Get Mystery Box with random crypto!

ሰማያዊ ስጦታ ቤተክርስቲያን//Heaven Gift Church//

የቴሌግራም ቻናል አርማ http_gcgm — ሰማያዊ ስጦታ ቤተክርስቲያን//Heaven Gift Church//
የቴሌግራም ቻናል አርማ http_gcgm — ሰማያዊ ስጦታ ቤተክርስቲያን//Heaven Gift Church//
የሰርጥ አድራሻ: @http_gcgm
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 16.34K
የሰርጥ መግለጫ

👉መልካሙ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን
👉ማቴ 14፥30
👉ሚኒስትሪያችንን በተለያዩ ስጦታዎች
ስለምታግዙን እናመሰግናለን።
ለማንኛውም ጥያቄ እና እገዛ👇
ለፀሎት አገልግሎት ከስር ያለውን ስልክ ይጠቀሙ።
https://www.facebook.com/gcgm.gctv?mibextid=sCpJLy
👉YouTube-https://youtube.com/@melkamqine?si=vBbrpgENQkfcJ

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2023-03-17 06:13:26 ሰላም ቅዱሳን እንደምን አላችሁ ይህ የምትመለከቱት Chart መጽሃፍ ቅዱስ ውስጥ ያለውን እውነት ማወቅ እፈልጋለሁ ለሚል እና እውነቱን አውቆ ለመኖር እንዴት መጽሃፍ ቅዱስን ላንብብ ብሎ ለሚል የሚጠቅም "chart" ነው።

መሰረታዊ የመጽሃፍ ቅዱስ አነባበብ

መጽሃፍ ቅዱስን እንዴት እናጥና?
በዘመን ከፍለን እናጥና

አንድ ሰው ለምሳሌ አንድ ቋንቋ ማወቅ ከፈለገ ፡ሊያውቀው የፈለገውን ቋንቋ መሰረታዊ ትምህርቶች ሊማር ግድ እደሆነበት::

መጽሃፍ ቅዱሳዊ እውነትን ለማወቅ እና ከእግዚአብሔር ሃሳብ ጋር ለመግባባት ከፈለገ ይህን "chart" በደንብ መረዳት አለበት::

እንግዲ እደምትመለከቱት መጽሃፍ ቅዱሳዊ መረጃን በመመርኮዝ ፡መጽሃፍ ቅዱስን በዘመን ከፍሎ ማጥናትን እናያለን
መነሻ ጥቅስ 2ጢሞ 2፥15
2 Timothy 2 (KJV) - 2 ጢሞቴዎስ
15:( Study) to shew thyself approved unto God, a workman that needeth not to be ashamed, rightly dividing the word of truth.
በንኡስ ሃሳብ( study) ወይንም( አጥና)ብሎ ሃዋርያው ጳውሎስ ይናገራል ።

ይህ የሚያሳየው መጽሃፍ ቅዱስ በዘመን ከፍሎ ማጥናት መሰረታዊ የሆነ ነገር እንደሆነ ይናገራ::
መጽሃፍ ቅዱስ በዘመን ከፍሎ ማጥናት ያሰፈለገው ምክኒያት እውነተኛ የሆነ እውነት ለመያዝ ነው::

በዚህ የመጽሃፍ ቅዱስ ክፍል ላይ የጊዜ መዛባት ይታያል
2 ጢሞቴዎስ 2 (2 Timothy)
15፤ የእውነትን ቃል በቅንነት የሚናገር የማያሳፍርም ሠራተኛ ሆነህ፥ የተፈተነውን ራስህን ለእግዚአብሔር ልታቀርብ ትጋ።
16፤ ነገር ግን ለዓለም ከሚመች ከከንቱ መለፍለፍ ራቅ፤ ኃጢአተኝነታቸውን ከፊት ይልቅ ይጨምራሉና፥ ቃላቸውም እንደ ጭንቁር ይባላል፤
17፤ ከእነርሱም ሄሜኔዎስና ፊሊጦስ ናቸው፤
18፤ እነዚህም፡— ትንሣኤ ከአሁን በፊት ሆኖአል እያሉ፥ ስለ እውነት ስተው፥ የአንዳንዶችን እምነት ይገለብጣሉ።

በዘመን ከፍሎ ባለማጥታት ምክኒያት እምነታቸው እስከሚገለበጥ ድረስ ሄሜኔዎስና ፊሊጦስ "ትንሳኤ"በፊት ሆኗል በማለት የስህተት ትምህርት ሲያስተምሩ እንመለከታለን ፡ለዚህ ነው ሃዋርያው ጳውሎስ አጥና የሚለው::

ትንሳኤ ወደፊት የሚሆን ሲሆን እነሱ ግን ከዚህ በፊት ሆኗል ፡የሚል አስተምህሮት ያንጸባርቃሉ

የመጽሃፍ ቅዱስ ሶስት ዘመናት እንዳለ ይነግረናል
1.ያለፉት ዘመናት(ኤፌ 2፥11)
2. አሁን ዘመን(ኤፌ 2፥13)
3.ወደፊት ዘመን(ኤፌ 2፥7)
===============================
በቀጣይ ሳምንት
ያለፈው ዘመን ለማን ተጻፈ?ያሁኑ ዘመን ለማን ተጻፈ?የወደፊቱስ ማንን የሚያመለከት ነው?
===============================
ለተጨማሪ ጥያቄዎች-0966222852
Or Inbox us on Telegram (https://t.me/joinchat/AAAAAFMzwMKEzglqqR6tnw)
Powered by እዮብ አበራ
Goodness of Christ Gospel Ministry 
320 viewsEjob @ JS, edited  03:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-17 06:13:10
314 viewsEjob @ JS, 03:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-16 16:09:34 “Lord Jesus, I am a sinner. I need You as my Lord and Saviour. Come into my heart and wash me with Your precious blood. Save my soul today, in Jesus’ name! Thank you, Lord!”


