Get Mystery Box with random crypto!

ሰማያዊ ስጦታ ቤተክርስቲያን//Heaven Gift Church//

የቴሌግራም ቻናል አርማ http_gcgm — ሰማያዊ ስጦታ ቤተክርስቲያን//Heaven Gift Church//
የቴሌግራም ቻናል አርማ http_gcgm — ሰማያዊ ስጦታ ቤተክርስቲያን//Heaven Gift Church//
የሰርጥ አድራሻ: @http_gcgm
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 16.34K
የሰርጥ መግለጫ

👉መልካሙ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን
👉ማቴ 14፥30
👉ሚኒስትሪያችንን በተለያዩ ስጦታዎች
ስለምታግዙን እናመሰግናለን።
ለማንኛውም ጥያቄ እና እገዛ👇
ለፀሎት አገልግሎት ከስር ያለውን ስልክ ይጠቀሙ።
https://www.facebook.com/gcgm.gctv?mibextid=sCpJLy
👉YouTube-https://youtube.com/@melkamqine?si=vBbrpgENQkfcJ

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2023-03-02 19:39:54 ልጅ ነን ወይስ መለኮት (ፀሎት)
672 viewsEjob @ JS, edited  16:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-24 16:01:32 ያወራድችሁ ህይወትን ይስጣችሁ
907 viewsEjob @ JS, edited  13:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-24 12:35:05
"ቦረና ወገኔ"በሚል መሪ ቃል ሚኒስትሪያችን እና ቤተክርስቲያናችን  የ5000ብር ድጋፍ አድርገናል ፥ከዚህም በኋላ በጸሎትም ሆነ በሁሉ ነገር ከወገኖቻችን ጋር ነን።

በክርስቶስ
413 viewsEjob1 Ejob, 09:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-24 12:26:16
#ቦረና

በ #ቦረና በታሪክ እጅግ አስከፊ በተባለው ድርቅ ሳቢያ የተጎዱ ወገኖቻችንን ለመርዳት የምትፈልጉ በ " #ALCHIISOO_PASTORALIST_UP " በኩል መርዳት ትችላላሁ።

You Are blessed
413 viewsEjob @ JS, 09:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-24 06:00:52 አምነንበታል!
ስለጌታ ኢየሱስ አዳኝነት መመስከር ካባድ ነውን?
ስናነብ ካገኘናቸው

እኔ ለሲዖል ያለኝን መረዳት የሚገልጽልኝ፦ ሰይጣን ከሰማይ አምጾ ከተጣለበት ጊዜ አንስቶ ዳግም ጌታ ኢየሱስ እስኪመጣ ለሰራው ጥፋት፣ ክፋት፣ አመጽ (የሰይጣንን ወንጀል መጠን አስቡት) ይገባዋል የተባለ ስፍራ ነው።በእርግጥ ተመጣጣኝ ቅጣት ነው። ትክክለኛ ፍርድና ዋጋ!

ሲዖል ለሰው ዘር የተዘጋጀ ስፍራ አይደለም!
"ለሰይጣንና ለመላአክቱ ወደ ተዘጋጀ ወደ ዘላለም እሳት ከእኔ ሂዱ" ማቴ 25፡41

ጌታ ኢየሱስ የሰማይና የምድር ፈጣሪ የጌቶች ጌታ የነገሥታት ንጉስ ኃያል አምላክ ዙፋኑን ክብሩን ትቶ ሰው ሆኖ የባሪያን መልክ ይዞ ወደ ምድር መምጣቱ፣ ሰዎች ሲዖል እንዳይገቡ የከፈለው ዋጋና የተቀበለው መከራ የሲዖልን አደገኛነትና ዘግናኝነት በግልፅ የሚያሳይ ነው! "የሰው ልጅ የጠፋውን ለማዳን መጥቶአልና" ማቴ 18፡11

ሲዖል ቀላል ስፍራ ቢሆን ኖሮ ወይም ለሰውም የተገባ የተዘጋጀ ቢሆን ኖሮ አምላክ ሰው ባልሆነ በፈጠረው በሰው እጅ የርጉም ሞት ባልሞተ ነበር!

