጠኝነት ይከፍትልሀል፡፡


ነብዩ ሰዐወ በለሊት ተነስቶ ሚስቱንም ቀስቅሶ ሁለት ረከአ ለሰገዱት አላህ ይዘንላቸዉ ብለዋል፡፡
እናም ተኝቶ ድምፃችን ይሰማ እያሉ ከማንኮራፋት ተነስቶ ሚስትህ ጋር መስገድ አብራችሁ ዱአ ማድረግ ለዚህ ቅጥ ላጣ ዘመን መፍትሄ ነዉ፡፡

ዱንያ የደስታ ምንጭ አይደለችም ይሄን ማወቅ አለብን አላህ የትንኝ ክንፍ ለኔ ቦታ የላትም ብሎ እኛ ደስተኛ እንሆናለን ብለን ራሳችንን አናሳምን

አል ኢማም አር ራዚ ቆንጆ ልብስ መልበስ ይወዱ ነበር፡፡ አንድ ቀን ከመስጅድ ወጭ እያሉ አንድ ሙስሊም ያልሆነ ሰው ጋር ተገናኙ፡፡ ሰውዬው የተበጣጠሰ ልብስ ነበር የለበሰው፡፡ ለኢማም አርራዚ እንዲህ አላቸው የናንተ ነብይ ይህች ዓለም ለአማኞች እስር ቤት ለከሐዲዎች ጀነት ናት፡፡› ይላል፡፡ ይህን የመሰለ ፀጋ ውስጥ እያለህ ከየትኛው እስር ቤት ውስጥ ነህ? እኔስ በየትኛው ጀነት ውስጥ ነኝ? አላቸው፡፡ ኢማም እርራዚም እኔ አሁን ያለሁበት ሁኔታ በጀነት ውስጥ ካለው ድሎትና ፀጋ አንፃር እስር ቤት ነው፡፡ አላህ (ሱ.ወ) በጀሃነም ውስጥ ለከሐዲያን ካዘጋጀው ቅጣት ደግሞ አንተ አሁን ያለህበት የችግር ኑሮ ጀነት ነው፡፡ አለው፡፡ ሰውዬውም ጥቂት ካስተነተነ በኋላ በርግጥም የናንተ መልእከተኛ የተናገረው እውነት ነው፡፡› አለና ሰለመ፡፡

ይህች ዓለም እስር ቤት መሆኗ፣ አላህ (ሱወ) ጀነትን ለኛ ማዘጋጀቱ፣ አኺራ በላጭና ዘላለማዊ መሆኗ ... ይህ ሁሉ አላህ (ሱ.ወ) እኛን ሊያስደስተን የፈለገ መሆኑ ያመላክተናል፡፡ _ ስለሆነም ጀነት ሊያስገባን ብሎ ይከታተለናል፣ ይጠብቀናል፣ በችግሮችም ይፈትነናል፡፡

በተጨማሪም ሲህርም ባይሆን ማንኛዉም ህመም ሲያጋጥመን ሀኪም ቤት ልሂድ ከማለት መጀመሪያ አላህ እንዲያሽረን እንማፀን

ዑሥማን ኢብን ጦለሐ የሚባል ሰሐባ ነብዩ (ሰዐወ) ዘንድ መጣና የአላህ መልእተኛ ሆይ!!! ሰውነቴ ውስጥ ህመም ይሰማኛል፡፡ አላቸው፡፡ ነብዩም (ሰዐወ)  በአላህ (ሱ.ወ) መካከል ያለው ግንኙነት የጠበቀ እንዲሆን ፈለጉ፡፡ እናም በሚያምህ ቦታ ላይ እጅህን አኑርና ሶስት ጊዜ ቢስሚላህ በል፡፡ ከዚያም ሰባት
ጊዜ አዑዙ ቢላሂ ወቁድረቲሂ ሚን ሸር ማ አጂዱ ወኡሓዚሩ፡፡" በል አሉት፡፡ ሰሐባውም እሳቸው እንዳሉኝ አደረኩኝ፡፡ ህመሙም ለቀቀኝ፡፡ በአላህ እምላለሁ ከዚያ ቀን ጀምሮ ለቤተሰቤና ለማውቀው ሰው ሁሉ ከማስተማር ወደኋላ አላልኩም፡፡› ብሏል፡፡


ታማሚም አስታማሚም አላህ ፅናቱን ጥንካሬዉን ይስጠን...እኛም ለዲናችን ጠቃሚ ለሰዉ የምንተርፍ ያድርገን
ለሰዉ ክፋት መጥፎ የምናስብ ሰዎች እባካችሁ ቶብቱ በሰዉ ደስታ ለምን እንደኛ ይቸገር እንላለን??
ክፉዉን ማዳመጥ ማየት የክፋት መጀመሪያ ነዉ
ክፋት በሰዉ ባህሪ ዉስጥ አብሮ የተፈጠረ ሳይሆን ክፋትን ማስወገድ ባለመቻሉና ዉጫዊ ተፅእኖዉን መቋቋም ስላቃተዉ የመጣበት ነገር ነዉ፡፡
ህይወት ወጪዉን የማትሸፍን ንግድ ነችና በእሷ ስኬትን በሀራም በጠንቋይ በሳሂር እገዛ እጨብጣለሁ ብለህ አትሰብ እናም በሰዉ ስቃይ ሀዘን ለቅሶ መደሰት ምን የሚሉት ህሊና ነዉ ?? አላሁ የስቱርና አላህ ከመጥፎ ባህሪ አመል ይጠብቀን


አላህ ሆይ ከደጋሚዎች ከሳሂሮች ተንኮል ጠብቀን...ምቀኛን ቀናተኛን ከጎናችን አርቅልን..ስቀዉ ከሚጎዱ የቅርብ ሰዎች ጠብቀን ያረብ...
ሲህር የተየደረገብን የታመምን ወይ ሲህር ተደርጎብን ሳናቅ ብዙ አመታት ፈጅቶ ከረፈደ ያወቅን አልሀምዱሊላህ ከረፈደም ማወቃቸዉን ...እንደ አጋጣሚ ያለወቅን ካለ አላህ አሳዉቀን ያረብ
ጠንቋይ ቤት ለሚሄዱትም ሂድያ ስጣቸዉ...

  ኢላሂ  ለዲነል ኢስላም  የምንጠቅም ባንጠቅም እንኳኝ በኛ እንዳይሰደብ የምንሆን ጀሊሉ ያድረገን
አንዳንዴ በማህበራዊ ሚዲያ ሙስሊሞች አለቅጥ ወንጀል ፈሳድ ላይ ተጥለቅልቀዉ የሌላ ሀይማኖት ወይም አንዳንድ ኢስላም ሲደፈር የሚቆጫቸዉ እህት ወንድሞች ሙስሊም አይደለሽ እንዴ ብለዉ ሰመከሩ
የማምለጫ ዘዴ አለች...እኔ ሙስሊም ነኝ ችግር ካለብኝ እኔን እንጂ እስልምናየን አትናገሩ ብለዉ ኮስተር ሲሉ ይታያሉ ይገርመኛል እነሱ ኢስላምን እያሰደቡ እስላምን አትሳደቡ እያሉ ቀጭን ኢስላምን አትንኩብኝ እያሉ የዉሸት ተስፋ ይዘራሉ...ተስፋ ጥሩ ቁርስ ቢሆንም መጥፎ እራት መሆኑን አንዘንጋ 
እናም በሚዲያ ላይ ሙስሊም ሁነን ጅልባብም ጀለብያም ለበስንም አለበስንም በኛ ኢስላም ሊሰደብ ሊመዘን አይገባም እኛ በኢስላም ሀይማኖት ማዕቀፍ ዉስጥ ነን አማኝ ነን ካልን ሙስሊም ተብለናል ...አማኝ ሙስሊም ባንሆን እንኳ ህሊናችን የሚሰራ ሰዉ እንሁን... አረ ሰዉ ሰዉ እንሁን እባካችሁ...ኢስላም በኔም በአንተም በእኛም በእናንተም እየተሰደበ እየተዋረደ ነዉ...አላህ ዲነል ኢስላምን እኔ ነኝ የምጠብቀዉ ስላለ ነዉ እንጂ በእኛ ስራ ቢሆን አፍርሰን ትቢያ አመድ አርገነዉ ነበር
ኢንሻ አላህ እያሉ ከመሾለክ ዝም ብሎ በምሉላስ አሏሁ አክበር እያሉ ሙስሊምን ከመጉዳት ያለችንን ትንሽየ ኢማን አላህ ያድስልን፡፡አላህ ጠንካራ የማይበገር ኢማን ይስጠን

