የሰርጥ አድራሻ:
ምድቦች:
ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች:
3.02K
የሰርጥ መግለጫ
ይህ ጉባኤ ቤት(ቻናል)፦ አፈ በረከት የሆኑ የቤተ ክርስቲያን አባቶች ተግሳጻትን፣ መንፈሳዊ የሆኑ አነቃቂ ስብከቶችን እንዲሁም አጫጭር የሆኑ ፊልሞችን የምናቀርብበትና የምንዘክርበት ጉባኤ ቤት ነው✞
ለማንኛውም ሀሳብና አስተያየት
@God_Listen
Ratings & Reviews
Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.
5 stars
0
4 stars
0
3 stars
0
2 stars
1
1 stars
1
የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች
2022-08-23 21:09:12
"አቤቱ አምላኬ እግዚአብሔር ሆይ አንጻኝ በአንተ ፊት ምንም መልካም ሥራ ያልሠራሁ ኃጢአተኛ ነኝና አቤቱ አንጻኝ።ከክፉ ነገር ሁሉ አውጣኝ ጠብቀኝ፤ከእኔ ጋርም ሁን ብቻየን ነኝና አትተወኝ አትለየኝ፤የኃጥያተኛ አንደበቴን በድፍረት ከፍቻለሁና ቅዱስ የሆነውን ስምህን አመሰግናለሁ።ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ዛሬም ዘወትርም ለዘለዓለሙ አሜን።"
ʝ𝖔𝖎𝖓 @Gubaye_Afe_Werk
627 viewsЅ𝖆𝖒𝖚 Є𝖑 G𝖞𝖙𝖙𝖆, edited 18:09
2022-08-09 21:29:48
ድንግል ሆይ !
ሰማይ በጠቆረበት ፣ ምድር በኃጢአት የጋለ ናስ በሆነችበት ፣ ነቢያት ከተነሡ አራት መቶ ዓመታት ባለፈበት ፣ የነፍስ ገዥ ዲያብሎስ ፣ የሥጋ ገዥ ሮማውያን በሰለጠኑበት ፣ ሃይማኖት በአጥባቂ ፈሪሳውያን ፣ በለዘብተኛ ሰዱቃውያን ፣ በመናኝ ኤሴያውያን ቡድኖች በተከፈለበት ፣ ሊቀ ካህንነት መኰንን ፣ ካህን በገዛ ቤቱ ደመወዝተኛ በሆኑበት ፤ ዓለሙ በአንድ ልዕለ ኃያል አገር ሥር በወደቀበት ፣ የሰው ልጅ በጣዖት አምልኮ መንፈሱ ፣ በሄለናውያን የኑሮ ዘይቤ ኑሮው በተቃወሰበት ፣ ምዕራብና ምሥራቅ ገመድ በሚጓተቱበት ፣ ፈራጆች በዝተው ሁሉም “እኔ ከደሙ ንጹሕ ነኝ” እያለ እጁን በሚታጠብበት ፤ በዚያ ዘመነ ጽልመት ፣ ዓመተ ፍዳ ዓመተ ኩነኔ ፣ የጌታን ዓመት በሚጠባበቁበት ፣ ዓመተ ሰብእ መቼ ያበቃ ይሆን ? ተብሎ በሚናፈቅበት በአስጨናቂው ወራት …..
ነቢይ ጠፍቶ ምክር ፣ ካህን ጠፍቶ ምሥጢር ጠባቂ ናዛዥ ፣ ንጉሥ ጠፍቶ መንጋ ሰብሳቢ ባልተገኘበት ፤ በዚያ የመርዶ ዘመን ጆሮዎችሽ የምሥራች ስለ ሰሙ ፣ ዓለሙ ሁሉ የሚሰማውን የምሥራች ያንቺ ጆሮዎች ሁሉን ወክለው ስለ ሰሙ ፣ ዓለሙ ሁሉ ወጥቶ ሊቀበለው የሚገባውን ጌታ በማኅፀንሽ ስለተቀበልሽው ፣ በአንቺ ድልድይነት ሰውና እግዚአብሔር ቤተ ዘመድ ስለሆኑ ፣ ዘላለማዊ አምላክ ደኃራዊ ሥጋን ተዋሕዶ አንቺ የወልድ መቅደሱ ፣ ማኅፀንሽ መንበረ ፀባዖት ፣ የንጉሡ የክብር ዙፋን ስለሆነ ማርያም ሆይ ደስ ይበልሽ !