ለማንም ሰው ሲዖል አይገባም።
ምክንያቱም ጌታ ኢየሱስ ለሰው ዘር ሁሉ መዳን የኃጢአትን ዋጋ ከፍሎአል፤ በቂና ብቁ ሥራ ሠርቷል!

የሰዎች መዳን ወይም አለመዳን ከአማኞች (ከእኔ፣ ከአንተ፣ ከአንች) ምስክርነት ጋር በቀጥታ የተያያዘ ነው። እንዲህ ተብሎ እንደተጻፈ፦ "እንግዲህ ያላመኑበትን እንዴት አድርገው ይጠሩታል? ባልሰሙትስ እንዴት ያምናሉ? ያለ ሰባኪስ እንዴት ይሰማሉ?" ሮሜ 10፡14

ያለ አንተ ምስክርነት እንዴት ይሰማሉ? የእኛ ዝምታ በሰዎች ላይ የሲዖል ፍርድ መፍቀድ ነው።

ወንጌልን መናገር ለአማኞች የተተው ድርሻ ነው።
ወንጌል መናገር የመላእክት ተግባር አይደለም። መላእክት የራሳቸው የሥራ ድርሻ አላቸው። በእርግጥ በዚህ ተልእኮ ውስጥ እንደ ጌታ ፈቃድ ያግዙናል። ነገር ግን አማኞች በእግዚአብሔር መንግሥት ውስጥ የሥራ ድርሻ ይኖረን ዘንድ ቀጥታ ለእኛ የተመደበ ሥራ ነው።

ከላይ ለመግለጽ እንደሞከርኩት ሲዖል የተዘጋጀው ለሰይጣን ከሆነና ለማሰብ እንኳን የሚከብድ ስፍራ ከሆነ፤ ጌታ ኢየሱስ ኃጢአተኞችን ሁሉ የሚያድን ሙሉ ሥራ ከሠራና ከኃጢአተኛውም የጌታ ኢየሱስን አዳኝነት አምኖ ለመቀበል ወንጌልን መስማት ግድ ከሆነ በጨለማ ላሉ ወንጌል መናገር የእኛ አንገብጋቢ ተግባር ነው።

ወዳጆቼ እስቲ ቆም ብለን እናስብ ላልዳኑ ወገኖች
"ኢየሱስ ያድናል!"  "ጌታ ኢየሱስ ይወድሃል!" "የኃጢአት እዳህን ኢየሱስ ከፍሎልሃል!" ብሎ መመስከር እስከዚህ በእርግጥ ካባድ ነውን??

የሰው ልጅ መክፈል የማይችለውን ከባድ ዋጋ ጌታ ኢየሱስ መስቀል ላይ ከፍሎል!

ከእኛ የሚጠበቀው ማድረግ የምንችለው ቀላል በጨለማ ላሉ ወንጌልን ማወጅ ነው!

የተደረገልንን መመስከር ማድረግ የማንችለው ካባድ ነውን?
የቀመስነውን ፍቅር መመስከር ያሳፍራልን?
ታሪካችንን የለወጠ ከጨለማ ያወጣን ጌታ መልካምነት ዝም ያሰኛልን?

በጌታ በኢየሱስ ስም አዚምና ድንዛዜ ከላያችሁ ይነሳ! አሁን በያለንበት "እብድ ብሆን ለክርስቶስ ነው!" የሚያስብል ዝም የማያሰኝ ታላቅ እሳት ያግኛችሁ!

