Get Mystery Box with random crypto!

📚ሀዲሦችና አጫጭር የቁርአን አንቀፆች መልቀቂያ ቻነል 📚

የቴሌግራም ቻናል አርማ allah_is_the_great — 📚ሀዲሦችና አጫጭር የቁርአን አንቀፆች መልቀቂያ ቻነል 📚
የቴሌግራም ቻናል አርማ allah_is_the_great — 📚ሀዲሦችና አጫጭር የቁርአን አንቀፆች መልቀቂያ ቻነል 📚
የሰርጥ አድራሻ: @allah_is_the_great
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.23K
የሰርጥ መግለጫ

የአላህን እዝነት ማግኘት ለምንፈልግ ሁሉ፦
وإذا قرئ القرآن فاستمعوا له وأنصتوا لعلكم
تزكمون
ቁርኣንም በተነበበ ጊዜ እርሱን አዳምጡ ጸጥም በሉ ይታዘንላችኋልና።(ሡራ አል-አዕራፍ 204)
ቁርኣንን ልብ ሰጥተን በማድመጥ ብቻ የአላህንራሕመት እንላበሳለን አላህ ራሕመቱን ያጎናፅፈን።
🔽 ሀሳብ አስተያየት ለመስጠት 🔽
@Astaytmschaa_bot

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-10-10 00:03:00
"ወላሂ ነብዩ እራሳቸው የመውሊድን ቀን አታክብሩ ቢሉን እንኳ እናከብረዋለን!" እያለ ነው ይሄ ሱፊ።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
40 views21:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-08 20:24:11
የሙእሚኖች እናት ዓኢሻ ረዲዬሏሁ (ዐንሃ)
ከነቢዩ (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) ሞት በሗላ
ከአርባ አመት በላይ ኑራለች

እሄን ሁሉ አመት እንኳ ስትኖር አንድም ቀን መውሊድን አላከበረችም?

ከዚያች ረሱል (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) ከሰዎች (ሁሉ) አንተ ዘንድ ተወዳጁ ማነው? በተባሉ ጊዜ «ዓኢሻ» ካሉላት የበለጠ እውን ረሱልን (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) ትዎዷቸዋላችሁ እና ነው መውሊድን የምታከብሩትን?!

​•┈┈•┈┈•⊰✿◇✿⊱•┈┈•┈┈•
t.me/IbnuMuhammedzeyn
119 views17:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-08 15:55:14
የዛሬ ቀን ረቢአል አወል 12 ነብዩ ﷺ የሞቱበት ነው። ይህን ቀን አመታዊ የደስታ ቀን አድርጎ መያዝ ሰይጣናዊ መንገድ ነው። በኢስላም የሙት አመት የሚባልም ነገርም የለም። በኢስላም የታዘዝነውን ብቻ እንስራ። ከክስረት እንጠበቃለንና። ነብዩ ﷺ "ቢድአ ሁሉ ጥመት ነው" ብለዋል።
https://t.me/joinchat/TOuxbiRtRHaliXPK
104 viewsedited  12:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-08 15:24:45
እንኳን ሚሊኒየም አዳራሽ መውሊድ መካ ቢከበር ራሱ መረጃ ይሆናል ወይ?
--------------------

ተረጋግተህ ስሜትህን ያዝ አድርገህ ነገሮችን ከመረጃ አንፃር ገምግም!!!

ረሱልን መውደድ መመዘኛው መውሊድን ማክበር ያደረገው ማነው??

መውሊድ ቢድዓ ሀሰና ነው ብሎ ሲያበቃ አላከብርም ስላልክ ቃላት ሊሰነዝር ይቃጣዋል!!

ኢስላም በመረጃ የቆመ ነው!! ኢስላም በሰዎች ስራ አይመዘንም!!

ኡስታዝ ኢብራሂም ሙሳ!!

https://t.me/joinchat/TOuxbiRtRHaliXPK
104 viewsedited  12:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-08 12:09:29
መውሊድ ይቻላል ለሚልህ ይህንን አቅርብለት


ጥያቄ አንድ
መውሊድ ማክበር አላህን መታዘዝ ነው ወይስ አላህን ማመፅ በለው?

