Get Mystery Box with random crypto!

ሰማያዊ ስጦታ ቤተክርስቲያን//Heaven Gift Church//

የቴሌግራም ቻናል አርማ http_gcgm — ሰማያዊ ስጦታ ቤተክርስቲያን//Heaven Gift Church//
የቴሌግራም ቻናል አርማ http_gcgm — ሰማያዊ ስጦታ ቤተክርስቲያን//Heaven Gift Church//
የሰርጥ አድራሻ: @http_gcgm
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 16.34K
የሰርጥ መግለጫ

👉መልካሙ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን
👉ማቴ 14፥30
👉ሚኒስትሪያችንን በተለያዩ ስጦታዎች
ስለምታግዙን እናመሰግናለን።
ለማንኛውም ጥያቄ እና እገዛ👇
ለፀሎት አገልግሎት ከስር ያለውን ስልክ ይጠቀሙ።
https://www.facebook.com/gcgm.gctv?mibextid=sCpJLy
👉YouTube-https://youtube.com/@melkamqine?si=vBbrpgENQkfcJ

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 10

2022-11-26 15:32:30
"በክርስቶስ"
አድራሻ ኢማና መጽሐፍት መደብር ቦሌ ጌቱ ኮሜርሻል ሴኔተር
1.1K viewsEjob1 Ejob, edited  12:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-25 18:41:26
መልካም ዜና
ለGoodness Of Christ Gospel Ministry ወዳጆቻችን በሙሉ “በክርስቶስ “የተሰኘው መጽሃፌ ለሁለተኛ ጊዜ ታትሞ በይፍ በነጻ መሰጠት ተጀመረ
መጽሐፉን ለማግኘት
+251966222852 ይደውሉ ወይ telegram ላይ ያነጋግሩ።
ወይም
ቦሌ ጌቱ ኮሜርሻል ህንጻ ኢማና መጽሐፍት መደብር ማግኘት ትችላላችሁ
ከአዲስ አበባ ውጪ ላላችሁ በፖስታ ቤት እንልካለን አሳውቁን

1.0K viewsEjob @ JS, edited  15:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-25 06:11:12 ሰላም ለእናንተ...
የGoodness Of Christ Gospel Ministry ወዳጆች ዛሬ ደግሞ አንድ እውነት ልንገራችሁ...
ርእስ፦ለኔ ሕይወት ክርስቶስ ነው

