Get Mystery Box with random crypto!

መሰንቆ ለኢትዮጵያ🇪🇹

የቴሌግራም ቻናል አርማ mesenqo_le_ethiopia — መሰንቆ ለኢትዮጵያ🇪🇹
የቴሌግራም ቻናል አርማ mesenqo_le_ethiopia — መሰንቆ ለኢትዮጵያ🇪🇹
የሰርጥ አድራሻ: @mesenqo_le_ethiopia
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.05K
የሰርጥ መግለጫ

አዳዲስ ኦርቶዶክሳዊ ዝማሬዎችን በፍጥነት ወደ እናንተ እናደርሳለን
የመሰንቆ ለኢትዮጵያ የ You tube chanal SUBSCRIBE በማድረግ እንድትተባበሩን በአክብሮት እንጠይቃለን
https://youtube.com/channel/UCFzrMygm7EdfxM3zVQ-zmDQ
for any coment
👇👇👇👇
@mesenqo_le_ethiopia_bot
@masin_ethio

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-20 14:31:33

212 viewsMelke , 11:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-04 13:59:07 ፀሐይ ብርሃን ካልሰጠች ፀሐይ አትባልም፤ ብርሃን አለመስጠት ተፈጥሮዋ አይደለምና፡፡ እንስሳት ካልተነፈሱ እንስሳት አይባሉም፤ መተንፈስ ተፈጥሮአቸው ነውና፡፡ ዓሣ ከውኃ ከወጣ ሕይወት ያለው ዓሣ መኾኑ ይቀርና ይሞታል፡፡ አንድ ክርስቲያንም እውነተኛ ክርስቲያን የሚባለው፡-

#ሲጸልይ_ነው፡፡ ክርስቲያን ማለት በወልድ ውሉድ በክርስቶስ ክርስቲያን በመንፈስ ቅዱስም መንፈሳዊ መባል ነውና፡፡ ልጅ ከኾኑ ደግሞ አባትን ማናገር ክርስቲያናዊ ተፈጥሮ ነውና፡፡

#ሲያመሰግን_ነው፡፡ ክርስቲያን ማለት እግዚአብሔር ፈጣሬ ዓለማት ነው ብሎ ማመን ነውና፡፡ ስለዚህ ለአንድ ክርስቲያን የሰማይና የምድር ውበት እየተመለከተ እግዚአብሔርን ማመስገኑ ክርስቲያናዊ ተፈጥሮው ነው፡፡

#ሲመጸውት_ነው፡፡ ክርስቲያን ማለት ሀብት ኹሉ ከእግዚአብሔር እንደ ኾነ መመስከር ነውና፡፡ ስለዚህ ራስን እንደ መልእክተኛ አድርጎ በመቁጠር ያለውን ለሌላው ማካፈል ክርስቲያናዊ ተፈጥሮው ነውና፡፡

#ቅዱሳት_መጻሕፍትን_ሲያነብ_ነው፡፡ ክርስቲያን ማለት በመንፈስ ቅዱስ ሀብት ደስ የሚሰኝ ነውና፡፡ይህን ለማድረግ ደግሞ መንፈስ ቅዱስ በቅዱሳት መጻሕፍት በኩል ሲናገር መስማት ለአንድ ክርስቲያን ክርስቲያናዊ ተፈጥሮው ነውና፡፡
400 viewsmesii, 10:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-25 23:03:04 #ገብርኤል

ገብርኤል አማልደን ከአምላካችን /2/ 
እንዳንጠፋ እንዳንሞት በነፍሳችን 
አደራህን ቁምልን ከጎናችን /2/

@mesenqo_le_ethiopia
517 viewsmesii, edited  20:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-25 22:52:02 #ሕፃን_ወእሙ

ሕፃን ወእሙ /4/ 
ክልዔሆሙ ፈጸሙ ገድሎሙ/4/

@mesenqo_le_ethiopia
                   
424 viewsmesii, edited  19:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-25 22:50:59 በክራር

@mesenqo_le_ethiopia
373 viewsmesii, 19:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-25 22:40:42
323 viewsmesii, 19:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-25 22:37:09 ​​ የቀጠለ