#ዉድ የተከበራችሁ  አንባባዎች በ➊➎ part ስለሲህር ድግምት አይነጥላ ..ስለትዳር ስለስንፈተ ወሲብ በሁሉም ባሉት ቸግሮች ትኩረት አድርጌ አቅሪቢያሁ
የሰዉ ልጅ ነኝ እሳሳታለሁ ከኔ በላይ እዉቀት ያላችሁ እዚህ ቦታ ተሳስተሀል በሉኝ  edit ማድረግ እችላለሁ edit አሁኑ ላድርግ ከወር ቡሀላ edit ማድረግ ስለማይቻል ...ብዙ ሰዉ እያነበበዉ ሼር እያደረገዉ ስለሆነ ...ግን የተዘጋጀዉ ከመፅሀፍ እና ከሀዲስ ከሚያቁ ጠይቄ ስለሆነ እስከ አሁን በአስተያየት መስጫ አስተካክል የተባልኩት የለኝም፡፡ በአስተያየት ስሰጡ ሳነባቸዉ  በሲህር ተለክፈዉ የነበሩ እና በይፋ  ያደረገባቸዉ ሰዉ እየነገረን ነዉ ያሉኝ አሉ  ፡፡
ወደ 5 የሚሆኑ አስተያየቶች እኔን ካላገባሽ መቼም አታገቢ ብለዉ ከወንድየዉ ተነግሯቸዉ  እንዳላገቡ በተጨማሪ  አንዷ አግብታ ኒካሁ ታስሮ ሳይቆዩ እንደተፋታች የነገረችኝ አለች ...ሌሎቹ ይሄን ፁሁፍ ሲያነቡ ራሳቸዉን ፈትሸዉ ሩቃ ሊጀምሩ እንደሆነ አሳዉቀዉኛል...እናም በተለይ በትዳር ላይ የተተበተበ ጉድ ከባድ ነዉ ራሳችንን ማኔጅ ብናደርግ ጥሩ ነዉ

ለ15 ቀን በ15 ክፍል የቀረበዉን ፁሁፍ ሀምሌ 1 ጀምረን ሀምሌ 15 2015 ጨርሰናል ፡፡ባለመሰልቸት ባለመታከት አንብባችሁ ስለጨረሳችሁ ጀዛችሁን አላህ ይክፈላችሁ ለምን እኔም እናንተ ባነበባችሁበት ራሳችሁን በፈተሻችሁበት አጅር ስለማገኝ እናንተም ባነበበባችሁት እኔም ባዘጋጀሁት ተጠቃሚ ያድርገን፡፡

ወሰላሙ አለይኩም ወራህመቱሁ ወበረካትሁ
  #ተ.......... #ፈ.......... #ፀ........... #መ

አንብባችሁ ምን ተረዳችሁ?
ምን አስተያየት አላችሁ?
እዚህ ላይ ይፃፉ
T.me/Aisuu_bot T.me/Aisuu_bot
T.me/Aisuu_bot T.me/Aisuu_bot
ከፁሀፉ ያልገባችሁ ያልተዋጠላችሁ ካለ
2.1K views02:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-22 05:39:46 ጧኢፍ ነዋሪዎቿን በነቂስ አውጥታ የስድብ እና የድንጋይ ናዳ እንዲወርድበት ፈቀደች። ምድር ከሰውነቱ የሚፈሰውን ደም መጠጠች።
በመርዝ የተለወሰ ምግብ ሲሱጠት፣ ከሚናፍቅው የትውልድ ቀዬ ሲባረር ይቅር ባይነት የዘወትር ስንቁ ነበር። ስቃይ በተሸከመው አካልና መንፈሱ ታግዞ እግሮቹ አስከሚያብጡ ድረስ ለሊቱን በመቆም አመስጋኝ ባሪያ ለመሆን ከአምላኩ ጋር ያወጋል ሰዎችን ይቅር ይሉ ነበር ሀቢቡና ሙሀመድ ሰዐወ 
እናም ፈተና  መብዛት ችግር መደራረብ ባይኖር ዱንያ የደስታ ሀገር ብትሆን ሀቢቡና ሙሀመድ ሰዐወ ባልተፈተኑ ነበር እናም አንተም አንቺም እሱም እሷም እናንተም ፈተና ላይ ናቸሁ ፈተና ጨርሳችሁ ትንሽ ከተደሰታችሁ ቡሀላ ሌላ የከበደ ፈተና እንደሚጠብቀን እርግጠኛ ሁን የዛን ጊዜ ነዉ ኢማንህ የሚለካዉ፡፡
ኢማናችን መለካት እንጂ መነካት የለብንም ወገን


እጅግ አምልኮ በማብዛት የሚታወቀው ታላቁ ታቢዒይ አልፉደይል ኢብኑ ዒያድ ረሒመሁላህ ፈገግታ አያበዙም ነበር፡፡ በአንድ ወቅት ግን ልጅ ሲሞትባቸው ፈገግ አሉ፡፡ ለምን ፈገግ እንዳሉ በተጠየቁ ጊዜ “አላህ የወደደው ነገር ነውና እኔም ወድጄ ነው፡፡ አላህ (ሱ.ወ) የወደደውን እንድትወድ ነፍሴ ፈገግ እንድትል አስገደድኳት” አሉ፡፡

ዑለማዎች ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ያለቀሱበትንና አልፉደይል ግን ፈገግ ያሉበትን ሁኔታ በማንሳት ለመተንተን ሞክረዋል፡፡ በመታገስ ደረጃ አፉደይል ከነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ይበልጣሉ ማለት ፈጽሞ የማይታሰብ ነገር ነው፡፡ ነገር ግን ትርጉሙም፡- ሞት በሚመጣበት ቅፅበት ቀልብን በሁለት ሰሜት ውስጥ ይከታል፡፡ እዝነትና ውዴታ፡፡ ማንም ሰው ሁለቱን ስሜቶች በአንድ ጊዜ ማስተናገድ አይችልም፡፡ አልፉደይል ሁለቱን ማሳካት አልቻሉምና በውዴታ ስሜት አንድም ፈገግ ማለት አለባቸው አሊያም አብዝተው ማልቀስ ነበረባቸው፡፡ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ግን ሁለቱን ማሳካት ችለዋል፡፡ አላህ የወደደውን ወደዋል በሌላ በኩል ደግሞ አልቅሰው እዝነት ስሜት አሳይተዋል

የነቢያችን አክስት የሆነችው : እመት ሶፊያ በኡሑድ ጦርነት ወቅት ቁስለኞችን ውሃ ታጠጣ ነበር፡፡ ታላቁ ጀግና ሐምዛ (ረ.ዐ) ተገደሉና አካላቸውም እንዲቆራረጥ ሆዳቸው እንዲቀደድ ተደረገ፡፡ ሒንድ በበቀል ስሜት ጉበታቸውን እስከማኘክ ደረሰች። ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ለልጇ ዙበይር ኢብኑ አልዐዋም ዝበይር ሆይ! ሶፊያን ወደ መዲና ይዘሀት ሂድ ሐምዛን ማየት የለባትም፡፡” አሉት። ልጇም ሄደና “እናቴ ሆይ! ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ወደ መዲና ተመለሽ ብለውሻል፡፡” አላት፡፡

ልጄ ሆይ! ይህን የምታደርጉት ሐምዛን እንዳላይ ብላችሁ ነው አይደል? አለችው፡፡
....“አዎን” አላት፡፡
....እሷም “ልጄ ሆይ! አላህ ከዋለልን ፀጋ አንፃር በሐምዛ ላይ የደረሰው በጣም ቀላል ነው፡፡ አላህ (ሱ.ወ) በሐምዛ የፈተነን ሥራውን መውደድ አለመውደዳችንን ለማየት ነው፡፡ ወደ አላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ሂድና የአላህ መልዕክተኛ ሆይ አላህ በሐምዛ የፈተነን ሥራውን መውደዳችንን ለመፈተን ነው ብላለች ሶፊያ በላቸው ፡፡ ልጁም ወደ ነብዩ (ሲዐወ) በመመለስ ነገራቸው፡፡
... ነብዩም (ሰ.ዐ.ወ) “እንግዲያውስ ማየት ትችላለች፡፡” አሉ፡፡ ሄደችና አይታው አለቀሰች፡፡ ኢንና ሊላህ ወኢንና ኢለይሂ ራጂኡን የኛዑን እኛ የአላህ ነን ወደ አላህም ተመላሾች ነን፡ በማለትም ዱዓእ አደረገችለት፡፡
እናም አላህ በሚያመጣብን ፈተና የዱንያም ሆነ የጂን የሲህርም አላህ ወዶን እየፈተነን እንደሆነ አንዘንጋ

ጅን ሲህር ሳሂር ደጋሚ ጠንቋይ ደብተራ እንደማይጎዳ አሏህ ብቻ ጎጂ እንደሆነ ማወቅን ከኢማኖች ውስጥ ጠንካራ ኢማን ሁኖ እናገኘዋለን!! በአሏህ ላይ የቂን እጅግ የምንፈልገው መሳርያ ነው!! ሌቦች ቤትን ሊዘርፉ ሲመጡ አለሁ ብሎ ድምፅን ማሰማት ሲቀጥልም የመሳርያን ድምፅ ማሰማት እነርሱን እንደሚያስበረግጋቸው ሁሉ የቂን ልክ እንደዛው ጅኖችን ያስፈራቸዋል እንዳይቀርቡን!! ይሁንና ያለ እውቀት ያለ መጠበቅያ የቁርአን አያዎች እና ዚክሮቸች ማለት ያለ መሳርያ መሳርያ ታጥቀው የመጡ ሌቦችን ማስፈራራት ብቻ ነው፡፡ ለኛ መሳርያችን ለጅኖች ሊያውም ከባለጌዎች ለመጠበቅ የምንታጠቀው መሳርያ ዚክርና ቁርአን እንዲሁም ዱአእ ነው፡፡ ሌላውን አይነት የመሀይማን መሳርያ የሆነውን ጥንቆላ መተት ፀበል እና አንጃ ግራንጃዎች ልክ ሌቦችን እንደመማፀን እንደመደራደር ነው የምንቆጥረው፡፡ ከሌባ ጋር ድርድር የለም ባንተ ንብረት ላይ መጥቷልና ፡፡ ከጅን ጋርም እያጠቃህ መደራደር የለም በቁርአን በዚክር ልኩን አሳይተሀው  መከባበር እንጂ፡፡


