2022-12-02 07:07:54
እግዚአብሔር የተደሰተበት
የዮሐንስ አገልግሎት በጣም ቀጥተኛ ከመሆኑ የተነሳ ያንን የተመለከቱ ሰዎች ይመጣል ከተባለው መሲህ ከክርስቶስ ጋር እንዳስተያዩት መፅሐፍ ይናገራል::
--------------------
የዮሐንስ ወንጌል 1
19፤ አይሁድም፦ አንተ ማን ነህ? ብለው ይጠይቁት ዘንድ ከኢየሩሳሌም ካህናትንና ሌዋውያንን በላኩበት ጊዜ፥ የዮሐንስ ምስክርነት ይህ ነው።
የአገልግሎቱን ከፍታ የተመለከቱ ሰዎች አንተ በቃ ይመጣል የተባለው መሲህ ክርስቶስ ነህ በማለት ባስጨነቁት ጊዜ እሱ ግን
--------------------
የዮሐንስ ወንጌል 1
20፤ መሰከረም አልካደምም፤ እኔ ክርስቶስ አይደለሁም ብሎ መሰከረ።
ዮሐንስን በክርስቶስ ደረጃ ሰው ሁሉ ተቀብሎት ከፍ ያለ ክብርና አድናቆት እየተቸረው ሳለ ቀድሞ ዮሐንስ ከነበረው ተቀባይነትና በእድሜም ከእሱ የሚያንስ በስጋ ሲታይ እንደ ማንኛውም እስራኤላዊ የሆነ አንድ ጎልማሳ ሲመጣ ቢያየው ጊዜ የተሰጠውን ክብርና አድናቆት ሁሉ መሬት ላይ ክስክስ አደረገና እንደዚህ ብሎ ጮኸ
--------------------
የዮሐንስ ወንጌል 1
29፤ በነገው ዮሐንስ ኢየሱስን ወደ እርሱ ሲመጣ አይቶ እንዲህ አለ፦ እነሆ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ።
በዚህ ደረጃ ዮሐንስ ወደ ክርስቶስ ሲያመለክት እግዚአብሔር አምላክ ተደሰተ::ሲጠመቅ ሳለ ሰማይ ተከፍቶ መንፈስ ቅዱስ በእርግብ አምሳል ተገለጠና የዮሐንስ አገልግሎት እውቅና ሰጠው::
--------------------
የማቴዎስ ወንጌል 3
16፤ ኢየሱስም ከተጠመቀ በኋላ ወዲያው ከውኃ ወጣ፤ እነሆም፥ ሰማያት ተከፈቱ የእግዚአብሔርም መንፈስ እንደ ርግብ ሲወርድ በእርሱ ላይም ሲመጣ አየ፤
--------------------
የማቴዎስ ወንጌል 3
17፤ እነሆም፥ ድምፅ ከሰማያት መጥቶ፦ በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው፡ አለ።
በአገልግሎታችን እና በህይወታችን እግዚአብሔር እንዲደሰትና እውነተኛ ክብሩ ሲገለጥ ማየት ከወደድን ?
እግዚአብሔር የተደሰተበትን ክርስቶስን ሰምተን
ኑሯችን ;ህይወታችን ;ትምህርታችን ሁሉ ኢየሱስን የሚገልጥ መሆን አለበት።
በዘመን መጨረሻ ያለው ሃሳቡ አለማትን በክርስቶስ መጠቅለል ነው።
ደስታውን መፈጸም ይሁንልን።
ብሩካን ናችሁ!
780 viewsEjob @ JS, 04:07