ፊልጵስዩስ 1:21 እንዲህ ይላል፣ “ለእኔ ሕይወት ክርስቶስ፥ ሞትም ጥቅም ነውና።” ብዙ ሰዎች፣ “…ሞትም ጥቅም ነውና።” በሚለው በጥቅሱ ሁለተኛ ክፍል ላይ በማተኮር አማኝ ከሞት በኋላ ስለሚገጥመው የሰማይ ደስታ ብቻ ሲያወሩ ይሰማል። ሆኖም የጥቅሱን ቀዳሚ ክፍል ማለትም፣ “ለእኔ ሕይወት ክርስቶስ…ነው” የሚለውን ችላ ማለት የለብንም፡፡ እውነቱን ለመናገር፣ “ለእኔ ሕይወት ክርስቶስ…ነው” የሚለው ሐረግ ለእያንዳንዱ ክርስቲያን ሕይወት ማዕከላዊ ሃሳብ መሆን ያለበት ነው፡፡
በዚህ ጥቅስ ውስጥ የምንመለከተው፣ ሐዋሪያው ጳውሎስ ጌታ ኢየሱስን መከተል ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ የሆነው እና ለመሆነ ያሰበው ነገር ሁሉ ክርስቶስ ኢየሱስን ማእከል ያደረግ መሆኑን ነው፡፡ ከተለወጠበት ጊዜ አንስቶ እስከ ሰማዕትነቱ ድረስ የወሰደው እያንዳንዱ እርምጃ ወንጌልን ላልሰሙ ሁሉ በማዳረስና ቤተክርስቲያንን በማሳደግ ላይ ያነጣጠረ ነበር፡፡ የጳውሎስ የሕይወት ዘመን ነጠላ ዓላማ፣ ለኢየሱስ ክርስቶስ ክብር ማምጣት ብቻ ነበር፡፡
“ለእኔ ሕይወት ክርስቶስ…ነው” ለእኔ ሕይወት ክርስቶስ…ነው” ማለት የክርስቶስን ወንጌል በጊዜውም ያለጊዜውም ማወጅ ማለት ነው፡፡ ጳውሎስ በምኩራቦች ሰብኳል፤ በወንዝ ዳርቻዎች ሰብኳል፤ እንደ እስረኛ ሰብኳል፤ እንደ ሐዋርያ ሰብኳል፤ እንደ ድንኳን ሰፊ ሰብኳል፡፡ በዚህ ሁሉ ግን መልእክቱ ወጥ እና አንድ ነበር፣ “…ከኢየሱስ ክርስቶስ በቀር እርሱም እንደተሰቀለ ሌላ ነገር” እንዳያውቅ መቁረጡ (1ኛ ቆሮንቶስ 2:2)። የክርስቶስን ቤዛዊ መስዋዕትነት ለነገሥታቶች፣ ለወታደሮች፣ ለገዥዎች፣ ለካህናትና ፈላስፋዎች፣ ለአይሁድና ለአህዛብ፣ ለወንዶችና ለሴቶች፣ በአጭሩ ሊሰሙት ለሚወዱ ሁሉ ሰብኳል፡፡
“ለእኔ ሕይወት ክርስቶስ…ነው” ማለት የክርስቶስን ምሳሌነት መከተል ማለት ነው። ኢየሱስ ያደረገውን እና የተናገረውን ነገር ሁሉ ነበር ጳውሎስ ማድረግ እና መናገር የፈለገው። ቤተ ክርስቲያን ከጳውሎስ የምሳሌነት ሕይወት ተጠቅማለች፣ “እኔ ክርስቶስን እንደምመስል እኔን ምሰሉ” (1 ኛ ቆሮንቶስ 11:1)። “ዛሬ ኢየሱስ በምድር ላይ ቢኖር ኖሮ ምን ያደርግ ነበር?” የሚለውን ጥያቄ ራሳችንን መጠየቅና ተግባራዊ ምላሹን በእርሱ ፈንታ እኛ ማድረጋችንን መገምገም የእርሱን ምሳሌያዊ ሕይወት እየተከተልን መሆን አለመሆናችንን ለመለካት ጥሩ መሣሪያ ነው።
“ለእኔ ሕይወት ክርስቶስ…ነው” ማለት ክርስቶስን ማወቅ ማለት ነው፡፡ በየቀኑ ክርስቶስን ከትላንትናው በተሻለ ለማወቅ እንፈልጋለን ማለት ነው፡፡ ይህ ማለት ግን፣ ስለ ክርስቶስ አንዳንድ እውነታዎችን ማወቅ ብቻ ሳይሆን
ክርስቶስ ራሱን ማወቅን ይጨምራል፡፡ “እርሱንና የትንሣኤውን ኃይል እንዳውቅ፥ በመከራውም እንድካፈል፥ ወደ ሙታንም ትንሣኤ ልደርስ ቢሆንልኝ፥ በሞቱ እንድመስለው እመኛለሁ”  (ፊልጵስዩስ 3:10-11)፡፡
“ለእኔ ሕይወት ክርስቶስ…ነው” ማለት ከክርስቶስ ጋር የጠበቀ ሕብረት እንዳይኖረን የሚከለክለንን ማንኛውንም ነገር ለመተው ፈቃደኛ ነን ማለት ነው፡፡ በዚህ ረገድ የጳውሎስ ምስክርነት አስገራሚ ነው:- “ነገር ግን ለእኔ ረብ የነበረውን ሁሉ ስለ ክርስቶስ እንደ ጉዳት ቈጥሬዋለሁ። አዎን፥ በእውነት ከሁሉ ይልቅ ስለሚበልጥ ስለ ክርስቶስ ኢየሱስ ስለ ጌታዬ እውቀት ነገር ሁሉ ጉዳት እንዲሆን እቈጥራለሁ፤ ስለ እርሱ ሁሉን ተጐዳሁ፥ ክርስቶስንም አገኝ ዘንድ፥ በክርስቶስም በማመን ያለው ጽድቅ ማለት በእምነት ከእግዚአብሔር ዘንድ ያለው ጽድቅ እንጂ ከሕግ ለእኔ ያለው ጽድቅ ሳይሆንልኝ፥ በእርሱ እገኝ ዘንድ ሁሉን እንደ ጕድፍ እቈጥራለሁ፤”(ፊልጵስዩስ 3:7-9)። ከዚህ የመስዋዕትነት ሕይወት ጎን ለጎን በማርቆስ 10፥29-30 ውስጥ የተሰጥውን የተስፋ ቃል ማስታወስ እጅግ አበረታች ነው:- “ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለ፦ እውነት እላችኋለሁ፥ ስለ እኔና ስለ ወንጌል ቤትን ወይም ወንድሞችን ወይም እኅቶችን ወይም አባትን ወይም እናትን ወይም ሚስትን ወይም ልጆችን ወይም እርሻን የተወ፥ አሁን በዚህ ዘመን ከስደት ጋር ቤቶችን ወንድሞችንና እኅቶችንም እናቶችንም ልጆችንም እርሻንም መቶ እጥፍ፥ በሚመጣውም ዓለም የዘላለም ሕይወት የማይቀበል ማንም የለም።”
ለእኔ ሕይወት ክርስቶስ…ነው” ማለት ክርስቶስ የእኛ ዋና ትኩረት፣ ዋና ግብ እና ዋና ፍላጎታችን ነው ማለት ነው፡፡ በዚህ ጊዜ ክርስቶስ የአዕምሯችን፣ የልባችን፣ የአካላችን እና የነፍሳችን ማዕከል ይሆናል፡፡ የምናደርገውን ነገር ሁሉ ለክርስቶስ ክብር እናደርጋለን፡፡ “ሸክምን ሁሉ ቶሎም የሚከበንን ኃጢአት” በማስወገድ “የእምነታችን.. ራስና ፈጻሚውን ኢየሱስን ተመልክተን፥ በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግሥት” እንሮጣለን (ዕብ. 12:1-2)። 