እናም ፈጣሪ ይሁን ብሎ ተፅፎብን ከሆነ ትዕግስት ጥንካሬ ፅናት ያስፈልጋል፡፡ በሲህር በጂን የሚፈተን ሰዉ በዛዉም የፀና የጠነከረ አላህ ወዶን ይሆናል ዱአ ላይ መበርታት ግዴታ ነዉ...ከዱአ በጭራሽ ተስፋ ልንቆርጥ አይገባም
{ وَإِذَا سَأَلَكَ عِبَادِی عَنِّی فَإِنِّی قَرِیبٌۖ أُجِیبُ دَعۡوَةَ ٱلدَّاعِ إِذَا دَعَانِۖ فَلۡیَسۡتَجِیبُوا۟ لِی وَلۡیُؤۡمِنُوا۟ بِی لَعَلَّهُمۡ یَرۡشُدُونَ }
ባሮቼም ከእኔ በጠየቁህ ጊዜ (እንዲህ በላቸው)፡- እኔ ቅርብ ነኝ፡፡ የለማኝን ጸሎት በለመነኝ ጊዜ እቀበለዋለሁ፡፡ ስለዚህ ለኔ ይታዘዙ፤ በኔም ይመኑ፤ እነሱ ሊመሩ ይከጀላልና፡፡[አል በቀራህ: 186]


  አንድ ድንቅ የሆነ ሐዲስ አልቁድስይ ላካፍላችሁ፡፡ ነቢዩ ባስተላለፉት ሐዲስ አላህ (ሱ.ወ) እንዲህ ይላል፡- “የአደም ልጅ ሆይ! እኔም እፈልጋለሁ አንተም ትፈልጋለህ፡፡ እኔ ለምፈልገው ነገር እጅ የሰጠህ እንደሆነ የምትፈልገውን አመጣልሃለሁ እኔ ለምፈልገው ነገር እጅ የማትሰጥ ከሆነ በምትፈልገው ነገር ላይ  እንድትደከም አደርግሃለሁ፡፡ በመጨረሻ እኔ የምፈልገው ነገር ብቻ እንጂ የሚሆን የለም፡፡” ይለናል፡፡ አላህ (ሱ.ወ) በተከበረ ቃሉ “አላህ ካሻ በስተቀር አናንተ አትሹም (አል-ኢንሳን ፡3) ብሏል፡፡

ኢብኑ ዑመር (ረ.ዐ) ዱዓዬ መቼ ተቀባይነት እንደሚያገኝ አውቃለሁ፡፡ አሉ፡፡ “እንዴት ልታውቅ ትችላለህ? ተባሉ፡፡፡ “ቀልቤ በጥልቀት የአላህ ፍራቻ ካደረበት፣ መላ አካላቴ ከተንቀጠቀጠ፣ ዐይኔ ካነባች፣ ይህች ሰዓት ዱዓዬ ምላሽ የሚያገኝበት ነው፡፡ በማለት በዱዓዬ እጠናከራለሁ፡፡ ብለዋል፡፡

ለዱአ መቸኮል አያስፈልግም
ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) “እስካልቸኮላችሁ ድረስ ምላሽ ይሰጣችኋል፡፡” አሉ፡፡ መቸኮል ሲባል እንዴት ነው? ሲሏቸው አንዳችሁ “ዱዓእ አደረግኩ፤ ዱዓእ አደረግኩ ምላሽ አላገኘሁም፡፡ ይላል፡፡ (ተስፋ መቁረጥ) ዱዓእ ይተውን ይተዉና በዚያው ምላሽ ያጣል፡፡” ብለዋል፡፡
ሲህር ከተደረገብን ወደ አላህ የማይቋረጥ ቀጣይ የሆነ ዱአ ያስፈልጋል፡፡

ኢብኑ አልቀይም ረሒመሁላህ እንዲህ ይላሉ፡ ብትባረርም እንኳን ከአላህ በር ላይ ከመቆም ተስፋ አትቁረጥ፡፡ ቢመልስህም እንኳን ምክንያት ከማቅረብ አትውረድ፡፡ በሩ ተቀባይነትን ላገኙት የተከፈተ እንደሆነ ቀስ ብለህ በስርአቱ ግባ፡፡ ድሀ ነኝ ምፅዋት እፈልጋለሁ፡፡ በለው፡፡ ምፅዋት የሚሰጠው ለድሆችና ለችግረኞች ነው፡፡ እኔም ምስኪን ደሃ ነኝ፡፡ በለው፡፡
1.6K viewsedited  02:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-22 05:37:39 #ሲህር_ጂን_አይነጥላን_ራስን_በራስ_ማከም
                  አሚር ሰይድ


            
#የመጨረሻዉ_ክፍል



   #ራስን_በራስ_ማከም_ከዛም_ለሌላ_መትረፍ



ከpart ➊➍ ቀጥታ የቀጠለ.....
  ከዛር ዉጭ ያለን ሩቃን ለማድረግ ባንፈራ ጥሩ ነዉ ብቻ መጀመሪያ አላህን ይዘን ነይተን ሀስበነሏህ ብለህ መጀመር  ነዉ ፡፡


ከተሞክሮ እስኪ ጀባ ልበላችሁ ወላሂ ይሄን የምነግራችሁ ጀሊሉ ያቅብኛል ለጉራ አይደለም ባልፅፈዉ ደስ ይለኛል ግን እንድትደፍሩ እንዳትፈሩ ለመጠቆም ነዉ፡፡ እኔ የዲን እዉቀት የለኝም በማንበብ እና የሰሙትን በመተግበር ላይ አተከለራለሁ ...እና ማንኛዉም ነገር አንድ እርምጃ ያስፈልገዋል የብዙ ሰዉ ችግር ሶስት አራት እርምጃ ይራመዳል ሳያጣራ ከዛ ግብ ሳይመታ ይመለሳል ...እኔ የማምነዉ አንድ እርምጃ ካልሆነ ወደፊት ሳይሄዱ መለስ እርምጃዉ የተሳካ ከሆነ ቀኝን እግርህን ካስቀደሙ ግራህን አስተከትለህ ሁለት እርምጃ ላይ ትቆማለህ ከዛ ነገሮችን እያገናዘቡ መሄድ ነዉ...
#ከተሞክሮ

አንዲት ክርስቲያን ጎረቤታችን  የ7 አመት ልጇ አላት ለሊት አይተኛ ቀን ታዝሎ ይዉላል ስራዉ ማልቀስ ምግብ የሚበላዉ ትንሽ ለዛዉም ያስመልሰዋል እንደ እድሜ እኩየቹ አይጫወትም ብቸኛ ነዉ ... ይሄ ህመም የጀመረዉ ገና በ4 አመቱ ነዉ 3 አመት ያህል ተሰቃይቷል  ያልሄደችበት ፀበል የለም ሌላም ሀገር ሂዳለች ፡፡በፀበል መፍትሄ ሲያጡ ሌላ ሀገር ጠንቋይ ቤት ሄዱ አረንጓዴ እስስት አምጡ ብሏቸዉ አረንጓዴ እስስት ለማግኘት አራት ወር ፈጀ በግድ ተገኘ ጠንቋዩ በአረንጓዴ እስስት ሌላም  ጨምሮ አንገት ላይ የሚንጠለጠል ሰጠው ምንም ለዉጥ የለም...ከ3አመት ስቃይ ቡሀላ ሲጨንቃት ቁርአን ቅሩልኝ አለች...

#አላህ_ሆይ እንዳታስፍረኝ የቁርአንን ሀይልን ለነዚህ ክርስቲያኖች አሳያቸዉ ብየ ዱአ አደረኩ ...ከዛማ በስፒከር ሩቃ ከፈትኩ ሁለት ሁነን በቻልነዉ ቀራን ወላሂ 45 ደቂቃ ባልሞላ እንቅልፍ ወስዶት ላብ በላብ ሆነ ቁርአኑን ስንጨርስ ጩኾ ተነሳ በዛዉ ለቀቀዉ ከዛ ቀን ቡሀላ ታሞ አያቅም ይሄዉ እንቅልፍም ይወስደዋል እናቱም አታዝለዉ ምግብም መመገብ ጀመረ የሚያስመልሰዉ ቀረለት  ትምህርትም ተመዘገበ አልሀምዱሊላህ....እናት አባቱ አጥባቂ ክርስቲያን ነበሩ አሁን ግን ከምነግራችሁ በላይ ለሙስሊም ያለቸዉ አመለካከት ደስ የሚል ነዉ አላህ ሂድያ ይስጣቸዉ የቁርአንን ሀይል ቤተሰብ ዘመድ ልጁን ተሽሎ ሲያዩት ይገርማቸዉ ይደንቃቸዉ ይዟል፡፡

አክስቴ ክርስቲያን ነች ታማ ፀበል ብትመላለስ ምን ብትል ያልተሻላትን በ30 ደቂቃ ሩቃ በመቅራት በአላህ ፍቃድ እንዲሻላት አድርጊያለሁ

ከነዚህ ዉጭ  3 ሰዎች ጎረቤት ምናምን ሲታመሙ በአላህ እገዛ ተሳክቶሎኛል እናም እንደዚህ ልላችሁ ያሰብኩት ሩቃ ማድረግ ከባድ አይደለም መጀመሪያ ጀሊሉን አላህየን ከያዙ ምንም የሚያስቸግር የለም እናም እህት ወንድምህን እናት አባትህን ...እናት አባትሽን እህት ወንድምሽን ለሌላ ባዳ አሳልፋችሁ አትስጡ