ወንጌል እንዳንመሰከር የሚያደርጉ እንቅፋቶች፦

1. የተደረገልንና ያገኘነውን የዘላለም ሕይወት ዋጋ አለመረዳት
2. መንፈሳዊ አይን አለመከፈት (የሲዖልንና የመንግሥተ ሰማያትን ልዩነት አለመረዳት)
3. በውስጣችን ላለው ለመንፈስ ቅዱስ ኃይል እውቅና አለመስጠት (የባዶነት ስሜት) በእውነተኛ አማኞች ሁሉ ውስጥ መንፈስ ቅዱስ አለ።
4. ክርስቶስ በጨለማ ላሉ ያለውን ርህራሔ መጠን አለመረዳት
5. ለሰዎች መዳን ሸክም ማጣት
6. ራስ ወዳድነት ለምድራዊዉ (ለራሳችን) ጉዳይ ብቻ ትኩረት መስጠት

7. ወንጌል መመስከርን ብዙ እውቀት እንደሚጠይቅ ማሰብ (በየትኛውም እምነትና እውቀት ደረጃ ያለ አማኝ መናገር ይችላል። ሳምራዊቷን ሴት ማሰብ በቂ ነው ዮሐ 4፡7)
8. ዛሬም ወንጌል ያለውን መለኮታዊ የመሥራት (የመለወጥ) ኃይል አለመረዳት
9.  በእኛ ምስክርነት (ንግግር) ውስጥ ያለውን ጉልበት አለመረዳት (የእኛ ምስክርነት እምነት የመፍጠር ኃይል አለማስተዋል)
10. በጨለማ ያሉ ሀብታም ይሁን ድሃ እንዴት ያለ
ተስፋ ቢስ ሕይወት ውስጥ እንዳሉ አለመረዳት
11. ሰይጣን በምን ያህል ትጋትና ቁጣ እየሰራ እንዳለ አለመረዳት
12. ሰዎች ድካማቸውን ብቻ ማየት ፀጋውን አለማሰብ (ከድካም ስወጣ ስለወጥ እመሰክራለሁ አትበል ስትመሰክር ከድካም ትወጣለህ)

13. የሰዎች አመለካከት ይለውጥብኛል ብሎ መፍራት (ይሉኝታ)
14. ቤተክርስቲያን ለምስክርነት ትኩረት ሰጥታ አለማስተማሪና አለመሥራት (ምሳሌ የሚሆኑ የሚያበረታቱ አማኞች በዙሪያችን ማነስ)
15. አሁን በሚታዩ ሁኔታዎች ተስፋ መቁረጥና ሕይወቴ ይመስክር ብሎ ማሰብ (መልካም ሕይወት መልካም ነው! ነገር ግን በአንደበታችን መመስከር ግድ ነው። ጌታ የሌላቸውም መልካም ሥነ ምግባር ያላቸው ብዙ ሰዎች እንዳሉ ማስታወስ)
16. መመስከር ለሚገባን በጨለማ ላሉ ሰዎች (ሐይማኖት ተቋማት) እንደማይቀበሉ ያለን የተሳሳተ ግምት (ሐናንያ ስለሳውል (ስለሐዋርያው ጳውሎስ) የነበረው መረጃ ተቃዋሚ አሳዳጅ እንደ ነበረ ያለው መረጃው እንቅፋት ሆኖበት ነበር ሐዋ 9፡13)
17. ወንጌል በተለያየ መንገድ በበቂ ሁኔታ እየተሰበከ ነው (በሚዲያዎች በኮንፈረንሶች...) ወንጌል ያልሰማ የለም ብሎ ማሰብ (መቼም ለእኔ ከዚህ በላይ ስህተት ያለ አይመስለኝም።) በሀገራችን እንኳ ገና ከ80% በላይ ሕዝብ እውነተኛ ወንጌል ያስፈልገዋል። ሌላው  ለአንድ ሰዉ እስከ መቼ ነው መመስከር ያለብን? መልሱ እስኪድን ድረስ ነው!
18. አለመመስከራችን በመጨረሻው ቀን ተጠያቅነት ጸጸትም እንዳለበት መዘንጋት ...