እኒኽም ቅዱሳን ይኽንን በሚነጋገሩበት ጊዜ በውስጡ አንገትን የሚቆለምም ልብንም የሚያቀልጥ ሆድን የሚሰነጥቅ ሥርን የሚበጣጥስ መሳሪያ ካለበት የብረት ጋን ውስጥ ጨመራቸው፡፡ ከዚህ በኋላ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወረደና የብረቱን ጋን እሳት አጠፋው፡፡ ከቅዱሳኑም አንዳቸውንም ሳያቃጥላቸው የብረቱ ጋር ማቃጠሉና መፍላቱ ጸጥ አለ፡፡

ወንድሞቻችን ሆይ እንግዲህ በጭንቃቸው ጊዜ ገድላቸውን እስኪፈጽሙ ድረስ ይህ መልአክ ከሰማእታትና ከጻድቃን ጐን እንደማይለይ እወቁ ለኃጥአንም ኃጢአታቸውን ይቅር ይላቸው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ይጸልይላቸዋል፡፡ እኛም የዚህ የሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል በዓሉን እያከበርን አማላጅና ወዳጅ እናድርገው። በዚህም በሚመጣውም ዓለም ሊረዳን ይችላልና፡፡

ዳግመኛም መስፍኑ ሐሳቡ ሳይሳካለት ስለቀረ 14 የሾሉና የጋሉ የብረት ችንካሮች አምጥተው ሰባቱን በእናቱ በኢየሉጣ አካል ሰባቱን በራሱ በቂርቆስ አካል ማለት ሁለቱን በጆሮዎቹ ሁለቱን በዐይኖቹ ሁለቱን በአፍንጫዎቹ አንዱን በልቡ ይቸነክራቸው ዘንድ ጭፍሮቹን አዘዘ፡፡ ዳግመኛም የህፃኑን የእራስ ቆዳ ገፈው እሳት ውስጥ ይጨምሩ ዘንድ አዘዘ፡፡

አሁንም መልአኩ መጥቶ ይህንን መከራ ከእርሱ አራቀለት፡፡ ቀጥሎም በመቃን ውስጥ ጨምረው በገመድ እንዲጎትቱት አዘዘ፡፡ በዚህም ጊዜ መልአኩ አዳነው፡፡ ሕዝቡም ይህንን ሁሉ ተአምር ባዩ ጊዜ እግዚአብሔርን አመሰገኑት ቅዱስ ገብርኤልንም አከበሩት፡፡ ቅዱስ ቂርቆስና ቅድስት እየሉጣ ብዙ መከራ ከተቀበሉ በኋላ ጥር 15 በሰይፍ ተመትተው ስማትነትን ተቀብለዋል።

የሊቀ መላእክት የቅዱስ ገብርኤል ፣ ቅዱስ ቂርቆስና የእናቱ የቅድስት እየሉጣ ተራዳኢነት ጸሎት አይለየን። ከዚህ በኋላ ሕፃኑን አስፈልገው ቢጠይቁት ነቢዩ ዳዊት የተናገረው ኃይለ ቃል መንፈስ ቅዱስ ተገልጾለት፤ ‹‹የአሕዛብ ጣዖታት የወርቅና የብር የሰው እጅ ሥራዎች ናቸው፡፡ የሚታመኑባቸውም ሁሉ እንደ እነርሱ ይሁኑ›› መዝ. ፻፴ በማለት ሲዘልፏቸው አገር ገዥው ሰምቶ ተቆጣና የብረት ጋን አስመጥቶ ውኃ ሞልቶ ከዕቶን እሳት ላይ ጥዶ ልዩ ልዩ ማገዶዎች በመጨመር ነበልባሉ ከመጠን በላይ ሆነ፡፡ የብረት ጋኑም ድምፅ እንደ ክረምት መብረቅና ነጎድጓድ እስኪያስፈራ ድረስ አስነድዶ ሕፃኑን ከነእናቱ ወስዳችሁ ጨምሩአቸው ብሎ አዘዘ፡፡