----- ጂን ሲናገር  ሊዋሽም ላይዋሽም ስለሚቾል አንዳንዴ ሲናገር እዉነት ነዉ ብለን ከተናገረዉ ሰዉ ጋር ሂደን መጣላት አያስፈልግም፡፡

ከዚህ ርዕሱ ጋር ባይሄድም በፊት ክፍል ላይ ዘንግቼ ሳላስገባ የቀሁት ጉዳይ አሁን ያለቦታዉም ቢሆን ስለዚህ ጉዳይ ትንሽ ልበል...
በቅርብ አመታት በተለያየ ማህበራዊ ሚዲያ ወንድና ሴት ዚና ሲሰሩ ወይ በባል ወይ በሚስቱ ላይ ሲማግጥ  ተጣብቀዉ እያየን ነዉ፡፡ ይሄ ባልየዉ ሚስቱን ካላመናት ወይም ሚስት ባሏን ካላመነችዉ ጠንቋዮች ጋር ሂደዉ ሌላ ወንድ ጋር ከተኛች ወይም ሌላ ሴት ጋር ከተኛ እዛዉ እንዲጣበቅ ሰዉ እንዲያዋርደዉ ይሁን ብለዉ አስደግመዉ ሊሆን እንደሚችል አንዘንጋ...ካልሆነም ደግሞ ፈጣሪ እኛን ለማስተማር እነሱን ምሳሌም እያረገ ሊሆን ይችላል፡፡እናም ለትዳራቸዉ ታማኝ ያልሆኑ ሰዎች መጀመሪያ  ባለመተማመን ይጋባሉ ከዛ ይሄ ይፈጠራል፡፡
እናም ወይ የአላህ ቁጣ ነዉ ካልሆነ ድግምት ነዉ ...
ግን በተለይ በትዳር ላይ የሚሰሩ ሲህሮች በአሁን ዘመን ላይ በሰፊዉ ተንሰራፍቷል፡፡


  #በጂን_የተያዘ_ወይም_ሲህር_ወይ #በአይነጥላ_የተያዘ_ሰዉ_ወይም_አስታማሚዉ      
         
#ምን_ማድረግ_አለበት

      ኩን ፈየኩን ...አላህ ኩን ብሎት አላህ ሱወ በሲህር በጂን በአይነጥላ ሊፈትነን ይችላል ፡፡  ዱንያ የፈተና አለም ነች ለአላህ የትንኝ ክንፍ ያህል ቦታ የላትም ላለን ዱንያ ደስታን እናጣጥማለን ማለት አይደለም፡፡  ዱንያ በሀዘን ማቅ የተተበተበች ደስታ እንደመብረቅ ብልጭ ብሎ የሚጠፋበት የኑሮ መድረክ የፈተና መሸጋገሪያ ድልድይ ነች የጀነት መግቢያ የኸይር መሸመቻ የፈተና ማለፊያና መዉደቂያ የቁጥጥር ጣቢያ ነች፡፡  

  በርዚቃችን ትዳር እንዳናገባ ነገሮች እንዳይሳኩ ወዘተ ሲህር ድግምት  ከተደረገብን የአላህ ዉሳኔ ነዉ ፅናት ብርታት ጥንካሬ ያስፈልጋል ፡፡

አላህ (ሱ.ወ) የወሰነውን ነገር መደው የተቀበሉ  ነብዩ ሰዐወ ናቸዉ በሲህር ተሰቃይተዋል.....በተጨማሪ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ኢብራሂም የሚባል ልጅ በተወለደላቸው ጊዜ ከፍተኛ የሆነ የደስታ ስሜት ውስጥ ገብተው ነበር፡፡ ተሸክመውት ወደተለያዩ ሰሐቦች ቤት ይዘውት ይሄዳሉ፡፡ ለሰዎችም ልጇን ኢብራሂምን ተመልከቱት፡፡› ይሉ ነበር፡፡ ትንሹ ኢብራሂም አባት ለልጅ በእጅጉ በሚጓጓበት የህፃንነት ዕድሜ ጡት መጣያው አካባቢ ሞተ፡፡ ነብዩም (ሰ.ዐ.ወ) አለቀሱ ፡፡ እንባ የልብ እዝነት ውጤት ነውና የአላህን ውሳኔ ካለመውደድ አይቆጠርም፡፡ እርሳቸውም ዐይን ያለቅሳል፣ ቀልብ ያዝናል፣ ጌታችን የሚወደውን ነገር እንጂ አንልም፡፡

#ኢብራሂም_ሆይ!!!! ከኛ በመለየትህ አዝነናል፡፡” አሉ፡፡ ከዚያም ወደቤታችው በመግባት ለአላህ (ሱወ) እንዲህ አሉ፡- ‹‹ጥሪህ ሰምተን በደስታ ወዳንተ መጣን፡፡ መልካም ነገር ሁሉ በእጅህ ነው፡፡ መጥፎ ካንተ አይደለም፡፡” ብለዉ የጌታቸዉን ዉሳኔ ተቀበሉ...

መቼም የሀቢቡና ሙሀመድ ሰዐወ ታሪክ ታቃላችሁ
በእናታቸዉ ሆድ ውስጥ ሳለ ወላጅ አባቱን በሞት ተነጠቁ
ዕድሜያቸዉ ስድስት ሲሞላ ወላጅ እናታቸዉን ቀበሩ።
በስምንት ዓመታቸዉ በፍቅር ተንከባክበው ያሳደጓቸዉ አያቱን አይቀሬው ሞት ነጠቀው።

እንደ አይን ብሌናቸው የሚሳሱለት በማራኪ ስብዕናው ተረታ የትዳር አጋሩ ለመሆን የበቃችው ውድ ሚስቱ በአንድ ዓመት ውስጥ ተከታትለው ተለዩት።
  ከሁለት ዓመታት ዕድሜ በላይ ያልቆዩ ሁለት ወንድ ልጆቹን ሞት ቀጠፋቸው። በህፃናቱ ፈገግታ ደምቆ የነበረው ቤት የሀዘን ጥላ አጠላበት።
ከእርሱ ህልፈት በኋላ በስድስተኛው ወር በሞት ከተከተለችው ተናፋቂ ልጁ በስተቀር ሁሉም ሴቶች ልጆቹ ወደ መጪው ዓለም ተጓዙ።

የአባቱ ጥሪት የነበሩት አጎቱ ተገደሉ። መገደል ብቻ አይደለም የሰው ልጅ ያደርገዋል ተብሎ የማይታሰብ ጭራቃዊ ተግባር በአካላቸው ላይ ተፈፀመ። ሂንድ አስክሬኑን አስቀድዳ ጉበቱን በላችው።
1.4K viewsedited  02:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-21 21:14:26
የምታመንህ ነኝ
1.6K views18:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-21 07:19:28
ዛሬ ጁምአ ነዉ የሆነ ችግር ሲበዛ ወይ ነይተን ለሰዉ ነግረን ያልተሳካ ካለ እንደዚህ ልጅ ሁኔታ ለጀሊሉ ነግረዉን ያሳፍረን ይሆን??
እስኪ ለጀሊሉ እንደዚህ ልጅ ሁኔታ አድርገን እንገረዉ
Join
t.me/IslamisUniverstiy_public_group
  t.me/IslamisUniverstiy_public_group
1.9K viewsedited  04:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-21 01:16:33 ሀስቡነሏህ ወኒዕመል ወኪል ብለህ ጀምር እርግጠኛ ሁን አላህ አያሳፍርህም ፡፡ ችግሩ የኛ ኢማን ጥንካሬ መድከምና ተስፋ መቁረጥ ነዉ....ንብ አንድ ኪሎ ማር ለመስራት 400 km ትንቀሳቀሳለች ተስፋ አትቁርጥም ታሳካለች ታዳ አንቺ አንተ እናንተ ምን የሚያስፈራ አለ???ምን ተስፋ የሚያስቆርጥ አለ??
ለምን እህትህን ለአጂ ነብይ ወንድ አሳልፈህ ትሰጣለህ??? ለምን እኔ አልችልም ትላለህ/ትያለሽ

ሀስቡነሏህ ብለህ መጀመር አቅቶህ ነዉ ወይስ አላህ በኔ ተማመን እያለህ በአሏህ መተማመን ፈርተህ ነዉ
የጀአለሁ መኽረጃ የወሙጫ መንገድ አዘጋጃለሁ ያለህ ጀሊሉን እንዴት መተማመን አቃተህ
ሀስቡነሏህ ወኒዕመል ወኪል አላህን ይዘህ ሁሉም ነገር ቀላል ነዉ....አላህን ይዘን መፍራት አያስፈልግም


ብዙ ሩቃ ቤቶች ሩቃን ለቢዚነስ አርገዉታል ከ3,000 እስከ 20,000 ከዛም በላይ እየጠየቁ እኔ መጀመሪያ ላይ ብር ላይ ፎከስ የሚያደርጉ ሰዎች ንያቸዉ ብር እንጂ ከአላህ አጅር እናገኛለን ብለዉ ስለማይሆን እንደነዚህ ሩቃ ቦታዎች እንጃ ብቻ ምን እንደምል አላቅም...በሀዲስ ይበቃል አይበቃም ፊርቃ ስላለዉ የሚሻለዉ ወላሁ አዕለም ግን ብዙም አይዋጡልኝ