ከዚህ በላይ ብዙ ምክንያት መዘርዘር ይችላል ነገር ግን በእግዚአብሔር ፊት ተቀባይነት ያለው አንድም ምክንያት የለም። ወንጌል ላለመስከራችን እግዚአብሔር ምክንያትን አይቀበልም።

ስለዚህ መፍትሔው አማኞች ሁላችንም በትጋት መመስከርና መመስከር ብቻ ነው!

ለመመስከር ከወሰንን፣ ራሳችንን ከሰጠን፣ የመዳን ዋጋ ከገባንና ፈቃደኞች ከሆንን አሁን በዚህ ሰዓት እንኳን በአጠገባችን ላሉ ሰዎች ወይም ወደሚገኙበት ወጣ ብለን ወይም ቴክኖሎጂውን (ሶሻል ሚዲያ) ተጠቅመን መመስከር እንችላለን።

ወንጌልን መመስከር ቀላል ነው! ይቻላል!
ምክንያቱም የተደረገልንን ያገኘነውን ሕይወት የቀመስነውን ፍቅር የምንወደውን ጌታ መመስከር ስለሆነ!

ማስታወስ ያለብን እኛ ለመመስከር ፈቃደኞች ከሆንን የምንናገረውን ቃልና ኃይል የሚሰጠን መንፈስ ቅዱስ ነው።

እስከዛሬ በሚገባ ባለመመስከራችን ሊድኑ የምችሉ (የሚገባቸው) ጌታን ሳይቀበሉ ስንቶች አልፈው ይሁን?

እርግጠኞች እንሁን በሚገባ ባለመመስከራችን ጌታን አሳዝነናል።

እግዚአብሔር ባገኘነው አጋጣሚ ሁሉ በተገኘንበት ሁሉ ሁልጊዜ መመስከራችንን ይፈልገዋል።

ላለፉት ብዙ ዓመታት ውስጤ ያለ ጥያቄ ነው ወንጌል መመስከር እስከዚህ ከባድ ነውን? ለምንድነው በሚገባ ወንጌል የማንመሰክረው??

መልሳችን (ምክንያታችን) ምን ይሁን ምን ተቀባይነት የለውም። መፍትሔዉ መመስከር መጀመር ብቻ ነው።

ጌታ ኢየሱስ እኛ መክፈል የማንችለውን የኃጢአት  እዳ በመስቀል ላይ ከፍሎልናል። ነገር ግን ቀላል እኛ መክፈል የምንችለው ወንጌል የመናገር የፍቅር እዳ አለብን።

"ቀንበሬን በላያችሁ ተሸከሙ...
ቀንበሬ ልዝብ ሸክሜም ቀሊል ነውና" ማቴ 11፡29
716 viewsEjob @ JS, 03:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-24 06:00:43
656 viewsEjob @ JS, 03:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-23 09:24:09
ጌታ መልካም ነው ወገኔ ምን ማድረግ እንደምንችል እንወያይ ቦረና እና በዙሪያው ላላችሁ በውስጥ አውሩን ።

ሐዋሳ ጁማ እና ለቦረና ቅርብ የሆናችሁ አውሩን
934 viewsEjob @ JS, 06:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-21 07:22:47
ሰላም ለእናንተ በማለዳ እንዲህ ልባርካችሁ ነገሬ ተስፋ የለውም ያላችሁት ነገር ዛሬ ልባርካችሁ
ጌታ ስላለበት ተስፋ አለው ተባረኩ
በኢየሱስ ስም ተስፋ ከቆረጣችሁት ነገር ጋር ተቃቀፉ
769 viewsEjob @ JS, 04:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-17 06:00:47 ሰላም ቅዱሳን ክፍል 6
እንግዲ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፡ይህ አዲስ ተደርጎ የተፈጠረው ሰው የመንፈስ ፍሬ ደግሞ አልፎም በስጋ ህይወት ላይ የሚገለጥ ህይወት አለው ብለናል።
መነሻ ጥቅስ ፥- ገላ 5፥22
ገላትያ 5 (Galatians)
22፤ የመንፈስ ፍሬ ግን ፍቅር፥ ደስታ፥ ሰላም፥ ትዕግሥት፥ ቸርነት፥ በጎነት፥ እምነት፥ የውሃት፥ ራስን መግዛት ነው።

