Get Mystery Box with random crypto!

ንቁ'የመዳን ቀን ዛሬ ነዉ!

የቴሌግራም ቻናል አርማ nkuyemedankenzare — ንቁ'የመዳን ቀን ዛሬ ነዉ!
የቴሌግራም ቻናል አርማ nkuyemedankenzare — ንቁ'የመዳን ቀን ዛሬ ነዉ!
የሰርጥ አድራሻ: @nkuyemedankenzare
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.17K
የሰርጥ መግለጫ

ነገ እግዚአብሔር በመካከላችሁ ድንቅ ነገር ያደርጋልና ተቀደሱ"""ኢያሱ፤3፤5
////////////////////////////
@bemaleda_neku የሚለዉን ቻናላችንንም ይቀላቀሉ ////////

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-03-11 13:51:05 ያለ እርሱ"……!

አንዳንድ በሽታ በባሕሪዉ ሰዉን የማታለል ልምድ አለዉ በዚህ ባሕሪዉ ገሚሱን በዝምታ እንደ ምስጥ ዉስጥ ዉስጣቸዉን ቦርቡሮ ከጨረሳቸዉ በኋላ እስከወዲያኛዉ ከዚህ ዓለም እንዲሰናበቱ ያደገርጋቸዋል ገሚሱን ደግሞ ቀለል ያለ ሕመም በማስከተል በማደንዘዣ ኪኒን ሰዉነት ዉስጥ ይደበቅና በዝምታ አስከፊ ደረጃ ላይ አድርሶ ሰዉነትን ካዳከመ በኋላ የሕመም ምልክት ማሳየት ይጀምራል በዚህ ጊዜ ወደ ሕክምና ሲኬድ ይሄ በሽታ መጥፎ ደረጃ ከመድረሱ የተነሳ ዋጋ የሚያስከፍል ሆኖ ይገኛል ታዲያ በእንዲህ ዓይነት በሽታ የተጠቁ ሰዎች የበሽታዉን አስከፊነትና ከምን ዓይነት አደጋ እንደተረፉ የሚረዱት የተሰጣቸዉን መድሃኒት በአግባቡ ወስደዉ ፈዉስ ካገኙ በኋላ ነዉ። አስተዉል ወዳጄ፥ ብዙሃኖቹ ኀጢአቶች እንደዚሁ በሽታ ፍጹም መንፈሳዊ አስመስለዉ በዝምታ ሰዉነትን ዉስጥ ዉስጡን በክፋት ጠርቀዉ በማሰር ዘለዓለማዊነትን የሚያሳጡ ናቸዉ፤ እንዲህ ዓይነቱ ኀጢአቶች ከሰዉነት ጋር ተዋህደዉ ጠባይ መስለዉ የሚደበቁ ስለሆኑ ያለ ቅዱስ ቁርባን በጾም ጸሎት ብቻ ድምጻቸዉን አያሰሙም የእነዚህ ኀጢአቶች አስከፊነት እግዚአብሔር የልብና የኩላሊትን አሳብ የማያዉቅ አስመስለዉ በማደንዘዝ ለእግዚአብሔር ታማኝ አገልጋይ እንዳንሆን ክርስትናን ለታይታና የይስሙላ እንድንኖረዉ የሚያደርጉ የክፋት ዓይነቶች ናቸዉ።



መድሃኒቱ! ፦ እናንተ ጻፎችና ፈሪሳዉያን በዉስጡ ቅሚያንና ስስትን ተሞልቶ ሳለ የጽዋዉንና የወጭቱን ዉጭ ስለምታጥቡ ወዮላችሁ! እንዳለ
ማቴ፤23፤25



እንደዚህ ዓይነቱ ኀጢአቶች ዉስጥን አጥቁረዉ ከላይ አሳምረዉ በሰዉ ዘንድ ጻድቅ በማስመሰል ከንቱ የሆነ ምስጋናን የሚያስጎናጽፉ የኀጢአት ዓይነቶች ናቸዉ። እነዚህ ኀጢአቶች በቅዱስ ቁርባን ኀይል እንጂ በትሩፋት ብቻ የሚላቀቁን አይደሉም ምክንያቱም ጠባይን መስለዉ ትኩረት የማይስቡ የኀጢአት ዓይነቶች ስለሆኑ ያለ ቅዱስ ቁርባን ክፋት መሆናቸዉን እንኳን ለይተን ልናዉቃቸዉ አይቻለንም እንደሚታወቀዉ መድሃኒታችን ዘንድ ደግሞ ሰዋራዉ ሁሉ ግልጥ ስለሆነና ከእርሱ የሚሸሸግ ልሸሸግ ቢልም የሚቻለዉ አንድም ነገር ስለሌለ ከእርሱ ጋር ሕብረት ፈጥረን ስንኖር ብቻ ነዉ ከተሸሸጉበት መንቀሳቀስ የሚጀምሩት እንጂ ጠባይ መስለዉ ከሰዉነት ጋር የሚኖሩ የክፋት ዓይነቶች ናቸዉ ታዲያ የእነዚህን ኀጢአቶች አስከፊነት ተረድታችሁ ከምን ዓይነት መከራ እንዳመለጣችሁና ክፋት መሆናቸዉን የምትረዱት ቅዱስ ቁርባን ደግማችሁ ደጋግማችሁ ስትቀበሉ ብቻ ነዉ። አስተዉሉ! ለእንዲህ ዓይነቱ ኀጢአቶች ጾምና ጸሎቱ ልክ እንደ ማደንዘዣ ኪኒን ይሆናቸዋል እንጂ ፍቱን መድሃኒት ሆነዉ ከዉስጣችን ሊያራግፉልን አይቻላቸዉም ቅዱስ ቁርባን ዘለዓለማዊነትን ከማቀዳጀት አልፎ ዉስጣችን ተሰዉሮ የተሰገሰገዉን እያንዳንዱን ክፋት እያራገፈ ክርስትናን ወደ ምድር እንድናወርድ የሚያደርግ ነዉ፡፡ ወዳጄ፥ ያለ ቅዱስ ቁርባን ክርስትናን ወደ ምድር አወርዳለዉ ብለህ አታስብ የማይቻል ነገር ነዉና ከመንፈስ ፍሬዎች ለመመደብ የግድ ቅዱስ ቁርባን ያስፈልጋል፡፡ ገላ፤5፤22 በእርሱና ስለእርሱ የምንኖረዉ ከመድሃኒቱ ጋር ሕብረት ስንፈጥር ብቻ ነዉ። ዮሐ፤6፤56 የሰዉ ልጅ በማስተዋልና ጥበብ ተደግፎ ከክፋት እየተጠበቀ መኖር የሚቻለዉም ወደ ቅዱስ ቁርባን ቀርቦ አስመሳይ ከሆነ የጠላት ሴራ ሲያመልጥ ብቻ ነዉ መፅሐፈ ጥበብ፤10፤10-14 ሙሉን ምዕራፍ ብታነቡት……! ያለ እርሱ በድንግዝግዙ ሕይወትን ለመምራት መገደድ ይመጣልና ዉስጥ ዉስጡን እረፍት ከሚነሳችሁ አሰልቺ ክፋቶች ታርፉ ዘንድ በክፍያ ሳይሆን በነፃ ወደ ተሰጣችሁ ቅዱስ ቁርባን መቅረብ አስፈላጊ ነዉ። መድሃኒታችን እግዚአብሔር ከሕመምና ስቃይ አሳርፎ ዘለዓለማዊነትን ለማቀዳጀት እንደ ዓለም ሕክምና ረብጣ ብር አልጠየቀም እርሱ የጠየቀዉ አንድ ነገር ብቻ እርሱም እናንተ ደካሞች ወደ እኔ ኑ የሚል መስፈርት ነዉ ማቴ፤11፤28 መልካም የሆነ ሕክምናን ለማግኘት የሚፈልግ ወደ ሐኪሙ ቀርቦ መታከም ብቻ ነዉ የሚጠበቅበት ምናልባት በስግደት በጸሎት የሥጋ ፈዉስ ሆነ ሌሎች መልካም ነገሮች ሊገኝ ይችላል እርሱ ግን በቂ አይደለም፥ ወሳኙ ነገር ለምድራዊ ነገር መጨነቅ ሳይሆን ሰማያዊ ሕይወትን መላበስ ነዉ። ሌላዉ አንድ ክርስቲያን የሚያደርገዉን ነገር ለምንና ለማን እንደሚያደርግ በሥጋ ዕዉቀት ሳይሆን በነፍስ ዕዉቀት አዉቆ የሚያደርግ መሆን አለበት እንጂ አድርግ ስለተባለ የሚያደርግ ሂድ ስለተባለ የሚሄድ ና ስለተባለ የሚመጣ ወደ ነፈሰበት የሚነፍስ መሆን የለበትምና የነፍስ ዕዉቀት ይገኝ ዘንድ በቅዱስ ቁርባን መታተም አስፈላጊ ነዉ። በተጨማሪም፤ ክርስቲያን የመድሃኒታችን እግዚአብሔርን ፍቅር ምን ያህል እንደሆነ በታሪክ አዋቂ ሆኖ ሊቀመጥ የሚገባዉ ሳይሆን በሕይወት ኑሮዉ ፍቅሩን እያጣጣመ ሊኖር ይገባዋልና ቅዱስ ቁርባን እጅጉኑ አስፈላጊያችን ነዉ።
አዎ፦ያለ እርሱ ክፋት እንደሆኑ የማይታወቁ ነገር ግን ክፋት የሆኑ እንደ ጠባይ የሚታዩ ቁጥር የማይገድባቸዉ ሰዋራ ክፋቶች አሉና ወደ እርሱ ቀርቦ መታከሙ እጽብ ነዉ!'። በነገሬ፥ በተደጋጋሚ እንደሚወሳዉ ቅዱስ ቁርባን ጾም ጸሎትና ስግደት የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች ናቸዉ ለዚህም ምስክሬ የታመነዉ ቃል ነዉ። ማቴ፤8፤1-13 ቁጥ፤ 28-34 ማቴ፤9፤18-34 ማቴ፤12፤9-37 ማቴ፤15፤21-28 ማቴ፤17፤14-23 በዚህም ስለዚህም ያለ መለያየት በአንድነት እንጠቀምባቸዉ ዘንድ ይገባናል!
ያለ እርሱ በእርሱና ስለእርሱ መኖር አይቻለንምና ወደ እርሱ እንቅረብ!።