የሚሻለዉ በራስ ኮንፊደስ ተወከልቱ አለሏህ ብሎ መጀመር ነዉ አሏህ ቁርአኑን መፍትሄዉን ነግሮናል ነብዩ ሰዐወ አስተምረዉናል እናም በራሳችን መታገሉ ኸይር ነዉ፡፡

ማወቅ ያለብን ጂን በደም ስር በመርፌ ቀዳዳ መሹለክ የሚችል ዉሸታም ሰላቢ የማይጨበጥ ነዉ ፡፡ #ግን_ቁርአን_በሚቀራበት_ጊዜ_መላኢካ_ከታማሚዉ_ሰዉነት_እንዳይወጣ_ጠፍሮ_ይይዘዋል፡፡
ከዛ ቁርአን በሚቀራበት ጊዜ ለእሱ ቁርአኑ ሰይፍ ነዉ የሚሆንበት ይቆራርጠዋል ...ወላሂ ቶሎ ብለዉ ነዉ የሚወጡት ለምን ካልወጣም ሊገለዉ ይችላል ፡፡

ቁርአን ለሰዉ ልጅም ለጂንም ካመንበት መድሀኒት እርጋታ ከፈጣሪ ጋር ያለን ግንኙነት መጨመሪያ ነዉ....ጂኖች ያቃሉ ግን ተገደዉ ወደ ሰዉ ገላ ስለሚገቡ ለመዉጣት የላካቸዉ ሸይጧን ወይም ትልቁ ጂን ወይ የጎሳ አለቃ ጂኑ ቅጣቱ ከባድ ስለሚሆንባቸዉ ላለመዉጣት ይታገላሉ ግን የሚያሸንፈዉ ቁርአን ነዉ ተቃጥለዉ ተንገብግበዉ አይናቸዉ ጠፍቶ እግራቸዉ ተቆርጦ ድረስ ይለቃሉ ሲናገሩ ከሰማችሁ አይኔ ጠፋ እግሬ እጄ ተቆረጠ ይላሉ ቁርአን ሀይል ነዉ ...አልሀምዱሊላህ ጀሊሉ ለሰጠን መድሀኒት ሀይል ብርታት ቁርአን

#ቁርአን 77430 ቃላት እና 430740 ፊደላት አለዉ አሏህ ፈጣሪያችን በቁርአን በአንድ ፊደል 10 ሀሰና አለዉ ብሎናል እናም 430740 ብናሰላዉ
በወር ሶስቴ ብናከትም 12,922,200 ሀሰና ሲኖረዉ
በወር ሁለቴ ብናከትም 8,614,800 ሀሰና እናገኛለን
በወር አንዴ ብናከትም 4,307,400 ሀሰና እናገኛለን

ቁርኣን አጠቃላይ ገፁ 604 ነው። ከመጽሐፍ ቅዱስ አንፃር በመጠኑ በግማሽ ያንሳል። ነገርግን ላለፉት 1,400 ዓመታት በመቶዎች የሚቆጠሩ ሙፈሲሮች ማብራሪያውን ቢፅፉትም ፈፅሞ ሊጨርሱት አልቻሉም።
ለአብነት
ቁርጢቢ ➨ 21 ቅፅ 5509 ገፅ
ኢብን ከሲር ➨ 10 ቅፅ 6608 ገፅ
ጠበሪይ ➨ 12 ቅፅ 3000 ገፅ
በገዊ ➨ 4 ቅፅ 1487 ገፅ
ጀላለይን ➨ 1 ቅፅ 1378 ገፅ
ሰዕዲ ➨ 10 ቅፅ 6600 ገፅ
ቁጥብ ➨ 30 ቅፅ 4018 ገፅ

ይህ ሁሉ ተፍሲር ለ604 ገፅ መጽሐፍ የተፃፈ ቢሆንም ሁሉም የሚችሉትን ያህል አብራሩት እንጅ አንዳቸውም አሟልተው ፅፈው አልጨረሱትም።

ከዚህ በተጨማሪ ቁርኣን በታሪክ፣ በህክምና፣ በጂኦግራፊ፣ በጠፈር ምርምርና በተለያዩ ዝርፎች የተጠና ሲሆን የተወሰነውን ቢያረጋግጡትም ገና ብዙ ያልተደረሱባቸው ምርምሮችን ይዟል።

ይህ ለሚያስተነትን ሰው በእርግጥ ተዓምር ነው።
«ይህ ቁርአን አንቀፆቹ በጥንካሬ የተሰካኩ ከዚያም የተዘረዘሩ የሆነ መጽሐፍ ነው። ጥበበኛ ውስጠ ዐዋቂ ከሆነው ዘንድ የተወረደ ነው።»
(ሑድ 1)
እናም እኛ እንደ ቀልድ የያዝነዉ የአላህ ቃል ቁርአን ማስተንተን አልቻልንም እንጂ ሀይላችን ቅዋችን ከህመም መሻሪያችን ነዉ እናም ሀስቡነሏህ ወኒዕመል ወኪል ብለን እንጀምር

ማስጠንቀቂያ
በፊት ለጅን የሚገብሩ በግ ፍየል ዶሮ በሬ ላም ወዘተ የሚያርዱ.... የሚገበረዉ ለብዙ ጃሂል ጂን ስለሆነ መጀመሪያ ማስቶበት ወደ አላህ እንዲመለሱ ማድረግ አለብን፡፡  ማድማቱን ማረዱን ሲያቆሙ ሀይለኛ ህመም ጂኑ ይልካል  ሀኪም ቤት ሲሄዱ ጂኑ አዉቆ እንደ ካንሰር ኩላሊት ምናምን ያስብላል


የዛን ጊዜ ካንሰር ኩላሊት ደም ግፊት ምናምን ከተባለ አደራ መድሀኒት አይጀሞሩ የካንሰርም በጨረር የሚሰራ አለ ባይሰሩ ጥሩ ነዉ  ለምን ጅኑ ደም ሲቆምበት እንዲሞቱ ይፈልግና ወደ ልጅ ወይ ልጅ ልጅ ይተላለፋል...የዚህ ጊዜ ጥሩ ሩቃ የሚቀራ ተፈልጎ ማስለቀቅ ነዉ መፍትሄው፡፡ግን ይሄን ጂን ለማስለቀቅ ቢያንስ 2ወር ሊፈጅ ይችላል፡፡ ነጬ በላ/ጥቁር በላ/ራሄሎ/አንበሴ/ወንዘኛዉ/ወዘተ ለጂን በሚያርዱበት ጊዜ ያለማካበድ ከ30 በላይ የሚሆኑ ናቸዉ የሚገበርላቸዉ እናም ማረድ ሲያቆሙ ያሁሉ ነዉ ቂም ይዞ እስከ ሞት የሚደርሽ ህመም ካንሰር ደም ግፊት የሚያስብሉት  ...ግን ለመሻር እንደ ታማሜዉ ቀልብ ይወሰናል፡፡ ትክክለኛ ተዉበት ከሆነ 3ቀን ለራሱ በቂ ነዉ፡፡
ነገር ግን አደራ አደራ!!! ሳይቶብቱ ሩቃ እንዳይጀምሩ ለምን ዋናዉ ቀልብ ነዉ ቀልባቸዉ ማድማት ለጂን ማረድ ከሆነ  ሩቃዉ በጣጣም አድካሚ ነዉ የሚሆነዉ ካልቶበቱ ሰዉነታቸዉን በጣም የሚያስጠላ ሽታ ሊሸቱ ይችላሉ፡፡ እናም ማስቶበቱ ላይ ትኩረት ማድረጉ ነዉ ...
አንዲት ሴትየ ሲታመሙ ካንሰር ተብለዉ ልጆቻቸዉ ቁርአን በተከታታይ ቀን ሲያስቀሩ የዛር ጂኖቹ ይለቃሉ መልሰዉ ከሁለት ከሶስት ቀን ቡሀላ ይመለሳሉ ከዛ ለምን ትመለሳላችሁ ብሎ ሲጠየቅ
ወላሂ እኛ እንወጣለን መጀመሪያ እሷን አስቶብታት ስንወጣ መልሳ እየጠራችን ተቸገርን ለምን እሷን ሳታስቶብት በቁርአን ታቃጥለናለህ ብሎ ነበር የመለሰዉ ጂኑ

አንዷ እናታችን በፊት ለጂን ያርዱ ነበር ሁለት ወር ያህል ታመዉ በአላህ ፍቃድ በሩቃ ጅኖቹ ለቀቁ.,,ሴትየዋ ግን አልሀምዱሊላህ በአላህ ቃል ተሻለኝ አላሉም....እኔን ያመመኝ እኮ ባለማድማቴ ነዉ የሚደማበት ቦታ ልሂድ ብለዉ ሲሄዱ የአሏህ ስራ የሚሄዱበት መኪና ሌላ መኪና ጋር ተጋጭቶ ከተሳፋሪዉ ሌሎቹ ሲተርፉ እሳቸዉ ግን ሞቱ ኢናሊላህ ወኢኒ ኢለይሂ ራጂኡን አሟሟታቸዉ አላማረም....አላህ የመቶበቻ ጊዜ ሰጥቷቸዉ አልተጠቀሙበትም