አዲሱ ሰው እና የመንፈስ ፍሬ
6.በጎነት
Greek translation.... Agathosyne
English Translation...Goodness
አማርኛ ፍቺ.....በጎነት

በገላትያ ምዕራፍ 5
ከተገለጹት የመንፈስ ፍሬዎች መካከል አንዱ "በጎነት" ነው፡፡ በጎነት ለሰዎች ያለን መልካም አመለካከትና የምናደርገው ማንኛውም መልካም ሥራ ሁሉ ነው፡፡

በጎነት ማንኛውንም መልካምና ጥሩ፣ የበጀ የተወደደ፣ ሥራን ያካትታል:: አምላካችን እግዚአብሔር በባሕርዩና በሥራው በፈጠረው ፍጥረት መደነቁ ሁሉ የበጎነቱ አይነተኛ ምልክት ነው፡፡ ሁሉንም በየወገኑ በመፈጠሩ ማለቴ ነው፡፡

እግዚአብሔር ለፍጥረቱ በፍጥረቱ በጎነት ይታወቃል እንዳሉ አበው እዚህ ላይ ማስተዋል ያለብን በጎነት ሲባል ንጽጽራዊ በጎነት ማለት ነው፡፡ ፍፁም በጎነት የእግዚአብሔር ባሕርይ ብቻ ነው፡፡
“የሰማዩ አባታችሁ ፍጹም እንደሆነ እናንተም ፍጹማን ሁኑ” ማቴ. 5፡48 ተብሎ በጌታ ቃል ከተገለጸው ፍጹምነት ጋር ተመሳሳይ ነው ይህም ንጽጽራዊ ፍጹምነት ነው፡፡

  ሁለት ዓይነት በጎነት አለ ይኸውም

1.አሉታዊና
2.አወንታዊ

አሉታዊ በጎነት ማለት ክፋትና ኃጢአትን ማስወገድ ነው፡፡ ይህም በ10ቱ ትዕዛዛት ውስጥ የምንማራቸው ናቸው፡፡

“የአግዚአብሔር የአምላክህን ስም በከንቱ አትጥራ የተቀረጸውን ምስል ለአንተ አታድርግ፣ አትግደል፣ አታመንዝር፣ አትስረቅ፣ በባልንጀራህ ላይ በሐሰት አትመስክር የባልንጀራህን ሚስት አትመኝ…”ዘዳ.5፡11በሚለው ውስጥ በእምነት የምንተገብራቸው ናቸው፡፡

አወንታዊ ስንል ደግሞ በጎነትን በብሉይ ኪዳን ውስጥ ስንመለከት “አንተም አምላክህን እግዚአብሔርን በፍፁም ልብህ በፍጹም ነፍስህ በፍጹም ኃይልህ ውደድ" ዘዳ.6፡5 በሚለው ውስጥ የተካተቱት ናቸው፡፡
አዲስ ኪዳንም ውስጥ ክርስቶስ ስለ ብፁዓን በተናገራቸው ዓረፍተ ነገሮች ውስጥ ተጠቅሰዋል፡፡
"በመንፈስ ድሆች የሆኑ…የዋሆች….ልበ ንጹሖች…የሚያስታርቁ…ብፁዓን ናቸው ወዘተ…"ማቴ.5፡3፡፡ አሁን በጻፍኩላችሁ በበጎነት የመንፈስ ፍሬ ላይም በግልጽ የምንማረው ነው፡፡

ከማንኛውም ኃጢአትና ክፉ ሥራ ሁሉ ለመራቅ፣ እና በመልካም ምግባር ታንጾ ለመጓዝ ሁለቱንም መንገዶች መከተል አለብን በሕግና በፍቅር /በውዴታ/የምንፈጽማቸው የበጎነት ሥራ ማለት ነው፡፡ አንድ ሰው ሙሉ የሆነ በጎነትን ገንዘቡ ካደረገ ከማንኛውም ክፉ ነገር ነፃ ይሆናል፡፡

