Get Mystery Box with random crypto!

ሁሌ አዲስ ሚዲያ (Hule Addis Media)

የቴሌግራም ቻናል አርማ hulaadiss — ሁሌ አዲስ ሚዲያ (Hule Addis Media)
የቴሌግራም ቻናል አርማ hulaadiss — ሁሌ አዲስ ሚዲያ (Hule Addis Media)
የሰርጥ አድራሻ: @hulaadiss
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 3.80K
የሰርጥ መግለጫ

ትክክለኛዉ የሁሌ አዲስ ሚዲያ ገፆች
Facebook : bit.ly/42rUuKj
Telegram: bit.ly/3NBQbro
YouTube : bit.ly/3p7kj3N
Twitter : bit.ly/3NVMRrB
Website : bit.ly/3ntuxuZ
ለጥቆማ ና አስተያየት እንዲሁም ለማስታወቂያ ስራ ተከታዮን አድራሻ ይጠቀሙ
bit.ly/3VMy7x7 ወይም 251939758767

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-08-30 11:51:05
መንግስት የ2015 ዓ.ም የዘመን መለወጫ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለሚያከናውናቸው ተግባራት  አምስቱ የጳጉሜ ቀናት በተለያዩ ሁነቶች ታስበው እንደሚውሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ።

እነዚህ አምስቱ ቀናት ሲታሰብ

፦ጳጉሜ 1 የበጎ ፈቃድ ቀን

፦ጳጉሜ 2 የአምራችነት ቀን

፦ጳጉሜ 3 የሰላም ቀን

፦ጳጉሜ 4 የአገልጋይነት ቀን እና

፦ጳጉሜ 5 የአንድነት ቀን ሆኖ ታስቦ ይውላል፡፡

ለወቅታዊ እና ለፈጣን መረጃዎች የሁሌ አዲስ ሚዲያ የማህበራዊ ሚዲያዎችን ይቀላቀሉ።

Facebook : https://www.facebook.com/Huleadissmedia/
Telegram : https://t.me/Hulaadiss
YouTube Channel
https://www.youtube.com/channel/UCk934znIu60LV3czcIVZ9Bg
Twitter: https://twitter.com/Huleaadis_Media
395 viewsEyasu Zekarias1, edited  08:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 11:30:28
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ለአንድ ደቂቃ 50 ሳንቲም የአገልግሎት እንደሚያስከፍል አስታወቀ!

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ለጀመረወው አገልግሎቶች ስንት እያሰከፈለ ነው በሚል ከአል ዐይን ለቀረበለት ጥያቄ ተከታዩን ምላሽ ሰጥቷል።

ድርጅቱ የድምጽ አገልግሎቱን በደቂቃ ከሳፋሪ ኮም ስልክ ቁጥሮች ወደ ሳፋሪኮም እና ወደ ኢትዮ ቴሌኮም ሲም ካርዶች በደቂቃ 50 ሳንቲም የሚያስከፍል ሲሆን ለኢንተርኔት ደግሞ በ10 ብር 120 ሜጋ ባይት፣ 900 ሜጋ ባይቱን በ50 ብር እንዲሁም ሁለት ጌጋ ባይት መጠን ያለውን ኢንተርኔት ደግሞ በ100 ብር ለ30 ቀናት በመደበኛነት በመሸጥ ላይ ነው።

ኩባንያው አክሎም እስከ ቀጣዩ ሚያዝያ 2015 ድረስ ባሉት ስምንት ወራት ውስጥ በ25 የኢትዮጵያ ከተሞች የቴሌኮም አገልግሎቶችን እንደሚጀምር ለአል ዐይን አስታውቋል።

ለወቅታዊ እና ለፈጣን መረጃዎች የሁሌ አዲስ ሚዲያ የማህበራዊ ሚዲያዎችን ይቀላቀሉ።

Facebook : https://www.facebook.com/Huleadissmedia/
Telegram : https://t.me/Hulaadiss
YouTube Channel
https://www.youtube.com/channel/UCk934znIu60LV3czcIVZ9Bg
Twitter: https://twitter.com/Huleaadis_Media
350 viewsEyasu Zekarias1, 08:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 11:26:35 ከዩክሬን የተገዛው እህል በዛሬው ዕለት ጂቡቲ ገባ።

በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አማካኝነት ለኢትዮጵያ ከዩክሬን የተገዛዉ እህል በዛሬው ዕለት ጂቡቲ መድረሱ ተነግሯል ።

ሩሲያ ዩክሬንን ከወረረች በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ አፍሪካ የተላከ እህል ነው።

ጂቡቲ የደረሰችው መርከብ የሊባኖስ ባንዲራ ያላትና ብሬቭ ኮማንደር የምትሰኝ ሲሆን በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአለም ምግብ ፕሮግራም የተገዛውን 23 ሺህ ቶን ስንዴ ጭነትም ይዛለች።

ለወቅታዊ እና ለፈጣን መረጃዎች የሁሌ አዲስ ሚዲያ የማህበራዊ ሚዲያዎችን ይቀላቀሉ።

Facebook : https://www.facebook.com/Huleadissmedia/
Telegram : https://t.me/Hulaadiss
YouTube Channel
https://www.youtube.com/channel/UCk934znIu60LV3czcIVZ9Bg
Twitter: https://twitter.com/Huleaadis_Media
329 viewsEyasu Zekarias1, edited  08:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 11:18:08 አንቶኒዮ ጉተሬዝ በድብቅ ከደብረጺዮን ጋር መነጋገራቸው ተነገረ።

አንቶኒዮ ጉተሬዝ የተ.መ.ድ ህግ ጥሰው በኢትዮጵያ በአሸባሪነት ከተፈረጀው ህወሓት ጋር በድብቅ አጭር ግንኙነት ማድረጋቸው ይፋ ሆኗል።

የመንግስታቱ ድርጅት ቃል አቀባይ ስቴፋን ዱጃሪች ሾልኮ የወጣ ኢሜል አስመልክቶ ለጋዜጠኞች እንዳረጋገጡት ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ባለፈው ሳምንት ከህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ ሊቀመንበር ደብረፂዮን ገብረሚካኤል ጋር “ለአጭር ጊዜ” መነጋገራቸውን አምነዋል። ጉተሬዝ በምን ጉዳይ ላይ የተ.መ.ድን አሰራር የጣሰውን ንግግር ከህወሓት መሪ ጋር እንዳደረጉ ግን በግልጽ አልተናገሩም።

ንግግሩ በኦገስት 25 ቀን 2022 መደረጉን ዱጃሪክ በይፋ አምነዋል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት መሪ ከአሸባሪ ድርጅት ጋር በቀጥታ መደራደሩ ከዚህ ቀደም ታይቶ የማይታወቅ እርምጃ ሲሆን ወያኔ አሁንም በአሜሪካ መንግስት እና በአፍሪካ ቀንድ በህግ ሽብርተኛ ከባሉት ቡድኖች ውስጥ አንዱ መሆኑ ይታወቃል። በአሰራሩ መሰረት የተባበሩት መንግስታት ከአይኤስ፣ ከአልሸባብ፣ ከአይአርኤ ወይም ከቦኮ ሃራም ጋር በቀጥታ እንደማይገናኝ ሁሉ ከሽብርተኛው ህወሓት ጋርም መገናኘት አይገባውም ነበር ተብሏል።

ከዚህም ባሻገር በጓተሬስ በኩል የተወሰደው መሰል እርምጃ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ቻርተር አንቀጽ 51 ላይ የተቀመጠው ቀጥተኛ ህግ እንዲሁም የተ.መ.ድ አባል ሀገራት ራሳቸውን ከሽብርተኝነት የመከላከል እና አስፈላጊ ከሆነም ጎረቤቶች እና አጋሮች እንዲረዷቸው የመጠየቅ መብት የሚሰጣቸው አንቀጽ የሚቃረን ነው።