https://t.me/http_GCGM
178 viewsEjob1 Ejob, 03:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-23 14:31:12 1ኛ ሳሙኤል 1
17፤ ዔሊም፦ በደኅና ሂጂ፥ የእስራኤልም አምላክ የለመንሽውን ልመና ይስጥሽ፡ ብሎ መለሰላት።


እግዚአብሔር የለመናችሁትን ይስጣችሁ::
461 viewsEjob @ JS, 11:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-22 15:16:46 ስለሆነላችሁ ነገር ሁሉ ፥በጸሎት ስለተመለሰላችሁ ነገሮች ሁሉ ክብሩን እግዚአብሔር ይውሰድ።(JS)
476 viewsEjob1 Ejob, edited  12:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-18 06:01:16 ሰላም ለእናንተ
የGoodness Of Chirst Gospel Ministry ወዳጆች

           የኢየሱስን ዋጋ መግለጥ

ዛሬ ላይ  በአለም ዙሪያ ያሉ ሰዎች የመኖሪያ ቤቶች ፥የእቃና በአክሲዮን ገበያ ውስጥ ያሉ በደባባይ የሚሸጡ የሚለወጡ ኩባንያዎችን ዋጋ ሲያውቁ የኢየሱስን ዋጋ አያውቁም።

አንተ ግን የጌታችን የኢየሱስን ዋጋ ስለተረዳህና  ኢየሱስ ስለተባለው ሰው ብቻ የሚያወራውን ይህን መጽሃፍ ለማንበብ ጊዜ ስለወሰድክ በጣም ደስ ብሎኛል።

የጸጋው አብዮት በአጠቃላይ ኢየሱስን ስለመግለጥ በመሆኑ፣ የኢየሱስ ዋጋ፣ ማን እንደሆነ ፣ ምን እንዳደረገና ዛሬም በአንተ ህይወት ወስጥ ምን እየሰራ እንደሆነ ስትረዳ ፣ በህይወትህ ውስጥ የጸጋውን አብዮት ሲካሄድ ታያለህ ።
ከጌታ ከኢያሱስ ጋር ድግሞ የግል ግንኙነት ሲኖርህ ደግሞ ከወደቀበት በላይ መኖር ትጀምራለህ።