ይህን በእውነተኛ መጽሐፍ ቅዱስ መረጃ ለማስረዳት የሞከርኩትን ከዚህ የሚከተለውን በጥሞና አንብባችሁ ተረዱልኝ፡፡ ይስሐቅና እስማኤል፣ ቃየልና አቤል በአንድነት መኖር እንዳልቻሉ ሁሉ መንፈስና ሥጋ /አሮጌ ተፈጥሮ/ እርስ በርሳቸው በተቃውሞና በጦርነት ላይ ናቸው፡፡

መንፈስ ቅዱስ አካላችንን የሚቆጣጠረው ከሆነ በመንፈስ እንመላለሳለን ሥጋ አካላችንን የሚቆጣጠረው ከሆነ በሥጋ ምኞትና ፍላጎት እንመላለሳለን፡፡ በመንፈስና በሥጋ መካከል ያለው ተቃውሞ ምክንያት መንፈስና ሥጋ የተለያዩ ፍላጎቶች ያላቸው መሆናቸው ነው፡፡

ለምሳሌ፡-
በግ ቆሻሻ ነገሮችን የማይወድ ንፁሕ እንስሳ ስለሆነ ነው፡፡
አሳማ ግን ከታጠበች በኋላ ወደ ጭቃ የምትመለስ ንጽሕናን የማትወድ ናት::

2ጴጥ 2፡19በኖኀ ዘመን የሆነው ቁራ ሥጋ በል እንደመሆኑ በቂ ምግብ በማግኘቱ በዚያው ቀረ፡፡
"መልካሟ ርግብ ግን የምሥራች ይዛ ተመልሳ መጣች ሁለተኛ ሲለቃት ወዲያው ቀረች የምታርፍበት ምድር ተስተካክሎ ነበርና"
ዘፍ.8፡6-12

ሮሜ7፡15 ፤ ዕብ10፡14 ፤ 2ቆሮ3 ፤ 1መዝ40፡8 ፤ 1ጢሞ1፡9 ፤ 2ጢሞ3፡2 ፤
ኤር. 17፡9 አንብቡ፡፡

ቅዱስ ዳዊት “ከአንተ በቀር በጎነት የለኝም”መዝ.15፡2 ባለው መሠረት የክርስቲያኖች በጎነታቸው ራሱ እግዚአብሔር ነው፡፡ ምክንያቱም ቃሉ እንደሚለን “እግዚአብሔርንም ለሚወዱት እንደአሳቡም ለተጠሩት ነገር ሁሉ ለበጎ እንዲደረግ እናውቃለን” ሮሜ.8፡28
ከእግዚአብሔር የሆነው ነገር ሁሉ በጎ ነገር ነው፡፡
ይህንን የእግዚአብሔርን በጎነት ለሰው ልጆች በሙሉ ማስተማር መንገር አለብን 1ጴጥ.2፡9
ክርስቲያኖችም መልካም ሥራን መፈለግም ሆነ ማድረግ የምንችለው በእግዚአብሔር በጎ ፈቃድ ነው፡፡
“የአግዚአብሔር በጎ ፈቃድም በስብከት ሞኝነት የሚያምኑ እንዲድኑ ነው" ፊልጵ2፡13
ቅዱስ ጴጥሮስ “በጎ ለማድረግ ብትቀኑ የሚያስጨንቃችሁ ማነው ብሏል" 1ጰጥ3፡13