በዚህ ጊዜ ቅድስት ኢየሉጣ በጣም ፈራች፡፡ የእግዚአብሔር ሥራ እፁብ ድንቅ ግሩም ረቂቅ ነው፡፡ ገና አፉን ያልፈታ የሦስት ዓመት ሕፃን ‹‹እናቴ ሆይ! ገድላችን እንፈጽም ዘንድ ጨክኝ በርቺ›› አላት፡፡ ቅድስት ኢየሉጣም ‹‹ልጄ የነፍስ አባት ሁነኝ›› አለችው፡፡ ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስም ከዘመናቸው ሳይደርስ፣ ታሪካቸውን ሳይማር የሠለስቱ ደቂቅን ታሪክ መንፈስ ቅዱስ ገልጾለት ‹‹አናንያን፣ አዛርያንና ሚሳኤልን ያዳነ አምላክ ያድነናል›› ቢላት ፍርሃቱ ሊለቃት ባለመቻሉ፣ ወደ እግዚአብሔር እንዲህ ሲል ጸለየ፡፡

‹‹ጌታ ሆይ! የወይኑን ፍሬ ስትሻ ግንዱን ታጠፋለህን? እንደዚህስ ሁሉ እኔን አድነህ እናቴን ታጠፋታለህን?›› ብሎ በጸለየጊዜ መንፈስ ቅዱስ አደረባትና መንግሥተ ሰማያትን በዓይነ ሥጋ እንድታይ አደረጋት፡፡ ከዚህ በኋላ ፍርሃቱ ለቀቃትና ‹‹ልጄ ሆይ! ከዛሬ ጀምሮ መምህሬ፣ አባቴ፣ መካሪዬ እልሃለሁ እንጂ ልጄ አልልህም›› ብላ በጭካኔ ከልጅዋ ጋር ወደ ፈላው የብረት ጋን ገባችበት፡፡

በዚህ ጊዜ ሕፃኑ ቂርቆስ አናንያን፣ አዛርያንና ሚሳኤልን ያዳነ አምላክ ያድነናል ያለውን ቃል ለመፈጻም እግዚአብሔር አምላክ መልአኩ
ቅዱስ ገብርኤልን ላከላቸው፡፡ መልአኩም በትእምርተ መስቀል እሳቱን ቢባርከው እንደ በረዶ ቀዝቅዞላቸዋል፡፡ በመልካቸውም እንደ ፀሐይ አበራ፡፡ ከእግር ጥፍራቸው እስከ ራስ ጠሩራቸው አንድም ሳይጎዳቸው በደህና ወጡ፡፡

በመጨረሻም ሕፃኑ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ እንዲህ አለ፡፡ ይህን ያህል ገድል ተጋድዬ ምን ዋጋ ትሰጠኛለህ ቢለው፣ ጌታ በልብህ ያለውን ሁሉ እሰጥሃለሁ አለው፡፡ ዳግመኛም ሥጋህ በምድር ላይ እንዳይፈርስ እንዳይበሰብስ በኤልያስ ሠረገላ ላይ አኖርሃለሁ አለው፡፡

ስለሆነም በዚህ ዕለት ቤተክርስቲያናችን መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ለእናታችን ለቅድስት ኢየሉጣ እና ለሕፃኑ ለቅዱስ ቂርቆስ ያደረገውን ይህን ታላቅ ተአምር ድንቅ ሥራ በማሰብ ከዋዜማው ጀምራ እግዚአብሔርን ስታመሰግን ትውላለች ታድራለች፡፡

የመልአኩ የቅዱስ ገብርኤል በረከት ተራዳኢነት ከሁላችን ጋር ይኑር አሜን።

@mesenqo_le_ethiopia
277 viewsmesii, 19:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-25 22:36:48 ​​#ቅዱስ_ገብርኤል

እንኳን ለታላቁ መልአክ ለቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ አደረሰን!!!

