2022-08-23 20:44:35
ነሐሴ ፲፯/፳፻፲፬ ዓ.ም
ምዕራፍ ፪
ግስ
፪
.፩. ግስ እና የግስ አይነቶችከዚህ በፊት እንዳየነው የአንድ ቋንቋ የተለያዩ የቃል ክፍሎች አሉት። እነዚህ የቃል ክፍሎችም መራሕያን፣ ግስ፣ ተውሳከ ግስ፣ ስም፣ ቅጽል፣ መስተዋድድ፣ መስተጻምር የመሳሰሉት ናቸው።
#ግስ ከእነዚህ የቃል ክፍላት መካከል ሲኾን "ገሰሰ" ከሚለው የግእዝ ቃል የተገኘ ነው። ትርጕሙም ዳሰሰ፥መረመረ ማለት ነው። ግስ ማለት ደግሞ የሚዳሰስ፣ የሚመረመር ማለት ነው።
ግስ ማለት በአጭር ቃል ሲገለጥ በአንድ ዐረፍተ ነገር ውስጥ #ድርጊትን_ገላጭ_ዐረፍተነገርን_የሚቋጭ ቃል ማለት ነው።
<<ለምሳሌ፦ ዳዊት በሬ ገዝቶ
_።>>
ብለን ብንጽፍ ዐረፍተ ነገሩ አልተቋጨም፣ ማሰሪያ፣ መጠቅለያ ቃል ያስፈልገዋል።
በክፍት ቦታው መጣ፣ ሄደ፣ ተቀመጠ፣ አረሰ፣ ወዘተ.... የመሳሰሉ ግሶችን መሙላት ይቻላል።
#ግስ- በዐረፍተ ነገር ውስጥ ድርጊቱ #በማን፣ #በማን_ላይ መፈጸሙን የሚነግረን ቃል ነው። ድርጊትን የሚገልጥ፣ መሆን አለመሆንን የሚያሳይ የቃል ክፍል ነው።
የግስ ምሳሌዎች፦
በልዐ = በላ
ሖረ = ሄደ
ተንበለ = ለመነ
ቀደሰ = አመሰገነ
ቀተለ = ገደለ
አእመረ = አወቀ
ተፈነወ =ተላከ
ተገብረ = ተሠራ
..........ወዘተረፈ
፫.፪.
ኅብራተ ግስ (የግስ አይነቶች)
አባቶች ግስን ለጥናት እንዲመቻቸው በተለያየ መንገድ ከፍለው ያጠኗቸዋል።
ከድርጊት ከመግለጽ አንጻር ግሶች በሁለት ይከፈላሉ
፩. ገ
ቢር ግስ (አድራጊ ግስ)
ይህ አይነት ግስ በአንድ አረፍተ ነገር ውስጥ ድርጊት የአድራጊነትን ወይም ፈጻሚነትን ኹነት የሚገልጥ፣ ቃላትንና ሐረጋትን የሚስብ ነው። በዐማርኛው አድራጊ ግስ፣ በእንግሊዝው active verb (active voice) የምንለው ነው።
ምሳሌ አንድ፦
አብርሃም መርሐ ማኅበረነ።
(አብርሃም ማኅበራችንን መራ።)
ከዚህ ምሳሌ የምረዳው ግሱ #መርሐ የሚለው አድራጊ ግስ መሆኑን ነው። አብርሃም የተባለው ሰው መምራት የተባለውን ድርጊት በማኅበሩ ላይ እየተገበረ ነው።
አብርሃም #ምን_አደረገ ? ብለን ብንጠይቅ #መርሐ - መራ የሚል መልስ እናገኛለን።
#ማኅበረነ የሚለው ቃል ደግሞ ተሰሐቢ ቃል፣ ድርጊቱ የተፈጸመበት ነው።
አብርሃም #ማንን_መራ ብለን ብንጠይቅ ማኅበሩን የሚል መልስ እናገኛለን።
ምሳሌ ሁለት፦
እግዚአብሔር ገብረ ሰማየ ወምድረ።
(እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን ፈጠረ።)