①) መውሊድ አላህን ማመፅ ነው ካለ አላህን ለማመፅ መውሊድ ማክበር አይቻልም በማለት ፋይሉ መዝጋት ይቻላል። ነገር ግን በፍፁም ይህንን አይሉም።

②) አላህን መታዘዝ ነው ካለ (የሚሉትም ይህ ነው) ወደ ሁለተኛው ጥያቄ ትሸጋገራለህ

ጥያቄ ሁለት
ይህንን አላህ መታዘዝ ነው ኢባዳ ነው የምትለው መውሊድ የአላህ መልእክተኛ ያውቁት ነበር ወይስ አያውቁትም ዘንግተውታል በለው።

①) መልእክተኛው አያውቁትም ዘንግተውታል ካለ ይህ ግልፅ የሆነ ኩፍር ነው። ነገር ግን ይህንን በፍፁም አይሉም።

②) የአላህ መልእክተኛ አውቀውታል ካለ (የሚሉትም ይህ ነው) ወደ ቀጣዩ ጥያቄ ትሻገራለህ።

ጥያቄ ሶስት
መውሊድ የአላህ መልእክተኛ አውቀውት ከሆነ ለህዝባቸው አድርሰውታል ወይስ አላደረሱትም በለው።

①) ለህዝባቸው አላደረሱትም ካለ አላህ ታማኝነታቸውን የገለፀውን ነብይ በመጥፎ መጠርጠር ስለሆነ ግልፅ የሆነ ኩፍር ነው። ነገር ግን ይህንን አይሉም።

②) ለህባቸው አድርሰውታል ካለ፦ በሙግትህ ላይ እውነተኛ ከሆንክ መረጃ አምጣ በለው? ነገሩ እዚህ ላይ ያበቃል። መረጃ ደሞ ከየትም ሊያመጣ አይችልም።

ምክንያቱም መውሊድን በተመለከተ አንድም የቁርአን ወይም የሀዲስ መረጃ የለምና። ይህም ማረጋገጫው እነሱ ራሳቸው መውሊድ ቢድአ ሀሰና ነው ማለታቸው ነው። መረጃ ያለው ነገር ደሞ ቢድአ ሀሰና ሊሆን አይችልምና።

ነገር ግን አላዋቂዎችን ለማታለል ከቁርአን ከሀዲስ መረጃ አለ ብለው ሊያጣቅሱ ይችላሉ። እውነታው ግን ለመውሊድ ብለው የሚያመጧቸው የቁርአንና የሀዲስ መረጃዎች በነሱ ላይ መረጃ የሚሆኑ እንጂ ለነሱ መረጃ የሚሆኑ አይደሉም።

http://t.me/Sadik_Ibnu_Heyru
110 views09:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-07 06:49:29 ሱረቱል ካህፍ

የአላህ መልዕክተኛﷺእንዲህ ብለዋል።

➯የጁምዓ ቀን ሱረቱል ከህፍን የቀራ ሰው አላህ በሁለቱ ጁምዓዎች መካከል ብርሃን ያበራለታል።
125 views03:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-05 17:49:22 (14) አላማ ይኑርህ። ለአላማህ ትጋ። ወደ አላማህ ተጓዝ። ወዴት ነው የምትሄደው? ታውቀዋለህ? ምንድነው የምትፈልገው? ይገባሃል? ምን ሰበብ እያደረስክ ነው? መቼስ ሰሜን ለመድረስ ወደ ደቡብ አይኬድም። ጤፍ ዘርቶ ባቄላ አይጠበቅም። ባጭሩ አላማህንም፣ አቅጣጫህንም፣ ሚናህንም እወቅ።
"የሚሄድበትን የማያውቅ የትኛውም መንገድ ይወስደዋል።"

(ኢብኑ ሙነወር፣ ጥር 21/2011)
የቴሌግራም ቻናል፦
@IbnuMunewor
155 views14:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-05 17:48:30 ጥቂት ምክሮች ለሙስሊም ተማሪዎች
~
① መምህርህን አክብር። አስተማሪህ ለደሞዝ ቢሰራም ላንተ ውለታ እየዋለ ነው። ኋላ ከሚፀፅትህ ዛሬ ለአስተማሪህ ትሁት ሁን። እድሜውንም አክብር። የሚያስተምርህን መናቅ የሚያጎርስህን መንከስ ነው። እንዲያዝንብህ፣ "ባጎረስኩ እጄን ተነከስኩ" እንዲል አታድርገው። ውለታ ይግባህ። የወጣትነት ስሜት ድፍን ቅል አያድርግህ።
"አስተማሪን መናቅ እውቀትን መናቅ ነው።"
"ለእውቀት ያለህ ክብር መጠኑ ለአስተማሪህ ባለህ ክብር ልክ ነው።"