በቤተ ክርስቲያን ሥርዓት መሠረት ሐምሌ 19 የቅዱስ ገብርኤል አመታዊ በዓል ነው፡፡ ይህ ቀን ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ቅድስት እየሉጣንና ልጇን ቅዱስ ቂርቆስን ከሞት አደጋ እንደታደገበት የሚታሰብበት ዕለት ነው። የሐምሌ 19 ስንክሳርና የሐምሌ ወር ድርሳነ ገብርኤል እንዲህ ተርከውታል፡፡

በዘመነ ሰማእታት ከሐድያን ነገሥታትና መኳንንት በክርስቲያኖች ላይ መከራ አጽንተውባቸው ነበር፡፡ በዚህም ምክንያት ብዙዎች ሰማእትነትን ሲቀበሉ የተቀሩት አገር ጥለው ተሰደዱ። እየሉጣም የሦስት ዓመት ህፃን የነበረውን ቅዱስ ቂርቆስን ይዛ ሸሸች በዚያም የሸሸችውን መኮንን አገኘችው ሰዎችም ነገር አሰሩባት ወደእርሱ አስቀረባት እና ስለ አምልኮ ጠየቃት እርሷም መኮንን ሆይ ዕድሜው ሦስት አመት የሆነው ህፃን አለ አማልክቶችህን ማምለክ መልካም እንደሆነ ወይም እንዳልሆነ ያስረዳን ዘንድ እሱን ጠይቅ አለችው፡፡

ህፃኑም ወዳለበት ጭፍራውን ልኮ ወደእርሱ አስመጣው ህፃኑም ፊቱ ብሩህና ደስተኛ እንደሆነ አየውና አንተ ደስተኛ ህፃን ሆይ እንዴት ነህ አለው፡፡ ህፃኑም መልሶ አዎ ለኔ ተጠብቆልኛል ላንተ ግን ሐዘንና ለቅሶ ጥርስ ማፋጨትም ነው፡፡ መጻሐፍ ለዝንጉዎች ተድላ ደስታ የላቸውም ብሏል እና አለው፡፡ እግዚአብሔር ኃይልና ንግግርን ሰጥቶታልና ብዙ ተናገረ በዚያም ያሉትን እስካስደነገጣቸው ድረስ ንጉሱን መኳንንቱንና ጣኦታቱን ረገማቸው፡፡ከብርታቱም የተነሳ አደነቁ፡፡

መኮንኑም በአፈረ ጊዜ በያይነቱ በሆነ ስቃይ ታላላቆች የማይችሉትን ታላቅና አስጨናቂ የሆነ ስቃይን አሰቃየው እናቱንም ከእርሱ ጋር አሰቃያት፡፡ እግዚአብሔርም ያለ ምንም ጉዳት ያነሳቸው ነበር፡፡ ብዙዎች አህዛብም ይኸንን አይተው አደነቁ ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስም አምነው በሰማእትነት አረፉ፡፡ የሰማእትነትንም አክሊል ተቀበሉ፡፡ በህፃኑም ላይ የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ አደረበት፡፡ ታላላቅ ድንቆችና ተአምራቶችንም አደረገ ብዙዎች በሽተኞችንም አዳናቸው፡፡

መስፍኑም በውስጡ ሰም፣ ጨው፣ ባሩድ፣ ሙጫ የዶሮ ማር፣ እርሳስ፣ ብረት፣ ቅንጭብ፣ ቁልቋል ጨምራችሁ ታላቅ የብረት ጋን አንጡልኝ ብሎ ጭፍሮቹን አዘዛቸው፡፡ ጭፍሮቹም እንዳዘዛቸው ካአደረጉ በኋላ ያዘዝከንን ሁሉ ፈጽመን እሳቱ ነዶ ፈልቷል፡፡ ድምፁ እንደነጐድጓድ ይጮኸል ወላፈኑም እንደጸሐይ ነጸብራቅ በሩቁ ይጋረፋል፡፡ የፍላቱም ኃይል በ14 ክንድ ያኽል ከፍታ ወደ ላይ ይዘላል፡፡ እንግዲህ በውስጡ የሚጣሉትን እዘዝ አሉት በዚህ ጊዜ ህፃን ቂርቆስና እናቱ እየሉጣ በክርስቶስ ስም ስለሚያምኑ አስረዋቸው ነበርና ከፍላቱ ሊጨምሯቸው ከእስር ቤት አወጧቸው፡፡