New Soul !
940 viewsEjob @ JS, 13:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-15 13:48:11
Annual Church leaders Conference held @ Millennium hall
Day -1
876 viewsEjob @ JS, 10:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-10 06:41:03 ሰላም ቅዱሳን

ጸጋ ፍሬያማ ያደርጋል

ገላ 5፥22-23 "ፍቅር፣ደስታ፣ሰላም፣ትእግስት፣ቸርነት፣በጎነት፣እምነት፣የዋህነት፣
ራስን መግዛት"የመንፈስ ፍሬዎች እንደሆኑ ይናገራል።

ጳውሎስ ስለመንፈስ ፍሬዎች የጻፈው በአምስተኛው ምእራፍ እንደሆነ አስተውል።ምክኒያቱም የገላትያ ክርስቲያኖች ተመልሰው በህግ ስር ወድቀው ስለነበር፣ ለእነሱ ሰለ መንፈስ ፍሬዎች ከመንገሩ በፊት ወደጸጋ ሊመልሳቸው ያስፈልገው ነበር።

ስለዚህ በመጀመሪያዎቹ አራት ምእራፎች ስለጸጋ እየተናገረ፣ ጸጋን ከህጉ ጋር እያነጻጸረና በተጨማሪም በእምነት መፈረድን በመሰበክ በቅንነት እየተጋደለ ነበር።

በጸጋው ስር የመሆን ፍሬ እንዴት የመንፈስ ፍሬ እንደሆነ መመልከት ትችላለህ?

ጳውሎስ እንዴት የስጋ ስራና የመንፈስ ፍሬ ብሎ እንደሰየማቸው አስተውል

በስራ እና ፍሬ መካከል ያለው ልዩነት ምንድነው?
ስራዎች በከባድ የህግ ጥያቄዎች ስር በመሆን የሚመጡ የግል ጥረቶች ሲሆኑ
ፍሬ ደግሞ የህይወት ውጤት ነው!

አንድ ዛፍ በደንብ ውሀ ሲጠጣ እና ትክክለኛ የጸሀይ ሙቀት ሲያገኝ መልካም ፍሬ እንደሚያፈራ ሁሉ አንድ ክርስቲያንም የጸጋውን ቃል ውሀ በደንብ ሲጠጣና የእግዚአብሔርን የፍቅር ብርሀን ሲያገኝ ያለግል ጥረት መልካም ፍሬ ያፈራል።

ወዳጄ፣ የመንፈስ ፍሬ ልታሳይ የምትፈልግ ከሆነ ያለተበከለውን የጌታችንን የኢየሱስ ጸጋ እንጂ ህጉን እየሰማህ እንዳልሆነ እርግጠኛ ሁን።

ስለአንተ በሞተው በግ ባለህ እምነት እንደተፈረደልህ እንዲያስታውስህ የቀንደ መለከቱን ድምጽ እየሰማህ ለመሆንህ እርግጠኛ ሁን።
ይህ ህይወትህ በጠንካራው የክርስቶስ አለትና የተፈጸመ ስራው ጥብቅ መሰረት ላይ እንድታንጽ ይረዳሀል።
ስለዚህ እውነተኛው ወንጌል ለመስማትና በእርሱ ለመኖር በቅንነት ተጋደል።
ወንጌሉ በእምነት በኩል በጸጋው ወደ ቃልኪዳኑ ስፍራ ይወስድሀል።
===============================
በቀጣይ ሳምንት
ህግ ይጠይቃል፤ጸጋ ይሰጣል
===============================
ለተጨማሪ ጥያቄዎች-0966222852
Or Inbox us on Telegram (https://t.me/joinchat/AAAAAFMzwMKEzglqqR6tnw)
Powered by እዮብ አበራ
Goodness of Christ Gospel Ministry 
782 viewsEjob @ JS, 03:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-08 11:14:06 ትኩረታችንን ኢየሱስ ክርስቶስ ላይ ይሁን
808 viewsEjob1 Ejob, 08:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-06 13:25:29
በክርስቶስ

ወደ ኤፌሶን 1
4፤ ዓለም ሳይፈጠር፥ በፊቱ ቅዱሳንና ነውር የሌለን በፍቅር እንሆን ዘንድ በክርስቶስ መረጠን።
531 viewsEjob @ JS, 10:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-04 17:09:41 ይህን ዝማሬ ተባረኩበት


644 viewsEjob1 Ejob, edited  14:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-02 19:44:03 ልጅ ነን ወይስ መለኮት
(ክፍል 3)...ይቀጥላል...
639 viewsEjob @ JS, edited  16:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-02 19:43:15 ልጅ ነን ወይስ መለኮት(ክፍል 1)
646 viewsEjob @ JS, edited  16:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