   ትክክለኛ ተዉበት አድርገዉ ማድማቱን ሲያቆሙ ህመሙ ቁስለቱና ጂኑ ደማቸዉን ስለሚመጣቸዉ ደማቸዉ ይወርዳል ደም ግፊት ወይም ደም ብዛት ይባላሉ፡፡  በተጨማሪም የማህፀን ካንሰር ነዉ የመባል ቻንሱ ሰፊ ነዉ..ሰዉነታቸዉ ከበፊቱ በበለጠ መወፈር ወይም መክሳት ...ሆዳቸዉ እጃቸዉ አካባቢ ለብቻዉ ማበጥ ምልክት ያሳያል


የምናቃቸዉ ደም የሚያደሙ ለጅን የሚገብሩ እናት አባቶች ካሉን በተጨማሪ አያቶቻችን ካሉ ብዙ የዲነል ኢስላም እዉቀት ስለሌላቸዉ በህይወት ካሉ  ይሄን ጊዜ እንዲቶቡ ማድረጉ ኸይር ጥሩ ነዉ ካልሆነ አሟሟታቸዉ እንደማያምር እወቁ ካንሰር ምናምን ሆነ ተብሎ ነዉ ህይወታቸዉ የሚያልፈዉ፡፡

ህመሙ በሽታዉ በሩቃ ለጅን ከሚገብረዉ አካል ካልተወገደ የዛር ጂን ቂመኛ ነዉ  ወደ ልጅ ወይም ወደ ልጅ ልጅ ይተላለፋል ስለሆነም እንደ ቀላል ባናየዉ ጥሩ ነዉ፡፡


#የመጨረሻዉ_ክፍል_ይቀጥላል.....
4any cmt
T.me/Aisuu_bot T.me/Aisuu_bot
1.7K viewsedited  22:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-21 01:15:05 #ሲህር_ጂን_አይነጥላን_ራስን_በራስ_ማከም
                  አሚር ሰይድ

           
          
                 #ክፍል አስራ አራት




የሲህር(ድግምት) የቡዳ(አይንናስ ጂን ህክምናዎች


ነብዩ ሰዐወ በሀዲሳቸዉ አላህ እኔን በጠረጠራችሁኝ በኩል ታገኙኛላችሁ ብሏል እናም ሲህር አለብን ብለን ባንጠራጠር ራሳችን ባናሳምን ጥሩ ነዉ ምልክቱ እስካልታየብን ድረስ
...በተጨማሪ በዉዱዕ የምንቀሳበቀስ ..የጠዋት ማታ ዚክር የምናደርግ...
>> አላህ የከከለልንን የምንከለከል ከሆነ 
>> ዚናን ሙዚቃን ዉሸትን ስርቆት የየቲም ሀቅ የሰዉ ሀቅ የሚዲያ አጠቃቀማችን ለሀላል ነገር ብቻ ከሆነ ..
>> ከትልቅም ከትንሽም ወንጀል የራቅን ከሆን በአላህ ፍቃድ ወደኛ ማንም መጥፎ ሰዉ ቢያስብ አይነካንም
ከነካንም በዲናችን ጠንካራ ከሆን ዚክር ቁርአን የምናበዛ ከሆነ እንደተያዝን ሳናቀዉ በራሱ ጊዜ ይለቀናል፡፡

ግን ከላይ የጠቀስኳቸዉ በትልቅ ወይ በችንሽ ወንጀል በከፊልም በሙሉም የተዘፈቅን ከሆነ በተጨማሪ እስኪ ወደ ሆላ 3 ወይ 4አመታት አስታዉሱ የነበራችሁን ጥንካሬ
☞ አሁን ግን የኢማን መንሸራተት ካለባችሁ..
☞ ትዳር ሲመጣ ጭንቅጭ ጭንቅ የሚላችሁ
☞ከማግባት ይልቅ ለማበላሸት የሚቀናችሁ..ከዛ ካበላሻችሁ ቡሀላ የሚቆጫችሁ ከሆነ
☞ አጭቴችሁ ምነዉ አጭቼ ባልነበር ከአጨሁት ይሄኛዉ ይሻለኝ ነበር ወይም ያችኛዋ ትሻለኝ ነበር እያለ ሸይጧን ለማበላሸት የሚወሰዉሳችሁ ከሆነ
☞ ቁርአን ሂፍዝ እስከ መጥፋት..
☞ ቁርአን ስቀሩ ስታዳምጩ የሚጨንቃችሁ የሚያልባችሁ ካለ ሩቃ ቢደረግባችሁ ጥሩ ነዉ፡፡


ሩቃ ሁለት ጥቅም አለዉ
#የመጀመሪያዉ በኛ ላይ ሲህር ወይ ድግምት ወይ አይነጥላ ጅን ካለ ይለቃል
#ሁለተኛ ጥቅሙ እኛ ሁሉም ከሌለብን ቀልባችን ይጀደዳል በቁርአን ጥንካሬ ያገኛል፡፡

  በራስ ሩቃ ማድረግ በጣም በላጩ ነዉ
ሩቃ ሲባል ከባድ አድርገን አንያዘዉ ..ሩቃ በቀላል ቋንቋ ከአላህ ጋር ያለን ግንኙነትን ማስተካከል በዚክር በቁርአን ልብን ማርጠብ ማለት ነዉ
የጠዋት የማታ ዚክሮችን ማለት
ሲተኙ ሱረቱል ናስ ፈለቅ አሀድን ሶስት ሶስቴ መቅራት አያተል ኩርሲን መቅራት እነዚህን ስንቀራ ዉሀ በሀይላንድ ይዘን ዉሀዉ ላይ መቅራት ከዛ የሩቃ ዉሀ ሆነ ማለት ነዉ...የሩቃ ዉሀ መጠጣት ከተቻለም የወይራ ዘይት ጥቁር አዝሙድ ዘይት ዉሀዉ ላይ ጠብ ጠብ አድርጎ መጨመር ነዉ
ቁርአንን በቻልነዉ አጋጣሚ በቁርአን መቅራት..
ዚክሮችን በስራ ቦታ በትምህርት ቤት ታክሲ ላይ ሲንቀሳቀሱ ዚክሮችን ማድረግ አላህን ማስታወስ ነዉ...
#ነብዩላህ_የኑስ ዐ.ሰ ብዙ መልካም ስራ አልነበራቸዉም ጥፋት ባጠፉ ጊዜ አላህ ሱ.ወ በዓሳ ሆድ ዉስጥ ጣላቸዉ ከዚያ ያወጣቸዉ ያደረጉት ተስቢህ የአላህ ዉዳሴ ነዉ፡፡
አላህ ሱወ እንዲህ ይላል
እርሱ ለጌታዉ ከአወዳሾች ባልሆነ ኑሮ እስከሚቀሰቀስበት ቀን ድረስ በሆዱ ዉስጥ በቆየ ነበር
(አል ሷፋት 143-144)

እናም አላህን ማዉሳት መቶበት ለሁሉም መፍትሄ ነዉ
በቁርአን ዉስጥ በደረጃ ትልቅ አንቀፅ አያተል ኩርሲይ ነዉ በአንድ አንቀፅ ዉስጥ ስድስት ያህል መልካም የአላህ ስሞች እናገኛለን...አያተል ኩርሲን ባገኝንበት አጋጣሚ መቅራት


ወንጀል ላይ ካለን ዚና የምንሰራ ሙዚቃ የምናዳምጥ ትንሽም ትልቅም ወንጀል ላይ ካለን ከዛ መታቀብ
የማይጠቅሙ የማይጎዱ ጓደኞችን መቀነስ
በtv በስፒከር ቁርአን መክፈት ጆሯችን ጎን አድርገን የተለያዩ የሩቃ አንቀፆችን ቁርአኖችን መቅራት ነዉ...በአላህ ፍቃድ ጂኑ ሳይናገር ሳይለፈልፍ በራሱ ጊዜ እየተወገደ ይሄዳል፡፡
ከበፊቱ ለዉጥ ካለን እንቅልፍ እምቢ የሚለን ከሆነ እንቅልፍ መዉሰድ ከጀመረን መጥፎ ህልሞች እያየን በፊት ከነበረ ከዛ ቡሀላ መጥፎ ህልሞች ከራቁልን ..ሙዚቃ ካስጠላን ከዚና ቱብት ካደረግን ወይም ከዉሸት ከመጥፎ ጓደኛ ከራቅን በራሳችን ሩቃ ተሳክቶልናል ማለት ነዉ ...በዚሁ ኢማንን እያጠነከሩ መሄድ ነዉ

ጂን መቷቾሁ ከሆነ ወይም በምቀኛ ሰዉ ሲህር ድግምት ተደርጎባችሁ ከሆነ እኔ ራሴን በራሴ ሩቃ ማድረግ አይሆንልኝም ብላችሁ ካሰባችሁ...ሩቃ የሚያደርግላችሁ ፈልጋችሁ በቁርአን ሀይል የዛን ጊዜ መናገር ይጀምራል በአላህ ፍቃድ ይለቃል፡፡

ከሁሉም ግራ የሚገባዉ ነገር ማን ጋር ሩቃ እንጀምር የሚለዉ የብዙ ሰዉ ጥያቄ ነዉ ለምን ቢባል አንደንድ ሩቃ እናደርጋለን የሚል በሩቃ ስም ሀራም የሚሰሩ ሴቶች ጋር የሚተሻሹ በተጨማሪም ሳይታመሙ ታመምን የሚሉ አሉ እዛ ሂደዉ መተሻሸት የሚፈልጉም ሴቶች እንዳሉ ልናወቅ ይገባል ..እናም ትክክለኞቹ ማን ናቸዉ??ግራ የሚያጋባ ነዉ