@Nkuyemedankenzare
159 viewsedited  10:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-08 21:55:10 ዕዉቀትን ተግባራዊ ማድረግ!


እያንዳንዱ ቀን የየራሱ የሆነ አስተምህሮ አለዉ መምህሩም መድሃኒታችን ነዉ አዳዲስ ቀኖች የሚሰጠንም ዉስጣችን የተሰገሰገዉን ክፋቶች ወደ እግዚአብሔር ቀርበን እያራገፍን የቅድስና ሕይወትን እየተላበስንና አዲስ ማንነትን እየተቀዳጀን እንድንሄ የሚሰጠን ዉድና ዳግም የማይገኝ ዕድል ነዉ። የሰዉ ልጅ ቁስ ነገር ቢጠፋበት በተመሳሳይ ቁስ ነገር ሊተካዉ ይችላል ነገር ግን ከዕድሜዉ ላይ አንዲት ቀን በከንቱ ብትቀነስበት ይህችን ቀን ዳግም ተመልሶ ሊያገኛት አይችልም ጊዜ ወደፊት የሚገሰግስ እንጂ ወደኋላ የሚሄድ አይደለምና ዉድና ተመልሶ ማግኘት የማይቻል ነገር ቢኖር እግዚአብሔር እንለዉጥበት ዘንድ የሰጠን ጊዜ ነዉ። አብዛኛዉ ጊዜ ያኔ እንዲህ አድርጌ በነበረ እየተባለ በቁጭት የሚወራዉ ያለፈ ጊዜን ዳግም ማግኘት ስለማይቻለን ነዉ። እግዚአብሔር አዲስ አዲስ ቀን የሚሰጠን ከክፋታችን ተመልሰን ከዛሬ ነገ የተሻለ ስብዕናን ተላብሰን ወደ እርሱ እንመለስ ዘንድ ነዉ እንጂ ዕድሜአችንን በከንቱ ለከንቱ ነገር እንድናባክነዉ አይደለም። መምህራችን እግዚአብሔር አንድን ፅሑፍ እንድናነብ አልያ ስብከት እንድናዳምጥ የሚያደርገን ያለ አንዳች ምክንያት አይደለም። እዛ ፅሑፍና ስብከት ዉስጥ አንዳች ድክመታችን ላይ ነቅተን በዛ ድክመታችን የእርሱን እርዳታ ጠይቀን ነጻ እንድንወጣ እንጂ ምጽ የእኔ ችግር እያልን መልዕክቱን እንድንዘለዉ አልያ የፀሐፊዉንና የሰባኪዉን ጠንካራ ጎንና ደካማ ጎን እያወጣን እያወረድን እንድንተችና እንድናሞካሽ አይደለም። ሊቁ ዮሐንስ አፈወርቅ አስተምሮዬ የእናንተን ሕይወት የማይለዉጥ ከሆነ የእናንተ ጭብጨባና እልልታ ምንም አያደርግልኝም እንዳለዉ። ጊዜ ወስዳችሁ የምታነቡትን ፅሑፍና የምትሰሙት ስብከት በሕይወታችሁ ለዉጥ ሳያመጣ እንዲሁ ዕዉቀት ብቻ ሆኖ በአእምሮአችሁ ብትይዙት ምንም ሊጠቅማችሁ አይችል። እግዚአብሔር ይሄንን ፅሑፍ እንዳነበና ይሄንን ስብከት እንድሰማዉ የፈለገዉ ምን ሊያስተምረኝ ፈልጎ ነዉ ብላችሁ ሊያነቃችሁ በፈለገዉ ነገር ላይ ቶሎ ነቅታችሁ ለዛ ደካማ ጎናችሁ መፍትሔ ከእርሱ በመጠየቅ ሕይወታችሁ ዉስጥ ለዉጥ እንዲመጣ ማድረግ አለባችሁ እንጂ አዉቃችሁ የእኔ ችግር እያላችሁ አልያ አድናቆት ሰጥታችሁ እንድታልፉ አይደለምና ወደ ሕይወታችሁ በሚመጣዉ መልዕክት ዉስጣችሁን ፈትሹ መድሃኒታችንን እሩቅ ፈላጊ አትሁኑ ልክ ከቀደምቶቻችን ጋር ቅርብ ለቅርብ ሆኖ እያስተማረና እየገሰጸ ቀጥተኛዉን መንገድ እንዳሳየቸዉ ሁሉ የእኛ ሕይወት ዉስጥም ቅርባችን ሆኖ በየዕለቱ ወደ ተስፋይቱ ምድር የሚወስደንን መንገድ እያስተማረ ይመራናልና እሩቅ አትፈልጉት ደግሞ በገሃዱ ዓለም
የሚል…አልወጣኝም በመንፈስ ማለቴ እንጂ