ከዚህ ምሳሌ የምንረዳው #ገብረ የሚለው ግስ ገቢር ግስ (አድራጊ ግስ) መሆኑን ነው። ገብረ = ሠራ፣ ፈጠረ
<<እግዚአብሔር ገብረ ሰማየ ወምድረ>> በሚለው ዐረፍተነገር ውስጥ እግዚአብሔር መፍጠር የተባለ ድርጊት መፈጸሙን ያስረዳናል።
➻ማን ፈጠረ ብለን ሰንጠይቅ ድርጊት ፈጻሚውን እናገኛለን።
➻ማንን ፈጠረ ስንል ተስሐቢውን/የድርጊቱን ተቀባይ እናገኛለን።
ሰማየ ወምድረ- ሰማይንና ምድርን የሚለውን እናገኛለን
ገቢር ግስ(አድራጊ ግስ) በአንድ ዐረፍተ ነገር ውስጥ #ማን ብለን ስንጠይቅ ድርጊቱ በማን መፈጸሙን የሚነገረን፣ #ማንን ብለን ስንጠይቅ ድርጊቱን በማን ላይ እንደተፈጸመ የሚነግረን፣ ድርጊት ፈጻሚ አመልካች ቃል ወይም ሐረግ ተሰሐቢ የግስ አይነት ነው።
፪. ተ
ገብሮ ግስ (ተደራጊ ግስ)
ይህ የግስ አይነት ድርጊቱ በማን ላይ እንደተፈጸመ፣ የድርጊት ተቀባይ አካልን የሚነግረን የግስ አይነት ነው። በዐማርኛው ተደራጊ ግስ፣ በእንግሊዝው passive verb (passive voice) የምንለው ነው። ቃል ወይም ሐረግ አይስብም።
ምሳሌ፦
ክርስቶስ ተሰቅለ በዲበ መስቀል።
(ክርስቶስ በመስቀል ላይ ተሰቀለ።)
በዚህ ምሳሌ ላይ ማን #እንደሰቀለ ሳይሆን #እንደተሰቀ ይነግረናል።
#ማን_ተሰቀለ ብለን ስንጠይቅ ድርጊቱ የተፈጸመበትን አካል ይነግረናል።
ይህ ግስ የሚገኘው ገቢር ግስ ላይ መነሻ ቅጥያ <ተ> በመጨመር ነው።
ገቢር
ግስ ተገብሮ ግስ
ገብረ ተገብረ
ሰቀለ ተሰቅለ
ሰብሐ ተሰብሐ
ጸሐፈ ተጽሕፈ
የተገብሮ ግሶች መነሻቸው <ተ> ፊደል ናት።
ለብዉ-- አስተውሉ፦
በ <ተ> የሚጀምር ቃል ሁሉ ተገብሮ ግስ አይደለም።
ለምሳሌ፦ ተንበለ - ለመነ፣ ተመነየ -ተመኘ የመሳሰሉ ቃላት ገቢር ግሶች ናቸው።
በ<ተ> የሚጀምር ግስ የተገብሮ ግስ መሆኑን የምንለየው የተሰጠንን ግስ <ተ>ን አውጥተው የቀረው ቃል ገቢር ግስ ከኾነ ነው።
ምሳሌ፦
ሀ) ዳዊት በልዐ ኅብስተ። (ዳዊት ምግብን በላ። )
ለ) ዮም ተቀደሰ ቅዳሴ። (ዛሬ ቅዳሴ ተቀደሰ።)
፩} የግስ አይነት
ሀ) ግስ ፦ በልዐ = በላ
የግስ አይነት፦ ገቢር ግስ
ለ) ግስ ፦ ተቀደሰ = ተቀደሰ፣ ተመሰገነ
የግስ አይነት፦ ተገብሮ ግስ
፪} ገቢር ግስ ወደ ተገብሮ፣ ተገብሮ ወደ ገቢር ግስ ሲቀየር
ገቢር ግስ ተገብሮ ግስ
ሀ) በልዐ ተበልዐ
ለ) ቀደሰ ተቀደሰ
የተሰመረበት ግስ የተቀየረው ግስ ነው።
#በልዐ የሚለው #ገቢር ግስ ወደ #ተገብሮ ግስ ሲቀየር #ተበልዐ ይሆናል።
#ተቀደሰ የሚለው #የተገብሮ ግስ ወደ #ገቢር ሲቀየር #ቀደሰ ይሆናል።
(ይቀጥላል)
@GeezMediaCenter
877 viewsedited 17:44