ሰዎች ሰለእምነት ፣ ስለህግና ጸጋ፣ ሰለ ሃጥያት ፣ ስለንስሃ ፣ ስለዘላለማዊ ደህንነትና ስለተለያዩ  መጽሃፍ ቅዱሳዊ ትርጓሚዎች ይከራከራሉ እስቲ እኔ እያንዳንዱን እምነት፣አስተምህሮ እና መጽሃፍ ቅድይሳዊ ትርጓሜዎችን እንዴት እንደምትመረምር ላካፍልህ።

አንድ ትምህርት በሰማህ ጊዜ፣ ያ ትምህርት ጌታ ኢየሱስን እንድታመልከው እና በህይወትህ እንድታከብረው እንድትፈልግ አድርጎሃል ወይስ ብዙውን ዋጋ የጣለው በአንተ እና አንተ ማድረግ ባለብህ ነገር ላይ ነው?
ኢየሱስ በተባለው አካል ላይ እንድትመሰረትና በእርሱ እንድትሞላ አድርጎሃል?
ወይስ በስኬትህና በውድቀትህ ላይ በመመስረት በእርሱ እንድትሞላ ወይስ በራስህ እንድትያዝ አድርጎሃል?
በዚህ አስተምህሮ ውስጥ ጌታችን ኢየሱስ እንዴት ያለ ዋጋ  ነው የሰጠው?ብለህ ጠይቅ።

ታዲያ ስራ መስራት አይጠቅምም እያልክ ነው?
በጭራሽ አይደለም!ስራ ለመስራት ቁልፉ ያለው በህይወትህ ውስጥ ባለው በእርሱ ፍቅር ፣ጸጋና ባልተከፈለበት ሞገስ ነው እያልኩ ነው!በፍጹም መወደድህን ስታውቅ የእውነት መስራፍ ይቻልሃል።
===============================
በቀጣይ ሳምንት
የአምልኮ ልብ
===============================
ለተጨማሪ ጥያቄዎች-0911690964
Or Inbox us on Telegram (https://t.me/joinchat/AAAAAFMzwMKEzglqqR6tnw)
Powered by እዮብ አበራ
Goodness of Christ Gospel Ministry 
529 viewsEjob1 Ejob, 03:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-17 11:59:35
መልካም ዜና
ለGoodness Of Christ Gospel Ministry ወዳጆች ሁለተኛ እትም "በክርስቶስ"የሚለው መጽሃፌ በቅርቡ ወደእናንተ ይደርሳል።
ተባረኩ!

ማሳሰቢያ፦በነጻ የሚከፍፈል ስለሆነ
ለወንጌል ስርጭት ይጠቅመናል የምትሉ ወዳጆቻችን ከአሁኑ በtelegram አስታውቁን።
795 viewsEjob1 Ejob, edited  08:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-16 20:24:14 Subscribe አድርጉላቸው




1.3K viewsEjob @ JS, 17:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-12 15:34:12 እንደሰው ከባድ የሚመስል ነገር ሁሉ
እንደእግዚአብሔር ግን ቀላል ነው ስለዚህ ለእግዚአብሔር ስጡት
861 viewsEjob1 Ejob, 12:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-11 06:14:27 እውነተኛው አምላክ እና አዲሱ ሰው
አዲሱ ሰው እና የማይታወቅ አምላክ ተብሎ የተጠራው አምላክ
ሰላም ለእናንተ....
Acts 17 (WEB) -
23: For as I passed along, and observed the objects of your worship, I found also an altar with this inscription: 'TO AN UNKNOWN GOD.' What therefore you worship in ignorance, this I announce to you.