  ግን እኔ የምለዉ ቆይ እስኪ እቤት እናት አባት እህት ወንድም ሲታመም ምን የሚያስፈራ አለ?? የአላህ ቃል በስፒከር ከፍቶ በተከታታይ ቀናቶች መቅራት ነዉ ብዙዉ በአንድ ቀን ይለቃል እናም እኔም አንተም አንቺም እሱም እሷም ማላቀቅ እንችላለን መጀመሪያ በአላህ መተማመን አንተን ይዤ በአንተዉ ቃል ቁርአን አድነዋለሁ ብሎ ነይቶ መነሳት ነዉ እናም ሩቃ ቤት ከመዉሰድ መጀመሪያ በራስ መታገል ይበልጣል፡፡

የተለያዩ የሩቃ እወቀቶች መቅሰምና መፅሀፎችን ማንበብ ለቤተሰብህ ለጓደኛህ መሆን ይቻላል

ሴት የዲን እህትሽ ስትታም ለምን ለአጂ ነቢይ ወንድ አሳልፈሽ ትሰጫለሽ?? ሀስቢየሏሁ ወኒዕመል ወኪል ብለሽ አንቺዉ ቁርአን ቂሪባት

እህትህ ስትታመም ለምን ወንድ ሩቃ የሚያደርግ ትፈልጋለህ??
ሀስቡነሏህ ወኒዕመል ወኪል ብለህ ጀምረዉ  ...ሀስቡነሏህ ብለህ ከጀመርክ ከጀመርሽ ሰበብ አድርስ አላህ ያግዘሀል ያግዝሻል ግን ያለስበብ ወደፊት ያለርምጃ የሚሆን አይደለም ሰበብ ግዴታ ነዉ

ሀስቡነላህ ወኒዕመል-ወኪል”
ነቢዩ ኢብራሂም (ዐ.ሰ) ወደ እሳት በተወረወሩ ጊዜ የተናገሯት ቃል ነች፡፡
ነብዩ ሙሳ (ዐ.ሰ) ፊርአውንን በመሸሽ ላይ እያሉ በሱ ያመኑ ሰዎች “እነ ፊርዐውን ደረሱብን!” ባሏቸው ጊዜ ይህችኑ ቃል ተናግረዋል፡፡
የአላህ መልእክተኛም (ሰዐወ ሰዎች "በኡሀድ ጦርነት ሰዎች እናንተን ለማጥቃት ተሰባስበዋልና ፍሯቸው ባሏቸው ጊዜ ሀስቡነሏህ ወኒዕመል ወኪል ይህችን ቃል ብለዋል፡፡
እናም ሀስቡነሏህ ወኒዕመል ወኪል ብለን ጀምረን ፈጣሪ አያሳፍረንም እርግጠኛ ሁኑ
  እናታችን ሀጀር ብቻዋን በዛ በርሀ  ለኢስማኢል ዉሀ ጠምቶት ሲያለቅስ ቁማ አልተመለከተችም ሰባት ጊዜ ስትዞር ነዉ  ጂብሪል ከሰማይ በመውረድ  በክንፉ እግር ስር በመጫር ዘምዘም ዉሀ እንዲፈልቅ ያደረገዉ
መርየም በዛ በምጥ ተሰቃይታ ባለችበት ጊዜ አላህ የሚበላ የሰጣት እኮ በጅብሪል አማካኝነት የተምሩን ዛፍ አወዛዉዢዉ ሲላት ስታወዛዉዘዉ ነዉ የሚበላ ያገኘችዉ...እናም አላህ የሚያግዘን ከኛ ትንሽ ሰበብ ይፈልጋል ሀስቡነሏህ ብለን መጀመር ነዉ
1.5K viewsedited  22:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-20 21:19:23
ፑቲን የሰላሐዲን አል አዩቢ አፀደ ገላ ያረፈበት የመቃብር ሥፍራ ላይ ዓይኑን ተክሎ በትኩረት ይመለከተው ይዟል። “ተነስና ግጠመን! ተመልሰን መጥተናል” የሚል ይመስል፡፡

ይህ ክስተት ታሪክን የኋሊት መለስ ብዬ እንድንቃኝ አደረገኝ።

★ የፈረንሣይ ወታደሮች በአንደኛው የዓለም ጦርነት ሻምን ተቆጣጥረው ወደከተማዋ በዘለቁ ጊዜ ጄኔራል ጉሩፎራ የሰላሐዲን አል አዩቢን ቀብር በእግሩ ረገጠና “ሰላሐዲን ሆይ! ከሞትክበት ተነስ እነሆ ዛሬ ተመልሰን መጥተናል በበይተል መቅዲስ ስር መንፈላሰስ ይዘናል” በማለት ፎከረ፡፡

★ የመስቀል ጦረኞች አንደሉስ ገብተው ሙስሊሞችን ካረዱ በኋላ የመስቀላዊያኑ መሪ አልፎንሶ የሐጂብ አል-መንሱር መቃብር ላይ ድንኳን ተክሎ የወርቅ አልጋ ላይ ተደገፈ። ከሚስቱ ጋር ለሳምንታት ያህል ተኛበት። እንዲህም አለ "ዛሬ የሙስሊሞችን ሐገር ተቆጣጠርኩ። መሻኢኾቻቸውን ስገድል ከፊቴ የቆመ ማንም አልነበረም። እነሆ በትልቁ ጦር መሪያቸው ቀብር ላይ ተኝቻለሁ" አለ።
እኛ ነን ታሪካችንን የዘነጋነው እነርሱ ፈፅሞ አልረሱትም።

★ የግሪክ ወታደሮች ቡርሳ ከተማን ሲቆጣጠሩ የጦር አዛዣቸው ሶፍሎክስ የኦቶማን ኢምፓየር መስራች ወደሆነው ዑስማን አልጋዚ መቃብር አመራ። ቀብሩን እየረገጠ ጮኸ “የትልቁ ጥምጣሙ ባለቤት ሆይ ተነስ! አንተ ዑስማን ሆይ ንቃ! የልጅ ልጆችህን ሁኔታ ተመልከት! የመሰረትከውን ኢስላማዊ ኸላፋ አፈራርሰነዋል። ሀገሩን በታትነነዋል። አቅም ካለህ ንቃና ተፋለመን" አለ።

በአላህ እምላለሁ የእነዚህ መቃብር ባለቤቶች ተነስተው ቢተነፍሱ አንዳቸውም በሕይወት ባልተረፉ።


Join
t.me/IslamisUniverstiy_public_group
  t.me/IslamisUniverstiy_public_group
1.7K viewsedited  18:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-20 06:31:40 ከእነሱ አንዳንድ የምሰማዉም አለ....እስኪ በመጀመሪያ የራሳችንን እንወቅ ሙስሊም መስለዉ የሚሸዉዱት  ጥንቃቄ እናድርግ የሌላዉ ይደርሳል...ብቻ በፀበል
ይለቀናል ባላችሁ ሂዳችሁ የብስ ህመም ጨምራችሁ እንዳትመጡ ....
እነሸህ ተብየ ጫት ቅመዉ ወይ በዛር የሚያስለቅቁ ይሄ በቀላል ቋንቋ 90% እርግጠኛ ሁኑ ለጅን ይገብራሉ ትልቁ ጉልበተኛዉ ጂን ለትንሹ ቀላል ነዉ ...ሲያጎራ ሲጮሁ ሰምታችሁ ከሆነ በጣም ለአቅል ይከብዳል ሲለፈልፉ በእነሱ አድርጎ ይወጣል፡፡
አንዳንዴ ዛር ያለበት እያጨበጨበ እየጨፈረ ሲያስለቅቅ ያየሁት አሉ ጅኑ አጨብጭብ ጨፍር ብሎት ወላሂ በአይኔ ያየሁት ነዉ፡፡ ግን ይሄ ለጅን ግብር ነዉ ተመልሶ ይመጣል ወይ ሌላ የቤተሰብ አባል ወይም ልጅን ይይዛል፡፡
የሀሉም መፍትሄ ቁርአን ብቻ


    አይንናስ(ቡዳ) ..ሲህር..ጂን ብዙዎቻችን ላይ ያለ ይመስለኛል ለምን ብዙሀን ሙስሊሞች ከዲናችን  የተዘናጋን ስለሆነ ራሳችንን ቆም ብለን ብናይ  ጥሩ ነው.....ብዙዎቻችን
የጠዋት ማታ ዚክር ማድረግ አቁመናል
ቁርአን ስልክ ከመጣ ቡሀላ የምንቀራ በጣት የምንቆጠር ነን ሁሉም በስልኩ ቁርአን አዝካር አለ ያንን ለመቅራት ነይቶ ስልኩን ሲነካካ ወደ ማህበራዊ ሚዲያላይ ነዉ የሚወስደን፡፡ ግን አስተዉለናል?? በፊት ስልክ ሳይመጣ እኮ ለቁርአን ያለን ፍቅር ዚክር ለማድረግ ያለንን ጉጉት የተለየ ነበር ግን አሁን ማን ነዉ ቁርአንን አክብሮ ገልጦ የሚቀራዉ??የሚሻለዉ በስልክ ቁርአን መቅራት ብናቆም የተሻለ ነዉ እናም
የኛ ከቁርአን መዘናጋት ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ማሳለፍ ከዲን የመዘናጋት ስለሆነ ራሳችንን ማኔጅ ብናደርግ ጥሩ ነዉ
በማህበራዊ ሚዲያ በTG..Whatsap..facebok..instgram ወዘተ የምናደርገዉ profile pictur ፎቶ ለአይን ናስ(ቡዳ) መበላት ምክንያት ሊሆን ይችላል፡፡
ለምን ጀሊሉ ሲፈጥር ማስጠሌ ብሎ የፈጠረዉ የለም ግን የሰዉ አይን የፈለገዉን ቆንጆ የፈለገዉን ማስጠሌ አድርጎ ይስላል፡፡ profile ስታደርጉ እራሱን ወይ እራሷን እንደ ማስጠሌ የምታይ ዉይ ሲያምር ወይም ዉይ ስታምር ሊሉ ይችላሉ እናም profile ከማድረግ እንጠንቀቅ