በክርስትና ኃጢአት የሚባለው ክፉ ሥራ ብቻ ሳይሆን በጎ አለማድረግም ነው፡፡ “እንግዲህ በጎ ለማድረግ አውቆ ለማይሠራው ኃጢአት ነው”ያዕ4፡17:: ሐዋርያው ያዕቆብ በተጨማሪ እንዲህ ሲል ይመክረናል “የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ አትሳቱ በጎ ስጦታ ሁሉ ፍጹምም በረከት ሁሉ ከላይ ናቸው መለወጥም በእርሱ ዘንድ ከሌለ በመዞርም የተደረገ ጥላ በእርሱ ዘንድ ከሌለ ከብርሃናት አባት ይወርዳሉ፡፡ በጎ መሆን በራሱ ስጦታ መሆኑን አስረድቷል”

በጎ ሥራ የሌለው እምነት የሞተ ነው

“ወንድሞች ሆይ እምነት አለኝ የሚል ሥራ ግን የሌለው ሰው ቢኖር ምን ይጠቅመዋል? እምነቱስ ሊያድነው ይችላልን? ወንድም ወይም እህት ራቁታቸውን ቢሆኑ የዕለት ምግብንም ቢያጡ ከእናተ አንዱም በደኅና ሂዱ እሳት ሙቁ ጥገቡም ቢላቸው ለሰውነት ግን የሚያስፈልጉትን ባትሰጡአቸው ምን ይጠቅማቸዋል? እንደዚህም ሥራ የሌለው እምነት ቢኖር በራሱ የሞት ነው” ያዕ. 2፡14

በጎነት ከቅናት የራቀ ነው

"ከእናንተ ጥበበኛና አስተዋይ ማን ነው?በመልካም አነዋወሩ ሥራውን በጥበብ የዋህነት ያሳይ፡፡ ነገር ግን መራራ ቅንዓትና አድመኛነት በልባችሁ ቢኖርባችሁ አትመኩ በእውነትም ላይ አትዋሹ ይህ ጥበብ ከላይ የሚወርድ አይደለም ነገር ግን የምድር ነው፣ የሥጋም ነው፣ የአጋንንትም ነው ቅንዓትና አድመኛነት ባሉበት ሰፍራ በዚያ ሁከትና ክፉ ሥራ ሁሉ አሉና፡፡
ላይኛይቱ ጥበብ ግን በመጀመሪያ ንጽሕት ናት በኃላም ታራቂ ገር እሺ ባይ ምሕረትና በጎ ፍሬ የሞላባት ጥርጥርና ግብዝነት የሌለባት ናት፡፡ የጽድቅም ፍሬ ሰላምን ለሚያደርጉት ሰዎች በሰላም ይዘራል" ያዕ3፡13 ሲል ያስተማረው የበለጠ ልብ የሚነካ ምስጢር ነው፡፡

ስለዚህ አዲሱ ሰው ይህ ህይወት ስላለው ፡ወደዚህ መንግስት
" ኑ " እንላለን ።

እንግዲ አምላኬ እንደባለጠግነቱ መጠን የሚያስፈልጋችሁን ይሙላባችሁ እንዲባል የልቦልናችሁ አይኖች በርተው የመጥራቱ ተስፋ ምን እንሆን ማወቅ ይሁንላችሁ።
===============================
ለዚሁ ነው እኛም ጌታን ሰምተን የቻናላችን ስም Goodness of christ Gospel Minstry ያልንበት ክርስቶስ ኢየሱስ በዘመነ ምድሩ ጲጥሮስ ና በለኝ ካለ በኋላ በባህሩ ላይ ትንሽ ከተራመደ በኋላ መሃል ላይ ሊሰጥም ሲል እንጁን ይዞ (አዳነው) ይላል።

ይህ ነው ትክክለኛ መልካምነት ከኢየሱስ ያገኘነው።በዘላለም ጥፋት ውስጥ እንዳንገባ፡ራሱን ሰጥቶ ወደዘላለም ሃሳቡ በበጎነቱ የሳበን።ኢየሱስ ክርስቶስ ለአለም ሁሉ በጎነቱን ገልጿል
809 viewsEjob @ JS, edited  03:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-17 06:00:45
796 viewsEjob @ JS, 03:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