አማርኛ - የማይታወቅ አምላክ
English-Uknown God
Ancient Greek-Agnostos Theos
ይህን ልብ በማለት

                    1.ክርስትና

ክርስቲያን ተብለው የሚጠሩ አማኞች፡የእምነት መጠሪያቸው ሲሆን ፍቺውም "ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ " እንደሆነ የሚያምኑ ሰዎች መጠሪያ ሆኖ ያገለግላል:: አዲሱ ሰው ከነዚህ አማኞች ጎራ ነው:: ለምን አዲሱ ሰው ብዙ የእምነት አይነቶች በአሁኑ ዘመን እያሉ "ክርስትና" ላይ አተኮረ ካላችሁ.....

በመጀመሪያ የክርስትና ሃሳብ አጀማመር እና አቋም እንመልከት እና ሌሎቩንም በዘመናት መካከል የሚገኙትን የእምነት አይነቶች ተመልክተን ከዚያ ድምዳሜ  ላይ ለመድረስ እንሞክራለን::

ክርስትና የተባለው አሳብ መሰረት ያደረጉት ብሉይ ኪዳን እና አዲስ ኪዳን  ላይ ሲሆን:: በህብረትም ሆነ በግል ሆነው ለአምላካቸው እውቅና ለመስጠት እና  እራሳቸውን ሆነ ሌሎችን ለማነጽ፡ለመምከር ፡ለመገሰጽ፡ለማስተማር መጽሃፍ ቅዱስ ከአምላክ የተላከ በተመረጡ ሰዎች ተጽፈዋል በማለት  ይጠቀሙበታል።

ይህ እምነት በዋናነት ጎልቶ የወጣው ጴንጤናዊው ጲላጦስ ገዢ በነበረበት ዘመን ኢየሱስ በኢየሩሳሌም ከተሰቀለ በኋላ ነው።

በዋናነትም
እግዚአብሔር አብ "አባት"፡
እግዚ አብሔር ወልድ "ልጅ"
እግዚአብሔር መንፈስ "መንፈስ ቅዱስ"
ብለው ያምናሉ እና ሞት፡ትንሳኤ፡የኢየሱስ ክርስቶስ መምጣት ላይ ጽኑ አቋም ያላቸው አማኞች የሚጠሩበት ነው።

የዚህ እምነት አራማጆች  "ባለአምሳ ቀን" በተባለበት ቀን ክርስቶስ ኢየሱስ ከሞተ በኋላ ፡ተሰብስበው በህብረት በመሆን
ቤተ-ክርስቲያን (ኤክሊዢያ)፥ መስርተዋል:: በአብዛኛው በዚህ ህብረት ውስጥ የነበሩት " አይሁዳዊ" ሲሆኑ ቤተ-ክርስቲያን የመሰረቱት እየሩሳሌም ውስጥ ነበር:: ከተመሰረተም በኋላ ብዙ አህዛቦች ክርስቲያን የመሆን እድል አግኝተዋል።

በዋናነትም "ወንጌል" ወይም "የምስራች ቃል" ለመናገር እና ለማብሰር እንደተጠሩ ያምናሉ።
12 መሪ ሆነው በክርስቶስ ኢየሱስ ከተመረጡት ጨምሮ በዋናነት ወንጌልን አተኩሮ ይሰራ የነበረ ቀድሞ አሳዳጅ የነበረ ከዚያም የወንጌል ወዶ ዘማች የሆነው ሓውርያ ሊሆን የተጠራው  ጳውሎስ ለዚህ ተምሳሌት ተደርገው ይወሰዳሉ::

በ64 A.D"ንጉስ ኔሮ" ገዢ በነበረበት ሰአት ከባድ ስደት የተፈጠረባቸው እንደሆነ ይነገራል፡በተጨማሪም በ 313 A.D ትልቅ ስደት ተፈጥሮባቸዋል።

ይሕ ሁሉ ከሆነባቸው በኋላ
በድጋሚ የተነሳው የወንጌል  አብዮት እንዴት ነበር ሳምንት ይጠብቁን
===============================
በቀጣይ ሳምንት
በድጋሚ የተነሳው የወንጌል  አብዮት እንዴት ነበር
===============================
ለተጨማሪ ጥያቄዎች-0966222852
Or Inbox us on Telegram (https://t.me/joinchat/AAAAAFMzwMKEzglqqR6tnw)
P. እዮብ አበራ
Goodness of Christ Gospel Ministry 
655 viewsEjob1 Ejob, edited  03:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