ሰማይ የሰማያት ሰማይ የማይወስኑት በማኅፀንሽ ስላደረ ፣ ከሰፊው ዓለም ይልቅ ያንቺን ጠባብ ማኅፀን ስለመረጠ ፣ ከሥጋሽ ሥጋ ከነፍስሽ ነፍስ ነሥቶ አማኑኤል ስለተባለ አንቺን የመረጠ ቡሩክ ነውና ሰላም እለዋለሁ ! ኪሩቤል ቢሸከሙት አያዩትም ፣ አንቺ ግን በዓይኖችሽ ያየሽው ነሽና ከኪሩቤል ትበልጫለሽ ! ድንግል ሆይ ደስ ይበልሽ ! የዘላለም አምላክ በማኅፀንሽ የዕለት ፅንስ ሆነ ። ዘላለምና ዕለት በአንድ ላይ የተገናኙት ባንቺ ማኅፀን ነው ። ዘመን ካለ ዘላለም ፣ ዘላለም ካለ ዘመን የለም ። ሰውና እግዚአብሔር የታረቁብሽ የምሕረት አደባባይ ነሽ ። የልጅሽ ጌትነት የታየው ያንቺ ክብረት ይታየዋል ። ልጅሽን የሚወድ ይወድሻል ። ለምንና እንዴት የሚሉ ጥያቄዎች የተገዙልሽ ፣ “በበረት እንድወልድ ለምን ወሰነ ?” ብለሽ ያላዘንሽ ፣ እንዴት ይሆናልን “ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለም” በሚል ቃለ አሚን የረታሽ አንቺ ነሽ ። እመ ኢየሱስ ፣ እኅተ ኢየሱስ ሁነሽ ባሕረ እሳት ሲከፈል “ነፍሴ ጌታን ታከብረዋለች” ብለሽ የዘመርሽ ሐዲስ ማርያም ሰላምታ ይገባሻል !
ዛሬም እንደ ጥንቱ ችግራችን አንቺ በሥጋ ከነበርሽበት ዘመን ጋር ተመሳስሏል ። የምልጃሽ በረከት አብሳሪ መልአክን ይላክልን ። ፍልሰትሽ ትንሣኤያችንን ፣ ዕርገትሽ የምእመናንን መነጠቅ ያስታውሳል ። የሆነልሽ ግን ከሆነልን በላይ ነውና ክብር ይገባሻል !
ድንግል ሆይ …..
ኖላዊʝ𝖔𝖎𝖓 @Gubaye_Afe_Werk
1.5K viewsЅ𝖆𝖒𝖚 Є𝖑 G𝖞𝖙𝖙𝖆, edited 18:29
2022-07-25 13:49:33
"የዳነች ነፍስ የቆሰለች ሥጋን ማበርታት ትችላለች ፤ የተፈወሰች ሥጋ ግን የቆሰለች ነፍስን ማሳረፍ አትችልምና ለነፍስህ መዳን ቅድሚያ ስጥ ። በምድር ጌታ ፣ በሰማይ ከርታታ ከመሆን ፤ በምድር ከርታታ ፣ በሰማይ ጌታ መሆን ይሻላል ። የከተሞች ውበት የሰው እጅ ሥራ ፣ የገጠሮች ውበት የእግዚአብሔር ሥራ ነው ። የእግዚአብሔርን ሥራ ለማየት ወጣ ባልህ ቍጥር ዓይኖችህ ከአድማስ አድማስ ለማየት ነጻነትን ያገኛሉ ። ያልተበረዘ ማንነትና ሰይጣናዊ ብልጠት የሌላቸውን ሰዎች ታገኛለህና ከከተማ ወጣ ያሉትን ገጠራማ መንደሮች አዘውትርባቸው ።"
ኖላዊʝ𝖔𝖎𝖓 @Gubaye_Afe_Werk
3.9K viewsЅ𝖆𝖒𝖚 Є𝖑 G𝖞𝖙𝖙𝖆, edited 10:49
2022-07-23 17:54:55
"ያኔ ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ ሰው ኹሉ በተሰበሰበት አደባባይ ፊት ከምናፍር ዛሬ በአንድ ንስሐ አባት ፊት ማፈር ይሻለናል፡፡"
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅʝ𝖔𝖎𝖓 @Gubaye_Afe_Werk
2.2K viewsЅ𝖆𝖒𝖚 Є𝖑 G𝖞𝖙𝖙𝖆, 14:54
2022-07-13 10:03:44