ልብ በሉ፥ እየተቸገርን ያለነዉ አንዳች አንቂ መልዕክት ወደ ሕይወታችን ሲመጣ ተግባራዊ ማድረግ ሳይሆን ዕዉቀት ብቻ አድርገን ስለምናልፋቸዉ ነዉ። ዕዉቀት ተግባራዊ ካልሆነ ሕይወት ዉስጥ ለዉጥ አይመጣም እንደምናየዉ ወንጌልን አዉቀን በሕይወት ኑሮ ተግባራዊ ባለማድረጋችን ነዉ አንድ ሊሆን የሚገባዉ ምግባራችን ልዩ ልዩ ሆኖ የቀረዉ። ዕዉቀት ብቻዉን ቆንጆ ተናጋሪ አድርጎ ሕይወትን መንፈሰ ቢስ ሲያደርግ ዕዉቀትን በሕይወት ኑሮ ተግባራዊ ማድረግ ደግሞ ሕይወትን አስዉቦ መንፈሰ ሙሉ ያደርጋል ከሁሉም በላይ በሰማይ ያለዉ አባታችሁን ያመሰግኑት ዘንድ እንዲሁ ብርሃናችሁ በሰዉ ፊት ይብራ። እንዳለ የመፅሐፍ ቃል እግዚአብሔር አምላካችን በእኛ እንዲመሰገን ያደርጋል። ማቴ፤5፤16 መተዉ ያለባችሁን ጉስቁልና እንድትተዉ የተሰጣችሁ ቀንና ጊዜ በከንቱ እንዲባክን አትፍቀዱለት ጊዜ አጥፍታችሁ ለማንበብ ሆነ ለመስማት ስትቀመጡ የሆነ ነገር ተምራችሁ ዕዉቀትን ተግባራዊ በማድረግ ራሳችሁን ለመወጥ መሆን አለበት እንጂ መረጃ ብቻ ለመሰብሰብ አይሁን። የሰዉ ልጅ ራሱን ማንበብና ዉስጡን ማዳመጥ ከቻለ በሕይወቱ ብዙ ለዉጥ ማምጣት ይችላል። የክርስትና ሕይወት እንዲሁ እንደሚወራዉ ቀላል አይደለም ክርስትናን ማወቅና ክርስትናን ተግባራዊ አድርጎ በሕይወት ኑሮ መኖር የሰማይና የምድር ያህል ልዩነት አላቸዉ ወንጌል በሕይወት ትገለጥ ዘንድ ዕዉቀትን ተግባራዊ ማድረግ ተለማመዱ።

@Nkuyemedankenzare
250 views18:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-07 18:22:48 የጾም ጥቅም!

ምግብ ሲበዛ ለአደጋ ያጋልጣል መኪና ፍሬኑን ሲበጥስ መንገድ ስቶ ወደ ገደል እንደሚገባዉ ሁሉ የሰዉ ልጅም ለሥጋ ምቾቱ አድልቶ እየበላና እየጠጣ የሚኖር ብቻ ከሆነ ለተራበና ለተቸገረ የማያዝን፥ ለሰዉ ክብር የሌለዉ ሰዉነትን በቁስ ነገር የሚለካ፥ አምላኩን በአፍ እንጂ ከቶ የማያዉቅ ፍጥረት ይሆንና በሥጋ ስለ ሥጋ ብቻ የሚኖር ስለሚሆን የመጾም ጥቅሙ እየበላዉና እየጠጣዉ በምቾት ልኑር የሚለዉን የሥጋ ፈቃድ ስለሚገታ ለተራበ፥ ለተጠማ ለተቸገረ ሰዉ እንድናዝን ያደርገናል ማለት ነዉ፥ በነገሬ ላይ የሰዉ ልጅ ክፉና ጨካኝ የሚሆነዉ ነፍስ በኀጢአት አዘቅጥ ዉስጥ ወድቃ እንስሳዊ ባሕሪዉ ጎልቶ ሲወጣ ነዉ ( የሥጋ ፈቃድ ነፍስ ላይ ሲሰለጥን ማለት ነዉ) መሰረታዊ የጾም ጥቅሙ ደግሞ በነፍስ ጽድቅን ያሰጣል፥ ከእግዚአብሔር ጋር ያስታርቃል። ልብ በሉ፥ መጾም የሚከብዳችሁ በረከተ እግዚአብሔር ስለሚርቃችሁ ነዉ። መድሃኒታችን እግዚአብሔር ሰይጣን ካቀረበለት ፈተናዎች አንዱ ድንጋዩን ዳቦ አድርግ የሚል የስስት ፈተና ሲሆን መድሃኒቱም መልሶ የሰዉ ልጅ ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣዉ ቃል እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም ብሎ የዲያቢሎስን ፈተና ድል እንደነሳል ሁሉ ማቴ፤4 ጾም የሚጾመዉ በምግብ ኀይልና በራስ አቅም ሳይሆን በእግዚአብሔር ቸርነትና እርዳታ ነዉና አስቀድማችሁ በምግብ ኀይልና በራሳችሁ አቅም እንደምትጾሙ ማሰባችሁን ከአእምሮአችሁ አዉጥታችሁ በእርሱ ቸርነት እንደምትጾሙ አስባችሁ መጾም አለባችሁ መድሃኒታችን የማይችሉትን አቅመ ደካሞችን ብርቱ የሚያደርግ እጹብ ድንቅ አባት ነዉና በእርሱ ተመርኩዛችሁ ጹሙ። ስትጾሙም የረሀብ አድማ ራሳችሁ ላይ አዉጃችሁ መመገብ ሳይሆን በፈቃዳችሁ ተርባችሁ ያለ ፈቃዱ እየተራበ ያለዉን ወንድማችሁን እየመገባችሁ መሆን አለበት።

@Nkuyemedankenzare
308 views15:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-07 18:22:48 ሳያቋርጡ የመስገድ ጥቅም!