በዚያም ፍላቱ ወደላይ በሚዘል ብረት ጋን ውስጥ ለመጨመር ሲወስዷቸው የነዚህን ቅዱሳን አሟሟት ያዩ ዘንድ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች እንዲሰበሰቡ አዘዛቸው፡፡ በዚህን ጊዜ ቅድስት እየሉጣ የፍላቱን ጩኸት በሰማችና ባየች ጊዜ ተሸበረች፡፡ ተዘጋጅቶላት ከነበረው ክብር ልታፈገፍግ ሞከረች፡፡ ልጇ ቅዱስ ቂርቆስ ግን እናት ሆይ ከዚህ የብረት ጋን ግርማ የተነሳ አትፍሪ ድንጋጼም አይደርብሽ አናንያንና አዛርያን ሚሳኤልንም እግዚአብሔር ከእቶነ እሳት እንዳወጣቸው ሁሉ እኛንም ከዚህ ከብረት ጋን ሊያወጣን ችሎታ ያለው መሆኑን አትጠራጠሪ፡፡

እናት ሆ ከዚህ ከሚያልፈው ዓለም ጭንቅና መከራ ለመዳን ስትይ በማያልፈው ዘላለማዊ እሳት ለመቀጣት ትመርጫለሽን ይኽስ አይሆንም ይቅርብሽ፡፡ በአሁኑ ጊዜ እግዚአብሔር በመካከላችን አለና ይረዳናል፡፡ እናት ሆይ ሶስናን ከእደ ረበናት /መምህራነ አይሁድ/ ዳንኤልን ከአፈ አናብስት ያዳነ እርሱ እኛንም ከጋን ፍላት ያወጣናል፡፡ ይልቁንም እግዚአብሔር በዚህ የብረት ጋን ውስጥ ግዳጃችንን ልንፈጽም ፈቅዶ ከሆነ ኢዮብ ንብረቱንና ገንዘቡን ልጆቹንና ሚስቱን በመጨረሻም የተፈጥሮ አካሉን ባሳጣው ጊዜ እግዚአብሔርን አመሰግነዋለሁ እግዚአብሐር ሰጠ እግዚአብሔር ነሳ እግዚአብሔርም እንደወደደ አደረገ ከማለት በስተቀር ምንም የተናገረው ነገር እንደሌለ ሁሉ እኛም የሱን ዓላማ በመከተል ይኽንን መከራ ልንታገስ ይገባናል፡፡

ነገር ግን እናቱ በዚህ ምክር ልትጽናና ባለመቻሏ ቅዱስ ቂርቆስ ዐይኑን ወደ ሰማይ አቅንቶ አቤቱ አምላክ ሆይ ይችን ባሪያህን ከርስትህ የምትለያት ከሆነ ከባለሟልነትህ መጽሐፍ ፋቀኝ፤ አቤቱ አዝመራውን አቃጥለ ፍሬውን ልትባርክ ትወዳለህን ይኽን እንዳታደር ግን ቸርነትህ ትከለክልኸለች አቤቱ እንጨቱን ቆርጣችሁ አንድዱት ቅጠሉን ግን ጠብቁት ብለኽ ልታዝ መለኮታዊ ባሕሪህ አይደለም፡፡ ነገር ግን እንጨቱንም ቅጠሉንም በአንድ ጠብቁት ብለኽ ታዝዛለኽ እንጂ፡፡ እንግዲህ በዚህ ምክንያት ይኽንን ያየ ሁሉ ማዳን የሚችል አምላክ ቢኖራቸውስ ኖሮ ከእሳት ባልሸሹም ነበር ብሎ አይጠራጠር፡፡

አቤቱ ዲያብሎስም ከባለስልጣኑ ይልቅ እኔ በረታሁ ቅዱሳኖቹንም ድል ነሳኋቸው ብሎ እንዳይመካ ከመንጋውም አንድ በግ ቀማው በማለት እንዳይደነፋ ለእናቴ ጽኑ የሆነ ኃይለ መንፈስ ቅዱስን ስጣት ብሎ በጸለየ ጊዜ ዲያብሎስ ከእየሉጣ አጠገብ ብን ብሎ ጠፋ፡፡ ከዚህ በኋላ ቅድስት እናቱ በሰማያዊ መንግሥት አባት የሆንከኝ ልጄ ሆይ ጌታኽ ኃይልን ሰጥቶኛልና የሚጠብቀንን ገድላችንን ፈጽመን ድል እናድርግ እነሆ በብረት ጋን ውስጥ የሚነደውን እሳት በማይበት ጊዜ በለምለም /በምንጭ/ ላይ እንደሚወርድ ጠል ሆኖ አይቸዋለሁና አለችው፡፡