"በቅዱስ ወንጌል ውስጥ የምትወደውን እያመንክ የማትወደውን ካልተቀበልክ የምታምነው ወንጌልን ሳይሆን እራስህን ነው።"
ቅዱስ አውግስጢኖስ𝚓𝚘𝚒𝚗 @Gubaye_Afe_Werk
2.0K viewsЅ𝖆𝖒𝖚 Є𝖑 G𝖞𝖙𝖙𝖆, edited 07:03
2022-07-12 14:32:49
"አንደኛው በመስቀል ላይ ተዘቅዝቆ ተሰቀለ፤ አንደኛውም ክብርት አንገቱን ተቆረጠ።"
"በንጉሥ ኔሮን ዘመን ሩጫቸውን(ተጋድሎአቸውን) ለፈጸሙ ለሁለቱ ብርሃናት ሰላም እላለሁ።ጴጥሮስ እና ጳውሎስ የዘንባባ ዝንጣፊ ይዘው(የሰላምን ወንጌል እየሰበኩ) አንደኛው በመስቀል ላይ ተዘቅዝቆ ተሰቀለ፤ አንደኛውም ክብርት አንገቱን ተቆረጠ።
"
ሰላም ዕብል ብርሃናተ ክልኤተ
በአጸደ ንጉሥ ኔሮን እለ ፈፀሙ ረፀተ
ጳውሎስ ወጴጥሮስ እንዘ ይጸወሩ ፀበርተ
አሐዱ በመስቀል ተሰቅለ ቁልቁሊተ
ወአሐዱ ተመትረ ክሳዶ ክብርተ"መልክዐ ጴጥሮስ ወጳውሎስ𝚓𝚘𝚒𝚗 @Gubaye_Afe_Werk
1.9K viewsЅ𝖆𝖒𝖚 Є𝖑 G𝖞𝖙𝖙𝖆, edited 11:32
2022-07-04 10:04:01
"እግዚአብሔር በደመናና በወጀብ መካከል ሆኖ ኢዮብን የምጠይቅህ ነገር አለኝ፤ ያም ባይሆን ነገሬን አድምጥ እኔ እነግርሃለሁ፤ የምድር ልኳ ምን ያህል ነው? ምድርን በምን መሠረትኳት? በሄሞትና በሌዋታን እንዴት አዞርዃቸው? የዝናም አባቱ ማን ነው? ዝናምን ማን አሰገኘው? የነጠብጣቡን ጠብታ ማን ያወጣዋል? ወደ ምድር ዝናምን የማዘንበው በተራሮች ላይም ሣርን የማበቅለው እኔ አይደለሁምን? ለእንስሳት ምግባቸውን እሰጣቸዋለሀ፤ እጆቼ ይህን ሁሉ ሠርቷል።"
ድጓ ዘክረምት
ቅዱስ ያሬድ𝚓𝚘𝚒𝚗 @Gubaye_Afe_Werk
5.0K viewsЅ𝖆𝖒𝖚 Є𝖑 G𝖞𝖙𝖙𝖆, edited 07:04
2022-06-29 20:53:10
"ድንግል ሆይ አንገታቸውን እንደሚያገዝፉ እንደ ዕብራውያን ሴቶች ልጆች በዋዛ ያደግሽ አይደለም፤ በንጽሕና በቅድስና በቤተመቅደስ ኖርሽ እንጂ፤ ድንግል ሆይ ምድራዊ ኅብስትን የተመገብሽ አይደለም፤ ከሰማየ ሰማያት የበሰለ ሰማያዊ ኅብስትን ነው እንጂ፤ ድንግል ሆይ ምድራዊ መጠጥን የጠጣሽ አይደለም፤ ከሰማየ ሰማያት የተቀዳ ሰማያዊ መጠጥን ነው እንጂ።"
አባ ሕርያቆስ
ቅዳሴ ማርያም𝚓𝚘𝚒𝚗 @Gubaye_Afe_Werk
2.3K viewsЅ𝖆𝖒𝖚 Є𝖑 G𝖞𝖙𝖙𝖆, edited 17:53
2022-06-16 22:13:01
“ደካሞችን እጠቅም ዘንድ ለደካሞች እንደ ደካማ ሆንሁ፤ በሁሉ መንገድ አንዳንዶችን አድን ዘንድ፥ ከሁሉ ጋር በሁሉ ነገር እንደ እነርሱ ሆንሁ።”
1ኛ ቆሮንቶስ 9፥22𝚓𝚘𝚒𝚗 @Gubaye_Afe_Werk
5.9K viewsЅ𝖆𝖒𝖚 Є𝖑 G𝖞𝖙𝖙𝖆, edited 19:13
2022-06-14 07:52:22
"ድካማችሁን በእግዚአብሔር ፊት ጣሉ እግዚአብሔርም ብርታት ይሆንላችኃል።"
አባ ሙሴ ጸሊም𝚓𝚘𝚒𝚗 @Gubaye_Afe_Werk
2.7K viewsЅ𝖆𝖒𝖚 Є𝖑 G𝖞𝖙𝖙𝖆, edited 04:52