በሰዉ ልጆች ሕይወቱ ዉስጥ ብዙ ዉጣ ዉረድና ሸክም አለ ቢወራ ከንፈር መጦ ዝም ከማለት ዉጪ ምፍትሔ የታጣለት ዉስጥ ባዶ ሆኖ ላይ የጸዳበት የሕሊና ሰላም ተገፎ ደስታ የታጠበት ለብቻ የሚያስቆዝም ሕመም ተሸክሞ ሕይወቱን የሚመራ በዚህ ዘመን ይበዛል ማንም ቢሆን ይሄንን ሸክሙን አራግፎ የሰላም ሕይወትን መምራት የሚጠላ የለም ሁሉም ይፈልጋል ለዚህ ችግር መፍትሔዉ ያለዉ እግዜር ጋር ብቻ ነዉ የስግደት ኀይል ምን ያክል እንደሆነ የምንረዳዉ የሕይወት ዉጣ ዉረድ አስለቺ ሆኖባቸዉ በሰዎችም ዘንድ ተጠልተዉ በራሳቸዉ ተስፋ ቆርጠዉ ከተቀመጡ አይሁዶች መማር እንችላለን። በአይሁድ ዘንድ የለምጽ በሽታን እርኩሰት በመሆኑ ለምጽ የያዘዉን ሰዉ ያገሉታል እንጂ አያቀርቡትም ዘፍ፤13 እና 14 ታዲያ ለዘመናት በለምጽ በሽታ ሲሰቃይና በሰዎች ዘንድ ሲገለል የነበረዉ ሰዉ ከኀጢአት ባርነት ነጻ አዉጥቶ የልጅነት ጸጋ ሊሰጠን የመጣዉን መድሃኒታችንን ባየዉ ጊዜ ወደ እርሱ ቀርቦ ሰገደለትና አቤቱ ብትወድስ ልታነጻኝ ትችላለህ እያለ ለመነዉ መድሃኒቱም እወዳለሁ ንጻ ብሎ ዳሰሰዉ ከዚህም ስቃይ ዳነ ይሄም ሰዉ በስግደትና በጸሎት ኀይል ከሰቆቃ ኑሮ ነጻ ወጥቶ በሰላም ከወገኖቹ ጋር ለመቀላቀል በቃ ሉቃ፤5፤12-13 የስግደት ኀይል በዚህ ብቻ አያበቃም የሥጋ ፈዉስ ካገኘን በኋላ ድምጽ ሳናሰማ ሽል ብለን ወደ ነበርንበት እንዳንመለስ አሥራ ሁለት ዓመት (12) ደም ይፈሳት የነበረችሁ ሴት ምስክር ትሆንናለች ይህቺ ሴት አሥራ ሁለት ዓመት ሙሉ ደም ይፈሳት ነበረ ለዚህ በሽታዋ መፍትሔ ፍለጋ ገንዘቧን ለባለመድሃኒቶች በመስጠት የጨረሰች መፍትሔ ሳታገኝ ባዶዋን የቀረች በበሽታዋ ምክንያት ቤተሰቦቿ ወዳጅ ዘመዶቿ የራቋት ሁሉ ተጸየፏት ብቻዋን የምትሰቃይ ሚስኪን ሴት ናት የወደቁትንና የተገፉት ሊሰብስብ የመጣዉን መድሃኒታችንን ባየችሁ ጊዜ በእምነት የልብሱን ጫፍ ብነካ እድናለዉ ብላ የልብሱን ጫፍ ብትዳስሰዉ ከዚህ ስቃይ ተፈወሰች ከዳነች በኋላ ዝም ብላ ልትሄድ ስትል ወደ እቅፉ ገብተን ዳግም ከእቅፉ እንዳንወጣበት የማይፈልገዉ መድሃኒታችን ማነዉ የነካኝ ሲል ጠየቀ በዚህ ጊዜ ነገሩ እንዳልተሸሸገላት ስታዉቅ ከሰገደችለት በኋላ ምስክርነቷን ሰጠች። ሉቃ፤8፤41-47 ዮሐ፤9፤36፣እና 12 ቅዱሱ መፅሐፍ ላይ እንደተመለከትነዉ ስግደት ከብዙ መከራ ዉስጥ አዉጥቶ ወደ ተሻለ የሕይወት ደረጃ ይወስዳል። በልዩ ልዩ መከራ ዉስጥ ያላችሁ እናንተስ በምን ዓይነት ችግርና ስቃይ ዉስጥ ትገኛላችሁ? በሕይወታችሁ ዉጣ ዉረድ በዝቶ ብቻችሁን የምትሰቃዩ ወገኖቻችን የመድሃኒታችን ድንቅ ሥራ ቅዱሱ መፅሐፍ ላይ ብቻ ታሪክ ሆኖ አልቀረም አንተ አንቺ እናንተ እኛ ሕይወት ዉስጥም ይሰራል ችግራችሁ ምንም ይሁን ምን ከኀጢአት ባርነት ነጻ ትወጡ ዘንድ እርሱ ፊት ወድቁ አሰልቺ የሆነባችሁን ነገር በሙሉ አራግፎ በሰላም እንድትኖሩ ያደርጋችኋል። መከራችሁንና ፈተናችሁን ለሰዉ ብታወሩ ዘላቂ መፍትሄ አታገኙም እግዚአብሔር ዘንድ ግን መፍትሄ የሌለዉ ሕመምና ስቃይ የለም በምንም የኀጢአት አዘቅጥ ዉስጥ ብትወድቁም በማወቅ ሆነ ባለማወቅ አንዴ በድላችኋል ዳግም ላለመበደል ግን ወደ እግዚአብሔር ቀርባችሁ ይቅርታዉን ከልብ ፈልጉ።
( ፩) ሳያቋርጡ የመስገድ ጥቅሙ ሕሊና በኀጢአት ሲቆሽሽ እንስሳዊ ባሕሪዉ ጎልቶ ስለሚወጣ የሰዉ ልጅ ለሚሰራዉ ኀጢአት ጸጸት የማይሰማዉ ፍጥረት ስለሚሆን ስግደት ደግሞ የሥጋ ፈቃዳን ጎስሞ የዲያቢሎስን ትዕቢት ስለሚያዋርድ እግዚአብሔርን እንደበደልነዉ ከልብ የመነጨ ኀዘን አጎናፅፎን ወደ ንስሀ የሚመራ አንዱ ጠላታችንን የምንዋጋበት የጦር ዕቃችን ነዉ። (፪) ዲያቢሎስ በባሕሪዉ አታላይና አስመሳይ ፍጥረት ነዉ ባላጋራ ነዉና የሰዎችን ደካማና ጠንካራ ጎን ስለሚያዉቅ መስገድ በጀመራችሁ ጊዜ ድኛለሁ ብላችሁ ነገር ዓለሙን እንድትተዉ በማድፈጥ የጥፋት መረቡን ሰብስቦ ዝም ይላል በዚህ ጊዜ የሥጋ ፈዉስና በተቸገራችሁበት ነገር መፍትሔ ያገኛችሁ ስለሚመስላችሁ ስግደቱን ስታቋርጡ ጠብቆ ከበፊቱ የባሰ መከራ ሊያጸናባችሁ ይነሳል ማቴ፤12፤43-45 ታዲያ ሳያቋርጡ የመስገድ ጥቅሙ ጠላት እንዳያደፍጥ ስለሚያደርገዉ መሸሸጊያ አሳጥቶት ቀጥቅጦ ከሰዉነት ዉስጥ እንዲወጣ ያደርጋል፤ አስተዉሉ፦መስገድ ያለባችሁ የምትፈልጉት ነገር እስኪሟላላችሁ ሳይሆን ይህቺን ዓለም ተሰናብታችሁ ወደ ተስፋይቱ ምድር እስክትሄዱ ድረስ መሆን አለበት። በዘፈቀድ ዝም ብላችሁ አንድ ቀን ስግደት በሌላ ቀን እረፍት የምታዘዉትሩ ከሆነ አሰልቺ የሆነ ኑሮን ለመምራት ትገደዳላችሁ ስገደትን እያቋረጣችሁ መስገድ የለባችሁም፥ (፫) ሳያቋርጡ የመስገድ ጥቅሙ በሥጋ ፍትወት በዝሙት ፈተና ከመፈተንና ከልዩ ልዩ ፈተናዎች ይታደጋል ።(፬) ሳያቋርጡ የመስገድ ጥቅሙ መገዛትን፤ መታዘዝን፤ ማመስገንን፤ ፍቅርን፤ ትሕትናን፤ ያስተምራልና ሳታቋርጡ ስገዱ!



ሳያቋርጡ የመጸለይ ጥቅም!


የሰዉ ልጅ ቅድሚያ የሚሰጠዉ ከዉጪ ለሚገባዉ አዲስ አሳብ ሳይሆን መጀመሪያ ዉስጡ ተደላድሎ ለተቀመጠዉ አሳብ በመሆኑ አንዳንድ ምዕመናን በጸሎት ጊዜያት የአሳብ መበታተንና ቆሞ ለመጸለይ ችግር ሲያጋጥማቸዉ እግዚአብሔር ፊት ቆሜ እንዴት ክፉ አሳብ አስባለዉ ቁጭ ብዬስ እንዴት እጸልያለሁ ብለዉ አለመጸለይን እንደ መፍትሔ በመዉሰድ ጸሎቱን እርግፍ አድርገዉ ለመተዉ ይወስናሉ ይሄ ፈጽሞ የተሳሳተ መፍትሔ ነዉ፡እንዲህ አይነቱ እርምጃ ለሕመሜ የታዘዘልኝ መድሃኒት ስለማይጣፍጥ በሽታዉ ቢገድለኝ ይሻለኛል እንጂ መድሃኒቱን አልወስድም ብሎ እንደመወሰን ይቆጠራል፡የነፍስ መድሃኒቷ ጸሎት ነዉና ጸሎት ማቋረጥ ተገቢ አይደለም። እንዲህ የሚሆንበት ምክንያት ዲያቢሎስ ሕሊናን ተቆጣጥሮ እግዚአብሔር ፊት ቆሜ እንዴት ክፉ አሳብ አስባለዉ ብላችሁ ጸሎቱን እንድታቋርጡ አንዳች ባዕድ ድምጽ ከሕሊና ዉስጥ ሲያሰማችሁና ቆሞ ለመጸለይ የሰዉነት መዝለፍለፍ እንዲያጋጥማችሁ በማድረግ ስለሚያሸማቅቃችሁ እንጂ ችግሩ ከእናንተ ሆኖ አይደለም፡ ልብ በሉ! ወደ እግዚአብሔር የመቅረባችን ዋናዉ ዓላማ እንዲህ አይነቱንና መሰሎቹን ክፋቶችን ለማራገፍም ጭምር ነዉና የምትጸልዩት ጸሎት ለእናንተ ባይሰማችሁም ዲያቢሎስ በትክክል እየሰማ ነዉና ጸሎቱን ከማቋረጥ በርትታችሁ መጸለይ አለባችሁ በአሳብ ዥዉ ብላችሁ ለመሄድ የምትገደዱት ሕሊና በጠላት ቁጥጥር ስር ስለሚሆን የክፉዉን አሳብ ለማስተናገድ ተገዳችሁ ነዉና ጸሎታችሁ ትክክለኛ ጸሎት ባይመስላችሁም ለጠላት ትክክለኛ ጸሎት ነዉና ከመጸለይ አታፈግፍጉ፡ አትሸወዱ ጸሎት በማድረጋችሁ ለዉጡ ባይታያችሁም ለዉጡን የሚያዉቀዉ ስልት እየቀያየረ ፈተናዉን እንደቀጠለ ነዉ፥ መበርታታችሁን ባይታያችሁም መበርታታችሁን ያወቀዉ ጠላት አቅሙ እየተዳከመ ነዉና ሳታቋርጡ ጸልዩ። ሳያቋርጡ የመጸለይ ጥቅሙ ከሰዎች ጋር ከተቀራረብን በኋላ ከቀን ወደ ቀን ከጊዜ ወደ ጊዜ ወዳጅነታችን ተጠናክሮ የልብ ሚስጢረኛችን እንደምናደርጋቸዉ ሁሉ በጸሎት ምክንያት በየዕለቱ ከእግዚአብሔር ጋር የሚኖረን ቅርርብ ደግሞ ከዚህ በበለጠ መንገድ በየዕለቱ እየጨመረ እየጨመረ ስለሚሄድ እርሱን ብቻ የልብ ወዳጃችን የልብ ሚስጢረኛችን የችግራችን ተካፋይ እንዲሁም ለጉድለታችን መፍትሔ ሰጪ እናደርገዉና የእርሱ ፍቅር ከምንምና ከማንም በላይ ሆኖብን እንድንኖር ያደርገናል፥ ጸሎት ማድረግ እንዲሁ ቀለል አድርገን እንደምናስበዉ አይደለም በጸሎት ምክንያት ከእግዚአብሔር ጋር የሚኖረን ግንኙነት እጹብ ነዉና ጸሎትን በአግባቡ ተጠቀሙበት።
286 viewsedited  15:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-19 19:28:36 በረከታችሁን በከንቱ አታባክኑት!


