Get Mystery Box with random crypto!

ከደሴ ከተማ የፀጥታ ምክር ቤት በወቅታዊ የከተማው ሰላም እና ደህንነት ላይ መክሮ ውሳኔ አሳልፏል | ሁሌ አዲስ ሚዲያ (Hule Addis Media)

ከደሴ ከተማ የፀጥታ ምክር ቤት በወቅታዊ የከተማው ሰላም እና ደህንነት ላይ መክሮ ውሳኔ አሳልፏል።

በዚህም ፦

- የምግብ ቤቶች ፣ የምሽት መጠጥ ቤቶች/ግሮሰሪዎች/ ከምሽቱ 1፡ዐዐ ሰዓት ጀምሮ በማንኛውም ምክንያት አገልግሎት መስጠት እንደማይችሉ ተከልክሏል።

- ማንኛውም ምርት ላይ የዋጋ ጭማሬ የሚያደርጉ አካላት ላይ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ ተገልጿል።

- በመፈናቀል ሆነ በሌላ ማንኛውም ምክንያት ወደ ደሴ ከተማ የገቡ ተፈናቃዮች የከተማውን ደህንነት ለማስጠበቅ ሲባል የፀጥታ ኃይሎች ለጋራ ደህንነት ለሚተገብሯቸው የፍተሻና የቅድመ-ጥንቃቄ ስራዎች ተባባሪ የመሆን ግዴታ አለባቸው ተብሏል።

- አልጋ ቤት፣ የመኖሪያ ቤት ወይም መደብ ቤት አከራዮች የየትኛውንም ተከራይ ማንነትን የሚገልፅ መረጃ ለፀጥታ ተቋማት የመስጠት ግዴታ ተጥሎባቸዋል።

- ወደ ደሴ በማንኛውም ምክንያት የገቡ እንግዶች ከምሽቱ 1:00 ሰዓት በኋላ መንቀሳቀስ ተከልክሏል።

- ከተፈቀደላቸው የከተማው የፀጥታ ሃይሎች ውጭ ጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ ፈፅሞ ተከልክሏል።

- ከዛሬ ጀምሮ የትኛውም የከተማችን ነዋሪ ከምሽቱ 2:00 /ሁለት/ ሰዓት ጀምሮ በተናጠልም ሆነ በጋራ መንቀሳቀስ ተከልክሏል።

- በከተማ ደረጃ እውቅና ያላቸው የተሰጣቸው የታክሲ አሽከርካሪዎች እስከ ምሽቱ 2:00 ሰዓት ብቻ ህዝቡን እንዲያገለግሉ ተወስኗል።

- በሁሉም አካባቢወች የሚገኙ ባጃጆች እስከ ምሽቱ 1:00 ሰዓት ብቻ አገልግሎት እንዲሰጡ ውሳኔ ተላልፏል።

- የDSTV አገልግሎት መስጫዎች ፣ በጋራ ተሰብሰቦ ጫት የሚቃምባቸው መቃሚያ ቤቶች ፣ የሽሻ ቤቶች ከዛሬ ጀምሮ በይፋም ሆነ በስውር አገልግሎት መስጠት ተከልክሏል።

(ተጨማሪ ከላይ ተያይዟል)
@Hulaadiss