② ተባባሪ ሁን። እንዳቅምህ የምታግዛቸው በርካታ ደካማ ተማሪዎች በዙሪያህ አሉ። የእለት ጉርስ የሚገድላቸው፤ የደንብ ልብስ አቀበት የሆነባቸው፤ የሳሙና፣ የሃንዳውት፣ የታክሲ፣ የቤት ኪራይ፣ የህክምና፣ የደብተር፣ … የሚቸግራቸው፤ ብዙ ናቸው። ቢቻል አስተባብራችሁ የተቀናጀ ስራ ስሩ። ካልሆነ የራስህን ሐላፊነት ተወጣ። ደካማ ተማሪዎችን አስጠና፣ አግዝ። በዱንያ እርካታን ታገኝበታለህ። ልምድን ትቀስምበታለህ። ህይወትን ትማርበታለህ። በኣኺራ እጥፍ ድርብ ትሸለምበታለህ።

③ ከመንደሬነት ራቅ። የሰፈር፣ የቀበሌ፣ የወረዳ፣ የአካባቢ ብሽሽቅ ውስጥ አትግባ። ዘረኝነትን በየትኛውም መልኩ ተፀየፍ። ዘረኞችንም ከቻልክ ምከር። ካልሆነ አፍንጫህን ይዘህ ሽሻቸው። በዘርህ ከማንም በላይም፣ ከማንም በታችም አይደለህም። ሌሎችን በዘር አትውጋ። በዘር ለሚተነኩስህም ንቀህ እለፍ እንጂ እሳት ጎርሰህ አትነሳ። የማንም ሙገሳ ከፍ እንደማያደርግህ ሁሉ የማንም ትችትም ዝቅ አያደግህም። ትእግስት ፍርሃት እንዳልሆነ ለራስህ ሹክ በለው።
"ዘረኝነት ጥንብ ሲሆን ዘረኛ ደግሞ ጥንብ አንሳ ነው።"

④ ለዲንህ ጊዜ ስጥ። አንተ ያለ ዲንህ ባዶ ነህ። ያለ ዲን ስኬትም ስኬት፣ ህይወትም ህይወት አይደለም። ስለ ዲንህ ስትማር ክፍል ውስጥ ዲንህን አታስነካም። የተሳሳተ ቲዎሪ አያነቃንቅህም። ውሎህ በፕሮግራም ይሆናል። ሕይወትህ ጣእም ይኖረዋል። ስለዚህ ቁርኣን ቅራ። አስቀራ። ኪታብ ተማር። አስተምር። ደዕዋ ሞክር። ሶላት ስገድ። ስታልፍ ስታገድም ዚክርህን አድርግ። ዲንህን በራስህ ላይ አንፀባርቅ። ዲንህ የሚወራ ሳይሆን የሚንኖር ነው።
"ዲንህ ህይወትህ ነው። ዲንህ ከሌለ አንተ እራስህ የለህም።"

⑤ በትምህርትህ ላይ ሃላፊነት ይሰማህ። ቤተሰብ የላከህ ለዋዛ አይደለም። ገንዘቡም፣ ጊዜውም፣ ድካሙም ዋጋ አይጣ። ስለዚህ በወጉ ተማር። ክፍል ውስጥ በሚገባ ተከታተል። ንቁ ተሳትፎ ይኑርህ። በሚገባ አጥና ። ስንፍናን አትቀበል። "አልችልምን" አርቅ ። ኩረጃን፣ ጥገኝነትን ተፀየፍ። በጥረትህ የተሻለ ደረጃ ላይ ለመድረስ ወኔ ይኑርህ። አትጠራጠር! ስትጥር ዛሬ ካለህበት የተሻለ ትሆናለህ። ባለ መጣሩ እንደ ሰነፍ የሚታይ፣ እራሱን የማያውቅ ስንት ባለ ብሩህ አእምሮ አለ?! መማርህ ካንተ አልፎ ለወገን የሚተርፍ ዋጋ እንዳለው ተረዳ።
"Education is a better safeguard of liberty than a standing army."