የ21ኛዉ ክፍለ ዘመን ትዉልዶች የሆነዉ የማንበብና የመጻፍ ችግር የለብንም ነገር ግን ዕዉቀትን በሕይወት ኑሮ ዉስጥ ተግባራዊ አድርገን የመኖር ትልቅ ፍርሃትና ችግር አለብን! በዚህም ምክንያት 95 በመቶ በጭፍኑ የሚጓዝ ሆኗል፡ ምክንያቱም እግዚአብሔር በሰጠን መክሊት ሰርተን ማትረፍ ስላልቻልን፥ የመክሊት ባለቤት መሆን ማለት የግድ፤ ዘማሪ፤ዲያቆን፤ ቄስ፤ ሰባኪ፤ መሆን ማለት አይደለም እነዚህ መክሊቶች እንደ አምላክ ቸርነት ከብዙ ልፋትና ጥረት በኋላ የሚገኙ ተጨማሪ ስጦታዎቻችን ናቸዉ እንጂ ቁጭ ብለን ስለፈለግናቸዉና እድለኛ ስለሆን ብቻ የምናገኛቸዉ አይደሉም መድሃኒታችን እግዚአብሔር እነዚህንና እነዚህን መሰል ሌሎች ተጨማሪ መክሊቶችን ሰርተን እንድናተርፍበት እጅ እግር ዓይን ጆሮ አንደበት ሆድ የሚባሉ መክሊቶች ለሁላችንም ተሰጥቶናል ችግሩ በረከቶቻችን በአግባቡ ተጠቅመንበት ሌላ ተጨማሪ በረከት አናተርፍበትም እንጂ ሳንታክት ብንሰግድ ሳንታክት ብንጸልይ እሺ በጀ ብለን ንስሀ ገብተን በቅዱስ ቁርባን ብንታተምና ከመድሃኒቱ ጋር ሕብረት ፈጥረን ብንኖር መሆን የምንፈልገዉንና መድረስ ካለብን ደረጃ ላይ ከመድረስ የሚያግደን አንዳች ነገር አይኖርም ነበረ! ብዙሃኖቻችን ጋር አንድ የተሳሳተ አስተሳሰብ አለ እርሱም የ40 ዕድል የሚባል ነገር ይሄ አስተሳሰባችን ተጽዕኖ ስላሳደረብን ዉስጣችን ያለዉን ኀይል ወደ ዉጪ አዉጥተን እንዳንጠቀምበት አድርጎን በልባችን ዉስጥ ሸምቀን ለማስቀመጥ አስገድዶናል ልብ በሉ! እግዚአብሔር አምላካችን ሁላችንንም ሲፈጥረን እኩል አድርጎ እንጂ አንዱን አሳንሶ አንዱን አስበልጦ አልፈጠረም፡ ችግሩ ከመሰረቱ ተይዘን የምናድግበት አስተዳደግና ራስ ጋር ሆነና እርሱ የሰጠንን በረከቶቻችንን በአግባቡ ሳንጠቀምበት በመቅረታችን መሆንና ማግኘት የምንፈልገዉን ነገር በልባችን ሸምቀን ለመቀመጥ ተገደድን እንጂ መድሃኒታችን እግዚአብሔር የሚያዳላ አባት ሆኖ አይደለም፥ ዛሬም ከልብ ለዉጥን በመሻት ወደ እግዚአብሔር ብንቀርብ ፈልገን የምናጣዉ አንዳች ነገር የለም፡ ስለዚህ የማይጨበጥ ተስፋ እያሰባችሁ የተፈጥሮ በረከታችሁን በከንቱ አታባክኑ ቁጭ ብለን ካለብን ችግር ዉስጥ ለመዉጣት ስለፈለግንና ስላሰብን ብቻ የምናመጣዉ ለዉጥ የለም ሀሳብ ወደ ተግባር ካልተለወጠ ደግሞ የማያልቅ ቅዠት ይሆንና ሕይወትን በምሬት ጀምረን በምሬት ለመጨረስ እንገደዳለንና ጥራችሁ ግራችሁ ሌላ መክሊት የምታተርፉበትን አንደበታችሁን እጅ እግራችሁ ዓይን ጆሮአችሁን ሆድና አእምሮአችሁን በከንቱና ለከንቱ ነገር አታዉሉት በጉልበታችሁ ስገዱበት በሆዳችሁ ጹሙበት በአንደበታች ጸልዩበት በዓይናችሁ ቅዱሱን መፅሐፍ አንብቡበት በጆሮአችሁ መልካም ነገር ስሙበት በአእምሮአችሁ መርምሩበት የሰበሰባችሁትን ዕዉቀት በሕይወት ኑሮአችሁ ኑሩት ለጥቆ ተጨማሪዉን መክሊት ለሰጪዉ ተዉለት ጊዜዉ ሲደርስ ዋጋችሁን በግልጥ ይሰጣችሁኋልና። ለራሳችሁ ጥቅም ስስታም አትሁኑ ቆማችሁ መጸለይ የማትችሁ ከሆነ አቅሙን እስክታገኙ ቁጭ ብላችሁ ጸልዩ ብዙ መስገድ ባትችሉ ጠዋት 3 ማታ 3 መስገድ አያቅታችሁም ግማሽ ቀን መጾም ባትችሉ አረፋፍዶ መመገብ አያቅታችሁም መፅሐፍ ቅዱስ ብዙ ማንበብ ቢያቅታችሁ አንድ ምዕራፍ ማንበብ አያቅታችሁምና ካለባችሁ ችግር ወጥታችሁ ብርሃንን ታዩ ዘንድ በምትችሉት ታገሉ ኦርቶዶክሳዊያን የጉስቁልና መንፈስ ነዉ ያለባቸዉ ለመባል የበቃነዉ ከእግዚአብሔር ርቀን ከአንገት በላይ በአፍ ብቻ አባታችን ሆይ እያልን የአባትነቱን ጣዕም ባለማወቃችንና በሕይወት ኑሮአችን ላይ እንዲገለጥ ባለመፍቀዳችን ነዉና ደጃችሁ በር አፍ ላይ ቆሞ በራችሁን እንድትከፍቱለት ለሚለምናችሁ በራችሁን ክፈቱለት ወደ ቤታችሁ ይገባ ዘንድ ፍቀዱለት።እንዲሁ በማሰብ በመመኘት በማዉራት በማስመረር ብቻ የሚፈጠር አንዳች ነገር የለም፤ የግድ ሀሳብ ወደ ተግባር መለወጥ አለበትና ተንቀሳቀሱ ከመድሃኒቱ ጋር ሕብረት ፈጥሮ ካልተጉ ዉጤት የለም ካልጣሩ ማግኘት የለም ካልታገሉ ማሸነፍ የለም ስለዚህ የህልም እንጀራና ምዕናብን መከተል ይብቃችሁና ሀሳባችሁን ወደ ተግባር ለዉጡት ተአምር ከሰማይ እንዲወርድ አትጠብቁ ተአምር የምትፈጥሩበት ዉድ የአምላክ በረከቶች አላችሁና ከተቀመጣችሁበት ተንቀሳቀሱ ለምትፈልጉት ነገር ቀጠሮ አትስጡ ነገም ሌላ ቀጠሮ ይዞ ይመጣልና ወደኋላም ዘወር ብላችሁ ትናንትናችሁንም ተመልከቱ ስንት ትናንቶችን ለነገ ብላችሁ በቀጠሮ በማለፋችሁ ዛሬም ምንም የመጣ ለዉጥ እንደሌለ አስተዉሉና ነገ ልታደርጉ ያቀዳችሁትን ዛሬ አድርጉት እግዚአብሔር ይዞ ሽንፈት የለምና!!!!!