በtiktok ላይ video የምፓስቱም የሰዉ አይን ሰለባ ስለምትሆኑ መጠንቀቁ አይጎዳም...እስኪ እኔ ብዙም ግንዛቤዉ የለኝም በtiktok የሚታወቁ ሰዎች ትዳር አላቸዉ የላቸዉም? ካላገቡ መቼም የሚታዩት ቆንጆ ናቸዉ እንዴት አላገቡም?
መጀመሪያ በሚዲያን የቀረበ ራሱን ጨረታ ያወጣ በሀራጅ ተከስሮ ነዉ የሚሸጠዉ ጨረታ እቃ ያሸነፈ ነዉ በሀራጅ ይገዛል ኦዲት ሲደረግ ይወድቃል
በመቀጠል ግን የሰዉ አይንም(ቡዳ) ችግር ሊሆን ይችላል
ያለቅጥ የተካበደ ሰርግ ብራይድ ማድረግ በሰዉ አይን የመበላት አቅሙ ሰፊ ነዉ ለምን በዚህ በኑሮ ዉድነት ባለበት ዘመን የሚበላ የሚጠጣ ቤት ኪራይ መክፈል በአቃቃተበት ዘመን ያለቅጥ ደስታ በደሀ እምባ መቀለድ ነዉ የእናንተን ሰርግ ደሀ ሲያየዉ ወይ የበላችሁበት ወይ የጠጣችሁበት ምግብ ላይ ወይ የለበሳችሁት ልብስ ላይ አይኑ ያርፋል እናም የተቸገረ ሰዉ ቀልብ አይን ከባድ ነዉ ፡፡
በተጨማሪ በዚህ ወንዱ ብር ማስተዳደሪያ ሴት ደግሞ ባል ባጣችበት ዘመን በሚዲያ ሰርጋችሁ ተካብዶ ሲያዩት ወንዱም ወይኔ ትንሽ ኑሮኝ በነበር ሴቷም እድለኛ  ነች የሚያምር ባል አግብታለች ባይባል ጥሩ ነዉ የሰዉ አይን ከባድ ነው፡፡

የተወራለት በሚዲያ የታዩ ሰርጎች ብዙዎች ፍች ተፈጥሮ ደብቁኝ ደብቁኝ እያሉ ነዉ እናም ሁሉም በልክ ይሁን

ልጅ ሲወልዱ በደስታ prpfile pictur ማድረግ ይሄ ደግሞ በጣም ከባድ ነዉ ልጅ ያጣ ያላገባ ባለበት ዘመን ማሻ አላህ ሳይሆን አይኑ አፍንጫዉ መልኩ እናቱን ወይስ አባቱን በሚባልበት ዘመን profile ባይደረግ ባይ ነኝ፡፡

ከሰዎች የተለየ ልብሶችን መልበስ እና ቀን በቀን መቀያየር ይሄም ልብስ ያጡ አይኖች ላይ ትኩረት መግባት ነዉ ፡፡ ዱንያ ነዉ መብላት መጠጣት መልበስ ነዉ ማለት ቡሀላ ምነዉ ባልበላሁ ባልጠጣሁ ባለበስኩ ከማለት ሁሉን በልክ ማድረግ እና በዚክር በቁርአን መንቀሳቀስ ነዉ

   በሰዉ ህይወት ቀንታችሁ በማወቅም ባለማወቅም ያሰራችሁ ካላችሁ ጉዳቱ ለተደረገበትም ለእናንተም ጭምር መሆኑን አትዘንጉ የተዉበት ጊዜዉ ገና ነዉ ወደአላህ እንመለስ ...እኛ የምናምፀዉ በወንጀል ድንበር የምናልፍበት ጌታችን ቅርብ ሁኖ እያየን እንደሆነ አንዘንጋ....
ጌታችን አሏህ ሱወ በተከበረ ቃሉ እንዲህ ይለናል
“ባሮቼም ከእኔ በጠየቁህ ጊዜ (እንዲህ በላቸው) እኔ ቅርብ ነኝ፣ የለማኝን ፀሎት በለመነኝ ጊዜ እቀበለዋለሁ፣ ስለዚህ ለኔ ይታዘዙ፣ በኔም ይመኑ፤ እነሱ ለምመሩ፡፡ ይከጀላልና፡፡” (አል-በቀራህ፡ 186)

ታዳ ለምን እኛ የሰዉንም የራሳችንን ህይወት ለማበላሸት ደጋሚዎች ደብተራዎች ጠንቋይ ቤቶች እንሄዳለን??
የምንመቀዉን ሰዉ የሰጠዉ አላህ ለምን ለእኛስ ስጠን ብለን ወደ ጠንቋይ ከመሄድ ወደ ጀሊሉ እጃችንን አንዘረጋም??

በሐዲሥ አልቁድሲይ እንደተዘገበው አላህ (ሱ.ወ) እንዲህ ብሏል፡- የሰው ልጅና አጋንት በሚገርም ሁኔታ ውስጥ ነው ያሉት፡፡ እፈጥራለሁ  የሚመለከው ሌላ ነው፡፡ ሲሳይ እሰጣቸዋለሁ የሚመሰገነው ሌላ ነው:: መልካም ነገር ሁሉ ከኔ ወደ ባሮቼ ይወርዳል፤ የነሱ መጥፎ ነገር ወደኔ ይወጣል፡፡ ከነርሱ የተብቃቃሁ ሆኜ ሳለ በእዝነቴ ወደነርሱ እወደዳለሁ፡፡ እነርሱ ግን ከኔ ፈላጊ ድሆች ሆነው ሳሉ ወንጀል በመሥራት በኔ ለመጠላት ይሠራሉ፡፡ ለኔ ቅርብ የሆኑት እኔን የሚያወሱት ናቸው፡፡ እኔ   የምወዳቸው እኔን የሚታዘቡት ናቸው፡፡ ወንጀል የሚሠሩትን ከእዝነቱ ተስፋ እንዲቆርጡ አላደርጋቸውም፡፡ በተዉባ ወደኔ የሚመለሱትን እኔ ወዳጃቸው ነኝ፡፡ ቢያምፁም አካሚያቸው እኔ ነኝ፡፡ በችግርና መከራ የምፈትናቸው ከነውር ላፀዳቸው ነው፡፡ ተውባ አድርጎ ወደኔ የሚመለስን ሰው ገና ሩቅ እያለ እቀበለዋለሁ፡፡ ከኔ ዞር ብሎ የሄደውን በቅርብ ሆኜ እጠራዋለሁ፡፡ ከኔ ውጭ ሌላ አምላክ አለህ እንዴ ወዴት ነው የምትሄደው?› እለዋለሁ፡፡
በተጨማሪ

አላህ ለነብዩ ዳወድ እንዲህ አለ፡- ዳውድ ሆይ! ለኔ ጀርባቸውን የሰጡ ሰዎች (ወደኔ በመመለሳቸውና ተፀፅተው በመምጣታቸው) ለነርሱ ያለኝን ጉጉት ቢያውቁ ኖሮ ለኔ ከሚኖራቸው ጉጉት የተነሳ በቀለጡ ነበር፡፡ ዳውድ ሆይ! ይህ ለኔ ጀርባቸውን ለሰጡ ሰዎች ያለኝ ፍላጎት ነው፡፡ ፊታቸውን ወደኔ ላዞሩ ሰዎች እንዴት የሚሆን ይመስልሀል?
አላህ እንዲህ እያለ ይወቅሰናል
ለነዚያ ለአመኑት ለአላህ ተግሳፅና ከቁርአንም ለወረደዉ ልቦቻቸዉ ሊፈሩ ጊዜዉ አልቀረበምን??
አላህ እየወደደን ወደኔ ቅረቡ እያለ ይለምናል እኮ
እናም ያለፈዉ ስህተት ከነበርን ቶብተን ወደ አላህ እንመለስ ያስደረግንም ካለን በሰዉ ህይወት አንጫወት ላንጠቀም ነገር ሲህሩ ድግምቱ እንዲፈታ እንዲቆም ማድረግ አለብን፡፡
ህሊና ላለዉ ሰዉ  ሲህር አስደርጎ የተደረገበት ሰዉ ሲሰቃይ ሲቸገር ሲታመም እንዴት አቅላችን ይሸከመዋል??
እንዴት ሰዉ እንዳያገባ ተደርገ የእሱ ወይ እሷ አግብቶ መዉለድ እንዴት እኛን ሊያናድደን ይችላል??ብቻ አሁንም የተዉበት በሩ ክፍት ነዉ ወደ አላህ እንመለስ


#ክፍል
ይቀጥላል.....


አስተያየት መስጠት ለሚፈልጉ
T.me/Aisuu_bot

ለተለያዩ የዲን እዉቀቶች ይቀላቀሉ
Join
t.me/IslamisUniverstiy_public_group
 
1.8K viewsedited  03:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