⑥ እራስህን ሁን። የመጣውን ፋሺን ሁሉ ካልሞከርኩ አትበል። ለራስህ ክብር ስጥ እንጂ። አንተ'ኮ የማስታወቂያ አሻንጉሊት አይደለህም። አርአያህን ለይ። መልካም ስብእና ያላቸውን እንጂ፣ ያለ ቁም ነገር ስማቸው የገነነ ሰዎችን ለመምሰል አትፍሰስ። አንተ ህሊና የተሰጠህ ክቡር ፍጡር እንጂ በቀደዱለት የሚፈስ የቦይ ውሃ አይደለህም።
"እራሱን ያላገኘ ሌሎችን ሲከተል ይኖራል።"

⑦ ጊዜህን በአግባቡ ተጠቀም ። አንተ ዘንድ አላህ ከሰጠህ ሐብት ሁሉ ርካሹ ጊዜህ የሆነ'ለት ያለ ጥርጥር ከስረሀል። ወደ ጨለማ ጥግ ከሚያደርስ የድንግዝግዝ ባቡር ላይ ተሳፍረሀል።
እባክህን ሕይወትህ ላይ አንዳች እሴት በማይጨምሩ ነገሮች ዳግም የማታገኘው ውድ ጊዜህን አታባክን። የምልህ እየገባህ ከሆነ በሙዚቃ ከመመሰጥ፣ ፊልም ጋር ከመርመጥመጥ፣ የፈረንጅ እርግጫ ከማሳደድና መሰል አልባሌ ነገሮች ራቅ እያልኩህ ነው። እነዚህ ነገሮች ከእለት መዝናኛነት ባለፈ ተሻጋሪ ሱስ የሚሆኑ ወጥመዶች ናቸው።
"ጊዜ ሰይፍ ነው። ካልቆረጥከው ይቆርጥሀል።"
"አንተ የጊዜያት ድምር እንጂ ሌላ አይደለህም። እያንዳንዷ የጊዜ ክፍልፋይ ስታልፍ አንተ እራስህ እያለፍክ ነው።"

⑧ ጓደኞችህን ለይ። ጓደኛህ ወይ የምትጠቅመው ወይ የሚጠቅምህ መሆን አለበት። ከዚህ ውጭ የሆነ ጓደኛ የፋንዲያ ያክል ዋጋ የለውም። እንዲያውም ያጠፋሀል። በዱንያ ቁም ነገር ላይ ከመድረስ ያሰናክልሀል። አልፎም ኣኺራህን ያጨልመዋል። ኧረ ለመሆኑ አንተ እራስህ ምን አይነት ጓደኛ ነህ? አልሚ ወይስ አጥፍቶ ጠፊ? በል ከዛሬ ጀምሮ ከጓደኛህ ጋር ቁጭ ብላችሁ የአብሮነታችሁን ሂሳብ አወራርዱ። ጓደኝነታችሁ የምትጠቀሙበት እንጂ የምትጎዱበት እንዳይሆን በስርኣት ተመካከሩ።
"ሰው በወዳጁ እምነት ላይ ነው። ስለሆነም አንዳችሁ ማንን እንደሚወዳጅ ይመልከት።"

⑨ መልካም ስነ ምግባርን ተላበስ። አትሸማቀቅ፤ ግን አትኮፈስ። ትሁት ሁን፤ ግን አትልፈስፈስ። ሰከን በል፤ ግን አትፍዘዝ። ረጋ በል፤ አትንጣጣ። ከአንደበትህ ክፉ አይውጣ።
ፊትህ ሁሌ በፈገግታ ይታጀብ። ተግባቢና ለሰዎች ቀላል ሁን። የደረስክበትን ሁሉ በሰላምታ አውደው። በትህትና አጊጥ። በቅንነት አሸብርቅ። "መጣብን" ሳይሆን "መጣልን" የምትባል ሁን። አታጣላ። አታባላ። ሃሜትና ውሸትን ክላ።
"ህዝብ ማለት ስነ ምግባር ነው። ስነ ምግባር የሌለው ህዝብ ካለ አይቆጠርም።"