እንኳን ለዓብይ ጾም በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን! መልካም የጾም ጊዜ ይሁንላችሁ በርቱና ጹሙ!

@Nkuyemedankenzare
648 viewsedited  16:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-18 12:27:26 የት አለ አንተን መፍራት!
የት አለ አንተን ማክበር!

@Nkuyemedankenzare
483 views09:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-17 22:00:44 ይሄ ሁሉ ልፋትና ድካም ያስፈለጋቸዉ በመጨረሻዉ ዘመን (the new world order) የአዲሱን ዓለም መንግስት ስርዓት መስርተዉ ዓለምን ጠቅልለዉ ለዲያቢሎስ ለማስገዛት ስለሚፈልጉና ቀጣዩም (generation) በቀላሉ ለዲያቢሎስ እንዲገዛ ከወዲሁ ኀጢአተ ሰዶምን በዓለም ለማስፋፋት ሲሉ በረቀቀ ስልታቸዉ አሳማኝ በሆነ በዉሸት ቃላት እርኩሰትን እያለማመዱ ስለሆነ ነዉ. 1.2 million ሰዉ በዚህ እርኩሰት ተጠመደ ማለት የዓለም የሕዝብ ቁጥርም በዚያዉ ልክ ይቀንሳል ማለት ነዉ ያዉ እንግዲህ ዲያቢሎስ የአዳም ዘር እንዲበዛ ስለማይፈልግ በረቀቀ ስልቱ በአንድም በሌላም እያደረገ የሕዝብ ቁጥርን እንዲቀን ለማድረግ ጠንክሮ ይሰራል ማለት ነዉ፡ ይሄ ስልቱ ሰፊ ዝርዝር ስላለዉ እመለስበታለዉ።



የግለ ወሲብ ጥገኛ መሆን የሚያስከትለዉ ጉዳት፡



የግለ ወሲብ ጥገኛ የሆነ ሰዉ በሰዉነት ዉስጥ ያለዉን ፕሮቲንና ካልሲየም እንዲቀንስ በማድረግ አቅመ ደካማ ያደርገዋል፡ ለስንፈተ ወሲብ ያጋለጣል፡ፈጣን ንቃተ ሕሊና ያሳጣል ድብርት ዉስጥ ያስገባል ያፈዛል ያደንዝዛል፡ የማስታወዝ አቅም ያዳክማል ከሰዎች ጋር መግባባት እንዳንችል ያደርጋል ብቸኝነትን እንድናዘዉትር ያደርጋል ሱስ በመሆን ሕይወትን ይቆጣጠራል፡ ከተቃራኒ ጾታ ያሸሻል፡ የወንዱ የዘር ፈሳሽ እንዲቀንስ በማድረግ ለፅንስ አዳጋች ያደርጋል፡ የበታችነት ስሜትን ስለሚያስከትል በሆነዉ ባልሆነ ተነጫናጭ ያደርጋል፡ ወዘተረፈ ልዩ ልዩ ጉዳቶች ያስከትላል፥ አስተዉሉ! ዲያቢሎስ ማለት አተርፍ ባይ አጉዳይ ነዉ ክብርና ከፍታን ሲፈልግ የነበረዉን ክብር ተገፎ ወደ ታች ወርዶ ከክብሩ ተዋርዷል ይሄ ትዕቢቱ ከዉድቀት ሊያነሳዉ አልቻለም ዛሬም ቀጥሎበት የእግዚአብሔር የሆነዉን ለመዉሰድ ይታትራል እንደማይሆንለት እያወቁ እንኳን ተስፋ የማይቆርጥ ጨለምተኛ ነዉ ባላጋራ ነዉና በአንድም በሌላም ሰዎችን ሲቆራኝ ይሄን ባሕሪዉን ስለሚያዋርስ ሰዎችም ኀጢአት ሲሰሩ የተሻለ ነገር አገኛልዉ በሚል አስተሳሰብ እርኩሰትን ይጀምሩና መዉጫ የሌለዉ ገደል ሲሆንባቸዉ ተስፋ ቆርጠዉ ጨለምተኛ ሕይወት ለመምራት ይገደዳሉ። አብዛኞች ግለ ወሲብ የሚጀምሩት አተርፍ ባይ ሆነዉ ነዉ የባሰ አዘቅጥ ዉስጥ ከገቡ በኋላ ሕይወት ከባድ ሲሆንባቸዉ የማይሆን እርምጃ እራሳቸዉ ላይ ለመዉሰድ የሚገደዱት በዚህ ጸያፍ ምግባር ተጠምደዉ ሱስ ከሆነባቸዉ በኋላ ከዚህ ሕይወት ዉስጥ መዉጣት አቅቷቸዉ ሀፍረተ ሥጋቸዉ ላይ ጉዳት እስከማድረስ የደረሱ ሰዎች አሉ፡ራሳቸዉን እስከማጥፋት የሚደርሱ አሉ፡ ግብረ ሰዶም የሆኑ አሉ፡ ወዳጄ፥ እግዚአብሔር አምላካችን ካለመኖር ወደ መኖር የሚያመጣን በእኛ ሊከብር በእኛ ሊመሰገን ነዉና ወደ እርሱ ቀርበን ከእርኩሰት ልንላቀቅ እጅጉኑ ያስፈልገናል እርሱ ለምን በደልከኝ አይልም ብትበድልም አፍቃሪ አባትህ ነኝና ወደኔ ቅረብና ጠላትህን ድል ልንሳልህ ይለናል እንጂ ለምን ኀጢአት ሰራቹ ብሎ አይተወንም በዉኑ ኀጢአተኛ ይሞት ዘንድ መፍቀድን እፈቅዳለሁን? ይላል የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር፤ ከክፉ መንገድ ይመለስ በሕይወት ይኖር ዘንድ ነዉ እንጂ ሕዝ፤18፤23 የፈለገዉን ያህል በኀጢአት ብንቆሽሽ ከነቁሻሻችን ተቀብሎ ከበረዶ ይልቅ የሚያነጣን መዝ፤51፤7 እጽብ አባት አለንና ልንሸማቀቅ አያስፈልገነም ብቻ ወደ እርሱ ከነድካማችሁ ቅረቡ ሌላዉ ዝሙት ሰዉ ላይ የሚሰልጥነዉ ምግብ ሲበዛና ሥጋ ሞቾት ሲበዛበት ነዉና ሳታቋርጡ በአቅማችሁ የአምልኮ ስግደት ስገዱ ጸልዩ ጹሙ ለጥቆ በንስሀ ታጥባችሁ በቅዱስ ቁርባን ታተሙ መፍትሔዉ ነዉ! ወጥነት ያለዉ መንፈሳዊ ዉጊያ ከተገበራችሁ ከየትኛዉም የኀጢአት አዘቅጥ ዉስጥ መዉጣት ትችላላችሁ ብቻ የአምልኮ ስግደት አታቋርጡ ጸሎት አታቋርጡ በምትችሉት ጹሙ በንስሀ ታጥባችሁ እየቆረባችሁ ከመድሃኒቱ ጋር ሕብረት ፍጠሩ ድሉ የእናንተዉ ነዉ፡፡