#ይቀጥላል

@mesenqo_le_ethiopia
263 viewsmesii, 19:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-23 20:00:01 ​​#የመልካም_ወጣት_መገኛ

Share በማድረግ ለመጥፋት የተዘጋጁ በጎችን ከመንጋው እንዳይለዩ ታደጓቸው።
መልካም ወጣት ማለት ከኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሀይማኖት ወጥተህ መናፍቃን አዳራሽ መክተም አይደለም።

መልካም ወጣት ማለት ክርስቶስ የተሰቀለበትን መስቀል ከአንገትህ ላይ በጥሶ መጣል አይደለም።
መልካም ወጣት ማለት ቅድስት ድንግል ማርያምን መካድ ማለት አይደለም።
መልካም ወጣት ማለት ለሰዎች ይታዩ ዘንድ በምድር ላይ ባለጠግነትንና ዝነኝነትን ማካበት አይደለም፥ በምድር ላይ ሁሉ የከንቱ ከንቱ ነው።

#ይልቁንስ መልካም ወጣት ማለት ወንጌል ነው፦
ወዳጄ ወንጌል ማለት በሽንገላ ከንፈር ኢየሱስ ያድናል ማለት አይደለም። ወንጌል ማለት ክርስቶስን አምኛለውኝ ብሎ በግላዊ ግብር ለክርስቶስ ያለመታመንም ማለት አይደለም። ወንጌል ማለት መከራ መስቀልን መሸከም ነው። ወንጌል ማለት ክርስቶስ የተጓዘበትን የኩርንችት መንገድ በደስታ መራመድ ነው ። ወንጌል ማለት ለመሀተብህ ትሞታለህ ሲባል ከስጋው ይልቅ ነፍስን አስበልጦ ቀድሞ መሰለፍ ነው። ወንጌል ማለት ስለክርስቶስ ፍቅር ስጋህን እና ምኞትህን ገድለህ ለሞተልህ አምላክ መሰጠት ነው። ወንጌል ማለት ነፍስን መግደል በማይችሉት ፈርዖኖች ፊት በክብር ማሸብሸብ ነው ።

ወንጌል የምታወራው ልብ ወለድ ሳይሆን የምትላላክለት መወደድ ትዕዛዝ እንጅ። ወንጌል ማለት ክርስቶስ በደሙ የዋጃት ቤተክርስቲያን ክብር ላይ ዕጣ ሲጣጣሉባት እንደ 44 ታቦት ብላቴናዎች ቀድሞ የመገኘት ጥሪ ነው። ወንጌል የምትታዘበው እና ከአውደምህረት ላይ የምትወረውረው የማትኖርበት ቃል አይደለም። የምታልፍበት የመከራ ኮረብታ እንጅ ።

ከእዚህ አማናዊ ወንጌል ከሆነው ህዝብ ተማር። በጣም ተማር።
ልጆቻችሁን ወንድም እኅቶቻችሁን "መልካም ወጣት አዳራሽ" የምትልኩ ኦርቶዶክሳውያን ጊዜያዊ መላ ፍለጋ ልጆቻችሁን ለዘለዓለማዊ ሞት አሳልፋችሁ እየሰጣችሁ እንደሆነ ዕወቁ።
አዎ ልክ ነው ዘፋኙ ኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ ነው፥ አዎ ልክ ነው ሰካራሙ ኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ ነው፥ አዎ ልክ ነው ሱሰኛው ኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ ነው፥ አዎ ልክ ነው ተሳዳቢው፥ ተራጋሚው፥ ተደባዳቢው፥ አመጸኛው የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ ነው ነገር ግን ቤተ ክርስቲያኒቷ እና ሀይማኖቷ አጥብቀው ያወግዛሉ።