በተባበሩት መንግስታት ድርጅት አባል ላይ የትጥቅ ጥቃት ከተፈፀመ የፀጥታው ምክር ቤት አለም አቀፍ ሰላምና ደህንነትን ለማስጠበቅ አስፈላጊ የሆኑትን እርምጃዎች እስካልወሰደ ድረስ በዚህ ቻርተር ውስጥ ያለው ማንኛውም ነገር የግለሰብም ሆነ የጋራ ራስን የመከላከል መብትን መጉዳትም አይፈቅድም። ይህንን ራስን የመከላከል መብትን በመጠቀም አባል ሀገራት የሚወስዱት እርምጃ ወዲያውኑ ለፀጥታው ምክር ቤት ሪፖርት ይደረጋል። ይህም ዓለም አቀፍ ሰላምና ደህንነትን ለማስጠበቅ ወይም ወደነበረበት ለመመለስ አስፈላጊ ነው እርምጃ ነው።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ተ.መ. ድ በሀሙስ ጋዜጣዊ መግለጫው ላይ ዱጃሪች የወያኔን 12 የነዳጅ ታንከሮች የዘረፉትን እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሰራተኞችን ጥቃት ወይም አፈና እንዲሁም የአማፂያኑ ቀጣይ የህጻናት የግዳጅ ምልመላ ጉዳይ ጉዳይ ሳይላይ ሳይናገሩ እንዳለፉት ይታወሳል።

ለወቅታዊ እና ለፈጣን መረጃዎች የሁሌ አዲስ ሚዲያ የማህበራዊ ሚዲያዎችን ይቀላቀሉ።

Facebook : https://www.facebook.com/Huleadissmedia/
Telegram : https://t.me/Hulaadiss
YouTube Channel
https://www.youtube.com/channel/UCk934znIu60LV3czcIVZ9Bg
Twitter: https://twitter.com/Huleaadis_Media
377 viewsEyasu Zekarias1, edited  08:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 21:46:59 በቀድሞው የአዲስ አበባ ከተማ የቢሮ ኃላፊ የባንክ አካውንት፤ 8.5 ሚሊዮን ብር ገቢ ተደርጎ እንደነበር ፖሊስ አስታወቀ

ከኮንዶሚኒየም ዕጣ ማጭበርበር ጋር በተያያዘ በእስር ላይ ለሚገኙት የቀድሞው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቢሮ ኃላፊ፤ በቁጥጥር ስር ከዋሉ በኋላ 8.5 ሚሊዮን ብር በባንክ አካውንታቸው ገቢ እንደተደረገላቸው የፌደራል ፖሊስ ገለጸ። በዶ/ር ሙሉቀን ሀብቱ ስም ከተከፈቱ አራት የባንክ አካውንቶች፤ 6.4 ሚሊዮን ብሩ ወጪ መደረጉንም አስታውቋል።

የፌደራል ፖሊስ ይህን የገለጸው “በስልጣን አላግባብ መገልገል ከባድ የሙስና ወንጀል” ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር በሚገኙት ዶ/ር ሙሉቀን ላይ ተጨማሪ ምርመራ ለማከናወን ዛሬ ሰኞ ለፍርድ ቤት ጥያቄ ባቀረበበት ወቅት ነው። ፖሊስ በተጠርጣሪው ስም በተከፈቱ የባንክ አካውንቶች የተደረጉ ዝውውሮችን መረጃ ያገኘው ከፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት መስሪያ ቤት መሆኑን የጊዜ ቀጠሮ መዝገቡን እየተመለከተ ለሚገኘው ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አስታውቋል።(Ethiopian insider)

ለወቅታዊ እና ለፈጣን መረጃዎች የሁሌ አዲስ ሚዲያ የማህበራዊ ሚዲያዎችን ይቀላቀሉ።

Facebook : https://www.facebook.com/Huleadissmedia/
Telegram : https://t.me/Hulaadiss
YouTube Channel
https://www.youtube.com/channel/UCk934znIu60LV3czcIVZ9Bg
Twitter: https://twitter.com/Huleaadis_Media
494 viewsEyasu Zekarias1, 18:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 18:04:45
የወልድያ ዩኒቨርሲቲ ባደረባቸው በስጋት ምክንያት ግቢያቸውን ለቀው የወጡ ተማሪዎችን በሚመለከት ውሳኔ አሳለፈ

የወልድያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በነሐሴ 22 ቀን 2014 ባደረባቸው ስጋት ምክንያት ግቢውን ለቀው መውጣታቸውን ገልጿል።

በዚህም መሰረት ዩኒቨርሲቲው የሚከተሉትን ውሳኔዎች አስተላልፏል፡፡

1ኛ. የመደበኛ መርሀ ግብር ተማሪዎች በሙሉ ወደ ዩኒቨርሲቲው መመለሻ ጊዜ በቀጣይ ዓመት ጥሪ በሚደረግበት ጊዜ ይሆናል።

2ኛ. የክረምት መርሀ ግብር ተማሪዎች በሙሉ የተጀመረውን ትምህርትና ፈተና ለማጠናቀቅ ወደ ዩኒቨርሲቲው መመለሻ ጊዜ መስከረም 03 ቀን 2015 መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

ለወቅታዊ እና ለፈጣን መረጃዎች የሁሌ አዲስ ሚዲያ የማህበራዊ ሚዲያዎችን ይቀላቀሉ።

Facebook : https://www.facebook.com/Huleadissmedia/
Telegram : https://t.me/Hulaadiss
YouTube Channel
https://www.youtube.com/channel/UCk934znIu60LV3czcIVZ9Bg
Twitter: https://twitter.com/Huleaadis_Media
534 viewsEyasu Zekarias1, edited  15:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 11:44:34
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በድሬዳዋ አገልግሎት መስጠት ጀመረ

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በድሬዳዋ ከተማ የሙከራ ስራውን መጀመሩን አስታውቋል። ደንበኞችም የፈልጉትን ስልክ ቁጥር መርጠው ሲም ካርድ መግዛት እንደሚችሉ አስታውቋል።

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ እንደገለፀው በድሬዳዋ በጀመረው የሙከራ ትግበራ የ2G፣ 3G እና 4G ኔትዎርኮችን ያስጀመረ ሲሆን የተቋሙ መለያ ከተለጠፈባቸው መደብሮች ደንበኞች ሲም ካርድ መግዛት ይችላሉ ብሏል። ከሲም ካርድ በተጨማሪም የስልክ ቀፎ እንደሚሸጥ ተገልጿል።

ሲም ካርዶቹ የደንበኛነት ማስጀመሪያ ጥቅል እንዳላቸው የተገለፀ ሲሆን የአየር ሰዓቱ ሲያልቅ በተመሳሳይ ከሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የሽያጭ ማዕከላት እና መደብሮች መግዛት እንደሚቻል አስታውቋል።

በተጨማሪም የተሻለ አገልግሎት ለማቅረብ የሚረዳ ‘700’ አጭር ቁጥር የደንበኞች አገልግሎት የጥሪ መስመር ድርጅቱ ያቀረበ ሲሆን በአማርኛ፣ ኦሮምኛ፣ ትግርኛ፣ ሶማልኛ እና እንግሊዝኛ ቋንቋዎች ድጋፍ ማግኘት ይቻላል ተብሏል።

የሳፋሪኮም ደንበኞች የኢንተርኔት ዳታ መጠቀም፣ ከሳፋሪኮም ኢትዮጵያ እና ከኢትዮ ቴሌኮም ደንበኞች ጋር የድምፅ እና የፅሁፍ መልዕክት መለዋወጥ እንዲሁም ዓለም አቀፍ ጥሪዎች ማድረግ እንደሚችሉ ተገልጿል።