ይቀጥላል…

@Nkuyemedankenzare
504 viewsedited  19:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-17 22:00:44 ግብረ ሰዶማዊነት የሚስፋፋበት ሚስጢራዊ መንገድ፡

ግለ ወሲብ፥


የሰዉ ልጅ ከእንስሳ የሚለየዉ ማሰብ በመቻሉ ነዉ ምክንያቱም ከየት እንደመጣችና ወዴት እንደምትመለስ የምታዉቅ ሕያዊት የሆነች ረቂቅ ነፍስ በዉስጡ ስላለች ማለት ነዉ፡ ይህቺ ነፍስ በኀጢአት ቆሽሻ በጨለማ ስትዋጥ ሰዉ የተባለዉ ፍጡር አእምሮዉ ይጠብና ሆዱ ይሰፋል አእምሮ ወደ ሆድ ተቀየረ ማለት ደግሞ ሰዉ ለመብልና ለመጠጥ ለልብስና ለዉበት ለሀብትና ንብረት በሥጋ ስለ ሥጋ ብቻ የሚጨነቅ እኔ ባይ ሆኖ በመንጋ የሚጓዝ ይሆናል፡ እንደምናየዉ ፍቅር ጠፍቶ አንዱ አንዱን ለማጥፋት ደፋ ቀና የሚል የበዛዉ አእምሮ ጠቦ ሆድ ስለሰፋ ነዉ፡ እንስሳ ሰዉ ወደ መራዉ እንደሚጓዝ ሁሉ ሕሊናም በኀጢአት ቆሽሾ ሲጨልም ዲያቢሎስም ሰዎችን በመንጋ ወደ ፈለገዉ አቅጣጫ ይመራ ማለት ነዉ። በረከቱ ይደረብንና ሐዋሪያዉ ቅ•ጴጥሮስ በ1ኛ መልዕክቱ ምዕ፤5፤8 ላይ በመጠኑ ኑሩ ንቁም ባላጋራችሁ ዲያቢሎስ የሚዉጠዉን ፈልጎ እንደሚያገሳ አንበሳ ይዞራልና፡ ሲል ያስጠነቀቀን ሆድ ሲሰፋ አእምሮ ስለሚጠብ ነዉ። የጥንቶቹ ቅዱሳን ከመድሃኒቱ ጋር ሕብረት ፈጥረዉ በመጠኑ በመኖራቸዉ ከሰማያዊዉና ምድራዊ በረከት ተካፋይ ሆነዉ የሰዉን ሥጋ ተገን አድርጎ ዉጊያ የሚከፍትባቸዉን የጠላትን ሴራ እያፈራረሱ የመድሃኒቱ አባትነትና ክብር በእነርሱ ላይ ከፍ ብሎ ታይቶ ስልጣኔን ለዓለም አስተዋዉቀዉ በክብር ወደ መጡበት ተመልሰዋል ከመድሃኒቱ ጋር ሕብረት መፍጠር ያልፈለገዉ ትዉልድ ደግሞ ስልጣኔ መርዝ ሆኖበት የነፍስ ሟቲ ሆኖ ቀረ፥ ልብ በሉ! ስልጣኔ ያመጣብንን ጉዳት ደጋግሜ ሳወሳችሁ ስልጣኔ አያስፈልገነም ማለቴ አይደለም ያስፈልገናል ግን የእግዚአብሔር ሕብረት የሌለበት ስልጣኔ የሞት ሞት ስላመጣብን ንቁና ከመድሃኒቱ ጋር ሕብረት ፈጥራችሁ መርዙን ወደ ወተት ለዉጡት ነዉ የምላችሁ እንጂ ስልጣኔ አያስፈልገነም አላልኩም እንደምታዩት ከመድሃኒቱ ጋር ሕብረት ፈጥረን የምንጠቀምበት ስልጣኔ'ማ እኔና እናንተን በቀላሉ እያማማረን ነዉ፥ አዎ ወዳጄ መድሃኒቱ ጣልቃ ያልገባበት ስልጣኔ ተንቀሳቃሽ የቁም ሟቲ አድርጎናልና መንቃት ያስፈልገናል፡



ቀደምቶቻችን በጠዋት ተነስተዉ ምግብ አያዉቁም ጸሎት እንጂ ሲሰሩ ዉለዉ ተመግብዉ መተኛት አያዉቁም ጸሎትና ስግደት እንጂ ፈተና ሲያጋጥማቸዉ ወደ ሰዉ መሮጥ አያዉቁም ወደ እግዚአብሔር እንጂ እኔና እናንተስ ከእንቅልፋችን እንደነቃን ቁርስና ከfb'ና Tg ከTwitter'ና Instagram ከYouTube'ና tiktok ላይ መረጃ መሰብሰብ ይታየናል እንጂ በጸሎትና በስግደት ለመድሃኒቱ መገዛት አያስፈልገነም ከሰዓታት በኋላ ደግሞ ተጨማሪ ምሳ ያስፈልገናል ለጥቆ ቀኑን በስራ ስላሳለፍን እራትና የተለያዩ ድህረ ገጾችን እየጎበኘን አእምሮን ዘና ለማድረግ (motivation) ንግግሮች ያስፈልገናል እንጂ በጸሎትና ስግደት መድሃኒቱን ማመስገን አያስፈልገንም ስለዚህ? ስለዚህማ ሆድ ሲሰፋ አእምሮ ጠበበና ሰማያዊዉና ምድራዊዉ ሚስጢረ ነገር ተሰወረብን ብናነብ የማይገባን ብንማር የማይገባን እየሰማን የማንሰማ እያየን የማናይ ስንሆን ጊዜ እንስሳዊ ባሕሪያችን ከፍ አለና ዝሙትና እርኩሰት ነገሰብን ማለት ነዉ በዚህም ምክንያት 95 ከመቶ ታማሚሆች ነን ችግሩ የነፍስ ሕመምተኛ መሆናችንን አምኖ መቀበሉ ላይ ነዉ እንጂ።



ወደ መነሻዉ መንገዴ ልመለስና ሰዶማዊነት በአዉሬዉ ዘመን መብት ሆኖ ይከበራል በምዕራቡ ዓለም ይሄ እርኩሰት ፍቃድ አግኝቶ ተግባራዊ ሆኗል በሀገራችንም በግልጥ ሳይሆን በድብቅ ዉስጥ ዉስጡን በመስፋፋት ላይ ይገኛል፥ በነገሬ ላይ አዉሬ እየተባለ የሚጠራዉ የሰዉ ልጅ ነዉ እንጂ ሌላ ነገር አይደለም በመጨረሻዉ ዘመን እኔ ክርስቶስ ነኝ ብሎ የሚመጣዉ ሀሳዊ መሲህ ነዉ አበዉ ይሄ ሀሳዊ መሲህ ከኤሳዉ ነገድ እንደሚወለድና ስሙም መርመርምያኖስ እንደሚባል እያንዳንዱን ነገር በዝርዝር አስቀምጠዉልናል፡ ያዉ እኛ ከመድሃኒቱ ጋር ሕብረት ስለሌለን ብዙ ነገሮች ተሰዉሮብና እንጂ ወደ ሀሳቤ ልመለስና ግብረ ሰዶማዊነት ባለፈዉ ክፍል ላይ እንደገለጥኩት አእምሮ ያላቸዉ የሚመስሉ ግን ፈፅሞ አእምሮ የሌላቸዉ ሰዎች ተግባር ነዉ ይሄ እርኩሰት ከሚስፋፋባቸዉ መንገዶች አንዱ ግለ ወሲብ ነዉ ግለ ወሲብ በልዩ ልዩ መንገዶች ይጀመራል' ልቅ በሆነ በቃላት ልዉዉጥ፥ የወሲብ ፊልም በመመልከት፥ የወሲብ ፍላጎት ቀስቃሽ በሆኑ ፅሑፎችን በማንበብ፥ ወሊድ መቆጣጠሪያ በሚል ሰበብ፥ አላስፈላጊ በሆኑ (picture'ሮችን) በመመልከት፥ በአቻ ለአቻ ግፊት' ከማህፀን በሚቆራኙ መናፍስቶችና ወዘተረፈ ……በብዙ መንገዶች ግለ ወሲብ ይጀመራል፤