የአባ ዘጋስጫ ሀይማኖት ፥ የአባ ኤፍሬም ሀይማኖት ፥ የቅዱስ ያሬድ ሀይማኖት፥ የቅድስት አፎሚያ ሀይማኖት፥ የአቡነ ተክለ ሀይማኖት፥ ገብረ መንፈስ ቅዱስ፥ አቡነ አረጋዊ ሀይማኖት ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ነው፥ ትልቅ እምነት እና ከክርስቶስ ቀጥሎ በክርስቶስ መንገድ የሄዱ ቅዱሳን የተጠሩባት ሀይማኖት (1ቆሮ᎐11:1) እኔ ስጠራበት በመጥፎ ስራዬ ላፍር በሀይማኖቴ ግን ልኮራ ይገባል።

ይህ ሰበብ ሊሆነን አይገባም፥ እኔ መልካም ወጣት እንድሆን መናፍቅ መሆን በፍጹም አይጠበቅብኝም!!
ኦርቶዶክሳውያን ሰባክያነ ወንጌል፣ ማኅበረ ቅዱሳንና ሌሎች መንፈሳዊ ማኅበራት፣ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ኦርቶዶክሳዊውን ወጣት የመጠበቅ ኃላፊነትና አደራ ከጌታ የተሰጣችሁ ነውና ትውልዱን ከጥፋት ለመጠበቅ ምን መሥራት እንዳለባችሁ አስቡበት።

"ደግሞ ሁለተኛ፦ የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ ትወደኛለህን? አለው። አዎን ጌታ ሆይ፥ እንድወድህ አንተ ታውቃለህ አለው። ጠቦቶቼን ጠብቅ አለው።" (ዮሐ 21:16-17 )

@mesenqo_le_ethiopia
347 viewsmesii, 17:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-22 11:51:44 #ሁሉም_ነገር_ለበጎ_ነው



አንድ ንጉስ ከአሽከሩ ጋር ለአደን ወደ ጫካ ያመራል። ዙርያውን ወጥመድ በማጥመድ ላይ ሳሉ አንደኛው ወጥመድ የንጉሱን እጅ ላይ አርፎ እጁን ያሳጠዋል። ንጉሱም በመጮህ ላይ ሳለ አሽከሩ የደማውን እጁን በጨርቅ እየጠቀለለ "ንጉስ ሆይ አይዞህ ለበጎ ነው ይለዋል" ንጉሱም እጅግ ይበሳጭና የእኔ እጅ መቆረጥን ለበጎ ነው ትላለህ ብሎ ያሳስረዋል።

ከብዙ ቀን ቆይታ በኋላ ንጉሱ ለብቻው ወደ አደን ሲሄድ ሰው ገድለው ለአማልክቶቻቸው መስዋዕት የሚያቀርቡ ሽፍቶች ይይዙታል። ሊሰውትም ሲሉ ንጉሱ እጁ የተቆረጠ ነውና በባህላቸውም መሠረት አካለ ጎዶሎ ሰው ለመስዋዕት አይቀርብምና ይተውታል።

ንጉሱም ወዳሰረው አሽከር ሄዶ "ሁሉም ነገር ለበጎ ነው ያልከው እውነት ነበር ብሎ ታሪኩን ያጫውተዋል። ባደረገውም ተጸጽቶ "ይቅርታ አድርግልኝ አንተን ማሰሬ ልክ አደለም" ይለዋል

አሽከሩም "ንጉስ ሆይ አንተም እኔን ማሰርህ ለበጎ ነው ባታስረኝ ኖሮ ካንተ ጋር አብሬ እሄድ ነበር። አንተን ሲለቁህ እኔን ደግሞ ሙሉ አካል ነው ብለው ይሰዉኝ ነበር" አለው።


" እግዚአብሔርንም ለሚወዱት እንደ አሳቡም ለተጠሩት ነገር ሁሉ ለበጎ እንዲደረግ እናውቃለን።"
(ወደ ሮሜ ሰዎች 8:28)

ብናገኝ፣ ብናጣ ሁሉም ነገር ለበጎ ነው ከማማረራችን በፊት የእግዚአብሔርን በጎ ምላሽ እንጠብቅ። እግዚአብሔር ቢዘገይም የሚቀድመው የለም ከችግራችን በላይ እግዚአብሔር ይበልጣል።

@mesenqo_le_ethiopia
347 viewsmesii, 08:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