ለወቅታዊ እና ለፈጣን መረጃዎች የሁሌ አዲስ ሚዲያ የማህበራዊ ሚዲያዎችን ይቀላቀሉ።

Facebook : https://www.facebook.com/Huleadissmedia/
Telegram : https://t.me/Hulaadiss
YouTube Channel
https://www.youtube.com/channel/UCk934znIu60LV3czcIVZ9Bg
Twitter: https://twitter.com/Huleaadis_Media
580 viewsEyasu Zekarias1, 08:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 20:03:13
ከደሴ ከተማ የፀጥታ ምክር ቤት በወቅታዊ የከተማው ሰላም እና ደህንነት ላይ መክሮ ውሳኔ አሳልፏል።

በዚህም ፦

- የምግብ ቤቶች ፣ የምሽት መጠጥ ቤቶች/ግሮሰሪዎች/ ከምሽቱ 1፡ዐዐ ሰዓት ጀምሮ በማንኛውም ምክንያት አገልግሎት መስጠት እንደማይችሉ ተከልክሏል።

- ማንኛውም ምርት ላይ የዋጋ ጭማሬ የሚያደርጉ አካላት ላይ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ ተገልጿል።

- በመፈናቀል ሆነ በሌላ ማንኛውም ምክንያት ወደ ደሴ ከተማ የገቡ ተፈናቃዮች የከተማውን ደህንነት ለማስጠበቅ ሲባል የፀጥታ ኃይሎች ለጋራ ደህንነት ለሚተገብሯቸው የፍተሻና የቅድመ-ጥንቃቄ ስራዎች ተባባሪ የመሆን ግዴታ አለባቸው ተብሏል።

- አልጋ ቤት፣ የመኖሪያ ቤት ወይም መደብ ቤት አከራዮች የየትኛውንም ተከራይ ማንነትን የሚገልፅ መረጃ ለፀጥታ ተቋማት የመስጠት ግዴታ ተጥሎባቸዋል።

- ወደ ደሴ በማንኛውም ምክንያት የገቡ እንግዶች ከምሽቱ 1:00 ሰዓት በኋላ መንቀሳቀስ ተከልክሏል።

- ከተፈቀደላቸው የከተማው የፀጥታ ሃይሎች ውጭ ጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ ፈፅሞ ተከልክሏል።

- ከዛሬ ጀምሮ የትኛውም የከተማችን ነዋሪ ከምሽቱ 2:00 /ሁለት/ ሰዓት ጀምሮ በተናጠልም ሆነ በጋራ መንቀሳቀስ ተከልክሏል።

- በከተማ ደረጃ እውቅና ያላቸው የተሰጣቸው የታክሲ አሽከርካሪዎች እስከ ምሽቱ 2:00 ሰዓት ብቻ ህዝቡን እንዲያገለግሉ ተወስኗል።

- በሁሉም አካባቢወች የሚገኙ ባጃጆች እስከ ምሽቱ 1:00 ሰዓት ብቻ አገልግሎት እንዲሰጡ ውሳኔ ተላልፏል።

- የDSTV አገልግሎት መስጫዎች ፣ በጋራ ተሰብሰቦ ጫት የሚቃምባቸው መቃሚያ ቤቶች ፣ የሽሻ ቤቶች ከዛሬ ጀምሮ በይፋም ሆነ በስውር አገልግሎት መስጠት ተከልክሏል።

(ተጨማሪ ከላይ ተያይዟል)
@Hulaadiss
591 viewsEyasu Zekarias1, edited  17:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 20:01:21 ህወሃት ግብአተ መሬቱ እስኪረጋገጥ ድረስ እንቅልፍ እንደሌለዉ የሲዳማ ክልል ገለፀ።

ትዕግስትንና የሰላምን ጥሪ ላልተቀበለዉ የህወሓት ቡድን ግብአተ መሬቱ እስኪረጋገጥ ድረስ የሲዳማ ህዝብና መንግሥት እንቅልፍ እንደለሌዉ ክልሉ አሳወቀ።

ሲዳማ ክልል በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳይ ባወጣዉ መግለጫ ህወሃት ሀገር ለማፍረስ ወደ ኋላ የማይል በጥላቻ የታወረ ቡድን ነዉ ያለ ሲሆን በሀገራችን ላይ በተደጋጋሚ ጦርነት ከፍቷል ይህም ለሰላም ምንም አይነት ቦታ የሌለው ለሐገርና ለህዝብ ጠንቅ ተልዕኮ ማንገብን አመላካች ነዉ ብሏል።