ልብ በሉ! እርኩሳን መናፍስት ሥጋና አጥንት ስለሌላቸዉ አይጨበጡም አይዳሰሱም አይታዩም ስለዚህ እርኩሰትን ለሰዉ ልጆች ለማለማመድ የግድ ግዙፉ አካል ያስፈልጋቸዋል ዘፍ፤3 ማቴ፤24፤37-40 ማለት ነዉ። ከዚህ እርጉም ጋር ሕብረት ያላቸዉ የእርሱ መንገድ ጠራጊ የሆኑትን የምዕራባዊያንን ሥጋ ሽፋን በማድረግ በረቀቀ ስልቱ እርኩሰትን ለሰዉ ልጆች እያስተማረ የሲኦልን ነፍሳት ያበዛል ማለት ነዉ። ታዲያ ግለ ወሲብንም ሲያለማምድ አስቀድሞ ሰፊ ስራዉን የሚሰራዉ አእምሮ ላይ ነዉ እርግዝና እንዳይፈጠር ግለ ወሲብ መፍትሔ ነዉ፡ ወደፊት ትዳር ሲመስርቱ በሥጋ ሩካቤ ጊዜ እንዳይቸገሩ ግለ ወሲብ ያስፈልጋል የወሲብ ፍላጎት ቀስቃሽ ልቅ የሆነ ቃላት ልዉዉጥና ፅሑፎችን መላላክ እርድና ነዉ፡ ለስንፈተ ሩካቤ ወሲብ ቀስቃሽ የሆኑ ምስሎችን መመልከት ተገቢ ነዉ ነገሩን በጭፍኑ ከክፉ (angle) ሆነ ስንመለከተዉ ልክ የሚመስል ግን ልክ ያልሆነ በዉስጣቸዉ ገዳይ መርዝን የያዙ ናቸዉ። ይሄ እርኩሰት እግዚአብሔርን የሚያስቆጣዉ ሲልም የሞት ቅስፈት የሚያስከትል ዘፍ፤38፤8-10 ምግባር መሆኑን ጠላታችን ያዉቀዋል ስለዚህ አስቀድሞ አእምሮን አደንዝዞ ነገሮችን እርሱ ከሚያሳየን አቅጣጫ ብቻ እየተመለከትን እግዚአብሔርን ያሳዝነዉ አያሳዝነዉ ሳንመረምር በጭፍኑ ዘዉ ብለን የዲያቢሎስ ወጥመድ ዉስጥ ጥልቅ እንላለን እዚህ ጋር ሕዝቤዉ ዕዉቀት ከማጣቱ የተነሳ ጠፍቷል የሚለዉ የመፅሐፍ ቃል ተግባራዊ ሲሆን እናገኛለን ሆሴዕ፤4፤6፡፡ መፅሐፍን የመመርመር ዕድል ቢኖረን ሁሉም ነገር በግልጥ እናገኘዉ ነበር' አብዛኛዉ ወጣት ሆነ ባለትዳር ግለ ወሲብን አቅልለዉ ከጀመሩ በኋላ ከገቡበት ገደል መዉጣት የሚያቅታቸዉ ዲያቢሎስ አእምሮን አስቀድሞ ስለሚመርዝ ነዉ፡፡ የግለ ወሲብ ሱሰኛ የሆነ ሰዉ ከዚህ ጸያፍ ምግባር በንስሀ ታጥቦ በቅዱስ ቁርባን ታትሞ ወደ እግዚአብሔር ካልተመለሰ የወደፊት እጣ ፈንታዉ ግብረ ሰዶም መሆን ነዉ ምክንያቱም ግለ ወሲብ ከቃሉ እንደምንረዳዉ ከራስ ጋር የሚደረግ ጸያፍ እግዚአብሔር የሚጠላዉ ምግባር ነዉ በዚህ እርኩሰት የተጠመዱ ብዙሃኖች ከተቃራኒ ጾታ ጋር የሥጋ ሩካቤ መፈጸም አይፈልጉም ምክንያቱም ከራሳቸዉ ጋር የሚፈጽሙት እርኩሰት የሚሰጣቸዉን ደስታ ከተቃራኒ ጾታ ጋር የሚፈጽሙት የሥጋ ሩካቤ ደስታ ስለማይሰጣቸዉ ማለት ነዉ። አንዳንዶቹ ደግሞ በዚህ ሱስ ተጠምደዉ ከነጭራሹ ከተቃራኒ ጾታ የሚሸሹ ቤት ይቁጠራቸዉ ይሄ የሚያመልክተን ዲያቢሎስ ሰዎችን ለሰዶማዊነት እንዴት እያዘጋጃቸዉ እንደሆነ ነዉ ምዕራባዊያን ከ16 ዓመት በላይ ለሆኑት ታዳጊዎች የግለ ወሲብ ትምህርትን በሰፊዉ እየሰጡ እንደሆነ በድህረ ገጻቸዉ ላይ በዝርዝር አስፍረዋል ይሄንን ጸያፍ ምግባር በዓመት ለ1.2 million ሰዎች ማስተማር እንዳለባቸዉ አልፈዉ ተርፈዉም በማዕረግ እንደሚያስመርቁም ይናገራሉ፡
431 viewsedited  19:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-09 23:15:52 በምድር ያለዉ ማደሪያ ቤታችን ቢፈርስም በሰማይ በእግዚአብሔር ዘንድ የሰዉ እጅ ያልሰራዉ ዘለዓለማዊ ቤት እንዳለን እናዉቃለን ስለ እርሱ የምንደክምለትን በሰማይ ያለዉን ቤታችንን እንለብስ ዘንድ እርሱን ተስፋ እናደርጋለን። ከለበስነዉም በኋላ ዕራቁታችንን የምንገኝ አይደለንም። በዚህ ቤት ዉስጥ ሳለንም ከከባድነቱ የተነሳ እጅግ እናዝናለን ነገር ግን ሟች በሕይወት ይዋጥ ዘንድ ሌላ ልንለብስ እንጂ ልንገፈፍ አንወድም ለዚህም ያዘጋጀን እግዚአብሔር ነዉ እርሱም የመንፈስ ቅዱስን ፈለማ ሰጠን። እንግዲህ ሁልጊዜ እመኑ ጨክኑም በዚህ ሥጋ ሳላችሁም እናንተ እንግዶች እንደ ሆናችሁ ታዉቃላችሁ ከሥጋችሁ ተለይታችሁ ወደ ጌታችን ትሄዳላችሁ በእምነት እንኖራለን በማየትም አይደለም ታምነናል ይልቁንም ከሥጋችን ተለይተን ወደ ጌታችን እንሄዳለንና ደስ ይለናል አሁንም ብንኖርና ብንሞትም እርሱን ደስ ለማሰኘት እንጥራለን መልካም ቢሆን ክፉም ቢሆን በሥጋችን እንደ ሠራነዉ ዋጋችንን እንቀበል ዘንድ ሁላችን በክርስቶስ የፍርድ ዙፋን ፊት እንቆማለን።
2ኛቆሮ፤5፤1-10 ንስሀ መግባትን አንዘንጋ።

@Nkuyemedankenzare
562 views20:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-07 18:20:55
በመከራቸዉ ጊዜ በማለዳ ወደ እኔ ይገስግሳሉ እንዲህም ይላሉ፥ ኑ ወደ አምላካችን ወደ እግዚአብሔር እንመለስ እርሱ ሰብሮናልና እርሱም ይፈዉሰናል እርሱ መትቶናልና እርሱም ይጠግነናል ከሁለት ቀን በኋላ ያድነናል በሦስተኛዉም ቀን ያስነሳናል!
ትንቢተ ሆሴዕ፤6፤1-3

@Nkuyemedankenzare
759 views15:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