(10) በትምህርት ሕይወትህ ላይ ሳለህ መዝናኛህን ቁም ነገር መጨበጫ አድርገው። ቁም ነገር አዘል መፃህፍትን አንብብ። ከቻልክ እንደ የመጀመሪያ እርዳታ /first aid/ አሰጣጥ፣ እንደ ቴኳንዶ ያሉ ራስን መከላከያ ሥልጠና፣ የችግኝ ወይም የጓሮ አትክልት አተካከል፣ እና መሰል ጠቃሚ ስልጠናዎችን ሰልጥን፣ አሰልጥን። አካባቢህን አስተባብረህ አፅዳ።
"ራስን ብቁ ዜጋ ማድረግ ለሀገርም ለወገንም እሴት መጨመር ነው።"

(11) ከህገ ወጥ ፆታዊ ግንኙነት አጥብቀህ ራቅ። ህጋዊ በሆነ መልኩ ተረጋግተህ ለምትደርስበት ነገር በህገ ወጥ መልኩ ለማግኘት እየቸኮልክ ስብእናህን አታቆሽሽ። የሌላን ህይወትም አታበላሽ። ከአላማህም አትሰናከል። ክፉ ምሳሌም አትሁን።
"ስድ ግንኙነት ለህሊና ጠባሳ፣ ለቤተሰብ ጦስ፣ ለህዝብ መቅሰፍት ያስከትላል።"
"ከጓደኞቿ የወጣች ማሽላ አንድም ለወፍ አንድም ለወንጭፍ ትሆናለች።"

(12) ከደባል ሱሶች ራቅ። አላማ ያለው ሰው ከሱስ ጋር አይነካካም። ለነፃነቱ ዋጋ የሚሰጥ ሰው በተልካሻ ቆሻሻ ነገሮች አይታሰርም። ደግሞም ውለታ ቢስ አትሁን። አንተ አክብረህ ያማረ ቪላ፣ ወይም ቆንጆ መኪና፣ ወይም ሚሊየን ገንዘብ ቆጥረህ የሰጠኸው ሰው አይንህ እያየ ከፊትህ በእሳት ቢያጋየው ምን ይሰማሀል? ኣ? ሰውስ ምን ይላል? አላህ በክብር የሰጠህን ህይወት በጫትና በሲጋራ መግደል ማለት ከዚህ የከፋ ውለታቢስነት ነው። እራስህን በሱስ የምትገድለው ከቤተሰብ በተቆነጠረ ሳንቲም ከሆነ ግን አንተ ዘመን ተሻጋሪ ገልቱ ነህ። እንስሳ ነህ ብየ የእንስሳን ክብር ዝቅ ማድረግ አልፈልግም።
"እራስን በሱስ በመጉዳትና እራስን በማጥፋት መካከል ያለው ልዩነት የጊዜ ርዝማኔ ነው።"

(13) ለወላጆችህ በጎ ሁን። አቅምህ የሚችለውን ሁሉ ሁንላቸው። የሚረኩብህ እንጂ የሚሸማቀቁብህ፤ የሚዘኑብህ እንጂ የሚሳቀቁብህ፤ የምታሳርፋቸው እንጂ የምታሳፍራቸው አትሁን። ቤተሰብህ ላይ ጥገኛ ሆነህ ሳለ አልፈህ የምትፏልልባቸው ከሆነ ግን በርግጠኝነት መጥፊያህን ይዘሀል። "የማያድግ ልጅ ታዝሎ ያፏጫል" ይባላል።
"የቤት ቀጋ፣ የውጭ አልጋ አትሁን።"
155 views14:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-05 17:45:54
ውድ የነሲሓ ቲቪ ቤተሰቦች ፕሮግራሞቻችንን በ Nilesat ሙሉ ለሙሉ ያዞርን ስለሆነ ከታች በተጠቀሰው አድራሻ መከታተል የምትችሉ መሆኑን እናሳዉቃለን:-

Nilesat
Frequency: 11555 or 11554
Polarization: Vertical
Symbol Rate: 27500
Fec. 5/6

ነሲሓ ቲቪ "ኢስላማዊ እውቀት ለሁሉም!
119 views14:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-04 17:13:32
ኢስላም የተሟላው ሃይማኖት 01|| NesihaTv

https://t.me/joinchat/TOuxbiRtRHaliXPK
150 viewsedited  14:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