የኢትዮጵያ ህዝብና መንግስት ያቀረበለትን የሰላም አማራጭ ወደ ጎን በመተው ዳግም ለሦስተኛ ጊዜ ጦርነት በመክፈት ለኢትዮጵያና ለንፁሃን የትግራይ ህዝብ ያለውን ንቀት አሳይቷል ብሏል መግለጫው ።

የክልሉ መንግስት በመግለጫዉ እንዳመላከተዉ ከስህተቱ የማይማረው ህወሓት ዳግም ለሦስተኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ የከፈተው ጦርነት ለኢትዮጵያ ህዝብና መንግስት ያለውን ጥላቻ ያሳየበት ነው ሲል ገልጿል። ይህም ደግሞ ኢትዮጵያውያንን ከጫፍ እስከ ጫፍ በቁጣ የሚያነሳሳና በተባበረ ክንዳቸው ህወሓትን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ግባተመሬቱ እንዲያፋጥኑ የሚያደርግ መሆኑን ገልጧል ።

ለወቅታዊ እና ለፈጣን መረጃዎች የሁሌ አዲስ ሚዲያ የማህበራዊ ሚዲያዎችን ይቀላቀሉ።

Facebook : https://www.facebook.com/Huleadissmedia/
Telegram : https://t.me/Hulaadiss
YouTube Channel
https://www.youtube.com/channel/UCk934znIu60LV3czcIVZ9Bg
Twitter: https://twitter.com/Huleaadis_Media
500 viewsEyasu Zekarias1, 17:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 17:30:21 ህወሓት በአማራ እና አፋር ክልሎች የጀመረውን ወረራ እንቀለብሳለን ሲል የደቡብ ክልል ገለፀ።

የደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል መንግስት ህወሓት በአማራ እና በአፋር ክልሎች የከፈተዉን ጦርነት
በተባበረ ክንድ ለመቀልበስ ዝግጁ መሆኑን አሳዉቋል።

ክልሉ በዛሬዉ ዕለት ባወጣዉ መግለጫ  ከሰላም ይልቅ ጦርነትን መርጦ የሀገርን ሉዓላዊነት ለመዳፈር አልሞ እየተንቀሳቀሰ ያለውን የህወሓት ቡድን እንደ ከዚህ ቀደሙ ሁሉ አስፈላጊውን መስዋዕትነት በመክፈል ለመመከት  ዝግጁ መሆኑን ገልጧል።

መንግስት በሽብርተኛ እያለ የሚጠራዉ ህዘሓት ነእኔ ያልመራኋት ሀገር መፍረስ አለባት በሚል እሳቤ ለሰላም የተዘረጋውን አማራጭ ወደ ጎን በመተው ለጋ ህጻናትን በማሰለፍ ግልጽ ወረራ መጀመሩን ያሳወቀው መግለጫዉ    በመከላከያ ሠራዊት የሰሜን እዝ ላይ ከፈጸመው ክህደት ጀምሮ የትግራይ ወጣቶችን ወደ ጦርነት በማስገባት በአማራና አፋር ክልሎች በፈጸመው ግልጽ ጦርነትና ወረራ ያደረሰው እልቂት  ቡድኑ ለሰብዓዊነት ምንም የማይራራ አረመኔ መሆኑን በግልጽ የማያሳይ ነዉ ብሏል።

ለወቅታዊ እና ለፈጣን መረጃዎች የሁሌ አዲስ ሚዲያ የማህበራዊ ሚዲያዎችን ይቀላቀሉ።

Facebook : https://www.facebook.com/Huleadissmedia/
Telegram : https://t.me/Hulaadiss
YouTube Channel
https://www.youtube.com/channel/UCk934znIu60LV3czcIVZ9Bg
Twitter: https://twitter.com/Huleaadis_Media
512 viewsEyasu Zekarias1, 14:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